News today, Politics, social life

ግብፅና ኳታር በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች በትብብር ለመስራት ስምምነት ተፈራረሙ

የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ ከ4 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር ጉብኝት አድርገዋል

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም በሁለትሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል

የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አል ሲሲ በኳታር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተገልቷል።

ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ ከአራት ዓመታት ወዲህ በሳለፍነው ማክሰኞ ለመጀመሪያ ጊዜ ዶሃ ሲደርሱም በኳታር ኢሚር ታሚም አቀባባበል ተደርጎላቸዋል።

በትናትናው እለትም የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ እና የኳታሩ ኢሚር ታሚም በሀገራ የሆለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተመካክረዋል።

በዚህም የኳታሩ ኢሚር ታሚም ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እንዲያደግ እየሰሩት ላው ስራ ማማስገናቸውን የኳታር የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል።

የፕሬዝዳንት አል ሲሲ ግብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናከር እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በበኩላቸው፤ ግብጽ ከኳታ ጋር በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ እና በደህንነት ዘርፎች ከኳታር ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ውይይቱን ተከትሎም ሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተካሄደ ሲሆን፤ ከስምምነቶቹ ውስጥም ልማትና ኢንቨስምንት እንዲሁም የማህበራዊ ዘርፍ ይገኝበታል።