Politics

ዩጋንዳ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ከፈለች

ዩጋንዳ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ከፈለች

የዩጋንዳ ወታደሮች ከ23 ዓመት በፊት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ግዛት ገብተው ጥቃት ፈጽመው ነበር።

ዲሞክራቲክ ኮንጎም ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት በመውሰድ ክስ መስርታ ነበር።

በዚህ ችሎት ላይ የዩጋንዳ ወታደሮቿ ባደረሱት ጉዳት መሰረት ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 325 ሚሊዮን ዶላር በአምስት ዙር ክፍያ ካሳ እንድትከፍል የተወሰነባት ቢሆንም ላለፉት በርካታ ዓመታት ሳትከፍል ቆይታለች፡፡

በችሎቱ የተረታችው ዩጋንዳም ከ325 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ውስጥ 65 ሚሊዮን ዶላር ገንዘቡን ከቀናት በፊት እንደከፈለች ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

የዲሞክራቲክ ኮንጎ መንግስት ቃል አቀባይ ከዩጋንዳ መንግስት 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ክፍያው እንደተከፈላቸው አረጋግጠዋል፡፡

ዩጋንዳ የጎረቤቷን ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሉዓላዊ ድንበሯን ጥሳ በመግባት ከ10 ዓመት በላይ በርካታ ቦታዎችን በመቆጣጠር እና አማጺያንን በመርዳት ወንጀል ተከሳ ጥፋተኛ ተብላለች፡፡

በመጨረሻም ዩጋንዳ ጥፋቷን አምና ካሳዋን መክፈል መጀመሯን እና ከጎረቤቷ ጋር መልካም ግንኙነት እንደምትፈልግ አስታውቃለች፡፡

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya