የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚልኩት የነዳጅ መጠን በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ
ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚላከው የድፍድፍ ነዳጅ መጠን ካሳለፍነው ጥር ወር ወዲህ በ90 በመቶ መጨመሩ ተገለፀ።
የነዳጅ ፍላጎቱ የጨመረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎ የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነው።
ብሉምበርግ ባወጣው ሪፖርት መሰረት ባሳለፍነው 20 ቀናት ብቻ 1 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከሳዑዲ አረቢያ በግብጽ በኩል በሚያልፍ መስመር ወደ አውሮፓ የገባ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊየን በርሜል ደግሞ በስዊዝ ካናል በኩል ወደ አውሮፓ ገብቷል።
