News today, Politics

የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚልኩት የነዳጅ መጠን በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ

የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚልኩት የነዳጅ መጠን በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ

ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚላከው የድፍድፍ ነዳጅ መጠን ካሳለፍነው ጥር ወር ወዲህ በ90 በመቶ መጨመሩ ተገለፀ።

የነዳጅ ፍላጎቱ የጨመረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎ የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነው።

ብሉምበርግ ባወጣው ሪፖርት መሰረት ባሳለፍነው 20 ቀናት ብቻ 1 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከሳዑዲ አረቢያ በግብጽ በኩል በሚያልፍ መስመር ወደ አውሮፓ የገባ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊየን በርሜል ደግሞ በስዊዝ ካናል በኩል ወደ አውሮፓ ገብቷል።