አቶ ደመቀ መኮንን ”በወለጋ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል ይደረጋል” አሉ
ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ በዜጎች ላይ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት በሁሉም አካባቢዎች ተጋላጭ ቀበሌዎችንና መንደሮችን በመለየት አስፈላጊው ጥበቃ እንደሚደረግ ገለጹ።
ከዚህ ባለፈም ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል የሚሊሻ እና የኮሙኒቲ ፖሊሲንግ ስርዓት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚደረግም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት።

