ቱርክዬ በሽብር የተከሰሱ ኩርዶች ተላልፈው እንዲሰጧት ለስዊድን ያቀረበችው ጥያቄ ውድቅ ሆነ
አንካራ 70 የኩርድ ታጣቂዎችን እንድትሰጣት ስዊድንን ብትጠይቅም ተቀባይነት አለማግኘቷ ተገልጿል፡፡
ሆኖም ስዊድን እና ፊንላንድ የአንካራን ጥያቄዎች የማያሟሉ ከሆነ የኔቶ አባልነታቸው ጥያቄ ውስጥ እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን አስጠንቅቀዋል፡፡
ስዊድን እና ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን ተፈራርመዋል፡፡ አባልነታቸውን ተቃውማ የነበረችው ቱርክዬም የኋላ ኋላ ጥያቄያቸውን ተቀብላለች፡፡
አሁን ግን ጥያቄዎቿ ካልተሟሉ ወደ ድጋፏን ልታነሳ እንደምትችል ነው አንካራ የዛተችው፡፡

