News today, Politics

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አቀባበል ተደርጎላቸዋል
አረብ ኢሚሬትስና ፈረንሳይ በኢነርጂና በትራንስፖርት መስኮች እንደሚፈራራሙ ይጠበቃል

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት መሀመድ ቢን ዛይድ የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን በይፋ ጀምረዋል።

በትናንትናው ለት ምሽት ፈረንሳይ ፓሪስ የደረሱት
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ ዛሬ በፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑዔል ማክሮን በኤሊሴ ቤተ መንግስት ይፋዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።0
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በኤሊሴ ቤተመንግስት ከፈረንሳይ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተገናኝተው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የፈረንሳይ ባለስልጣናትን ያነጋግራ።

ሼህ መሀመድ ቢን ዛይድ አልነሃያን በፈረንሳይ ቆይታቸው በኢነርጅ እና በትራንስፖርት መስኮች እንደሚፈራራሙ ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

የፈረንሳዩ ጉብኝት ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ በኋላ ያደረጉት የመጀመሪያ አለምአቀፍ ጉብኝት ነው፡፡

Leave a comment