News today, Politics

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ
አርመን እና አዘርባጃን ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው


የአርመኒያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኒኮል ፓሺኒያን በትናንትናው እለት ከአዘርባጃን ጋር በነበረው ጦርነት 49 የአርመን ወታደሮች ተገድለዋል ሲሉ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።


በአርመን ፖርላማ ቀርበው ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዘርባጃን የአርመንን ይዞታዎች ማጥቃቷን እና ጦርነቱ አሁንም መቀጠሉን ተናግረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ግጭቱ ወደ ጦርነት እንዲያመራ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው።


በአርመን እና አዘርባጃን መካከል ለአስርት አመታ ያሰቆጠረው አለመግባባት ኒጋርኖ ካራባክ በተባለ ቦታ መጀመሩ ይታወሳል።


በኒጋርኖ ካራባክ የተመረው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ቆሞ የነበረ ቢሆንም በድጋሚጨሊቀሰቀስ ችሏል።
ሪሲያ እና አሜሪካ ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።