
ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቷን በቀን ወደ 13 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ መወሰኗን አስታወቀች
ትናንት በተካሄደው የገልፍ ሀገራት-አሜሪካ የልማትና ደህንነት ጉባዔ ላይ ትኩረት ከነበሩት ውስጥ አንዱ የነዳጅ ጉዳይ ነበር።
የሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን፤ “ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ያገናዘበ ሚዛናዊ አካሄድ መከተልን ይጠይቃል” ብለዋል።
ከነዳጅ ጋር ተያይዞ ሊያጋጥም የሚችል እጥረትን ለመቅረፍም ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቷን በቀን ወደ 13 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ መወሰኗንም አስታውቀዋል።
