በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ
አርመን እና አዘርባጃን ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው
የአርመኒያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኒኮል ፓሺኒያን በትናንትናው እለት ከአዘርባጃን ጋር በነበረው ጦርነት 49 የአርመን ወታደሮች ተገድለዋል ሲሉ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
በአርመን ፖርላማ ቀርበው ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዘርባጃን የአርመንን ይዞታዎች ማጥቃቷን እና ጦርነቱ አሁንም መቀጠሉን ተናግረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ግጭቱ ወደ ጦርነት እንዲያመራ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው።
በአርመን እና አዘርባጃን መካከል ለአስርት አመታ ያሰቆጠረው አለመግባባት ኒጋርኖ ካራባክ በተባለ ቦታ መጀመሩ ይታወሳል።
በኒጋርኖ ካራባክ የተመረው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ቆሞ የነበረ ቢሆንም በድጋሚጨሊቀሰቀስ ችሏል።
ሪሲያ እና አሜሪካ ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
