ሩሲያ በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለች
ሩሲያ በስንዴ እና በሌሎችም የእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ገለጸች።
ሩሲያ ይህን የገለጸችው በኢንዶኔዥያ መካሄድ በጀመረው የቡድን 20 (G20) አባል ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ነው።
በስብሰባው የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሃገራቸው በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
ቱርክ ከሰሞኑ ከዩክሬን የተሰረቁ የእህል ምርቶችን የጫኑ ናቸው ያለቻቸውን የሩሲያ የጭነት መርከቦች መያዟ ይታወሳል።

