News today

ሩሲያ በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለች

ሩሲያ በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለች

ሩሲያ በስንዴ እና በሌሎችም የእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ገለጸች።
ሩሲያ ይህን የገለጸችው በኢንዶኔዥያ መካሄድ በጀመረው የቡድን 20 (G20) አባል ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ነው።
በስብሰባው የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሃገራቸው በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
ቱርክ ከሰሞኑ ከዩክሬን የተሰረቁ የእህል ምርቶችን የጫኑ ናቸው ያለቻቸውን የሩሲያ የጭነት መርከቦች መያዟ ይታወሳል።

News today

የነዳጅ ላኪ ሀገራት ዋና ፀሀፊ አረፋ

የነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) ዋና ጸሐፊ ህይወታቸው አለፈ
የነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) ዋና ጸሐፊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ናይጄሪያዊው ዋና ጸሐፊ ሞሐመድ ባርኪንዶ በ63 ዓመታቸው ነው ህይወታቸው ያለፈው። የናይጄሪያ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ሃላፊን ጨምሮ ሁለት የኦፔክ ምንጮች የዋና ጸሐፊውን ማረፍ አስታውቀዋል።

News today

የአውሮፓ ህብረት ለ ኢትዮጵያዊ 81m ዩሮ

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ81 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ሊያደርግ ነው

የህብረቱ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ድጋፉን ለማድረግ የሚያስችሉ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል፡፡
ቻርለስ ሚሼል ይህን ይፋ ያደረጉት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ ነው፡፡

News today

Ethiopia | አርቲስት ሀናን ታሪክ በዛሬው ዕለት የ”ኢንጂ ፈርኒቸር” ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተፈራርማለች

ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተፈራርማለች

ቡሩል ትሬዲንግ ኃ / የተ / የግ / ኩባንያ ( Burul Trading PL.C. ) እ.ኤ.አ መስከረም 2016 የተመሰረተ አስመጪና ላኪ ኩባንያ ሲሆን ፤ ኩባንያው “ ኢንጂ ፈርኒቸር ”የሚል የብራንድ ስያሜ በመያዝ ! “ ይታሽ ሞቢሊያ ” የተባለው እድሜ ጠገብና ግዙፍ የቱርክ ፈርኒቸር ኩባንያ ወኪል በመሆን የሚሰራ ነው ፡፡

በተጨማሪም ኩባኒያው ባለፉት ስድስት ዓመታት ባደረገው ጥረት ፤ ኢንጂ ፈርኒቸር በአሁነ ጊዜ ለሦስት የተለያዩ ታዋቂ የቱርክ ፈርኒቸር ኩባንያዎች “ የምስራቅ አፍሪካ ገበያ ብቸኛ ወኪል ” በመሆን እየሰራ ይገኛል ።

የኢንጂ ፈርኒቸር ዋና መሥሪያ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፤ በሴንቸሪ ሞል አካባቢ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም አዲስ አበባ ውስጥ ሴንቸሪ ሞል ሦስተኛ ፎቅ እና ግራውንድ ፎቅ ላይ ሁለት ሾው ሩም በመክፈት ለደንበኞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው።

ኢንጂ ፈርኒቸር የሚለውን የብራንድ ስም የመረጠው ፤ በሾው ሩማቸው ውስጥ የሚገኙትንና ከተለመደው ወጣ ያሉ ቅንጡ ውብና ማራኪ ፈርኒቸሮች የሚወክል ስያሜ በመሆኑ ነው።

ኢንጂ ፈርኒቸር እስካሁንም በልዩ ትእዛዝና በከፍተኛ ጥራት የሚመረቱ ፤ እጅግ ቅንጡ ፤ ከተለመደው ወጣ ያሉ ቅንጡ ፤ ውብና ማራኪ ፈርኒቸሮች የሚወክል ስያሜ በመሆኑ ነው ፡፡

ዘመናዊ የነገውን ፋሽን መሰረት ያደረጉ ፤ አዳዲስና ብራንድ የቤትና የቢሮ ፈርኒቸሮችን በከፍተኛ ወጪ በማስመጣት ፤ የውስጥ ዲዛይን ማማከርን ጨምሮ የተገዙ ፈርኒቸሮችን ደንበኞች ባሉበት ቦታ የማድረስና የማስረከብ አገልግሎቶችን በመስጠት ረገድም ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ግንባር ቀደምና ታዋቂ ኩባንያ ነው ፡፡

ኩባንያው አዲስ አበባ ከከፈተው የምስራቅ አፍሪካ ወኪል ቢሮ በተጨማሪ ፤ በናይኖቢ ፤ ኬንያ ሌላ አስመጪና ላኪ ኩባንያ አቋቁሞ እየሰራ ሲሆን ፤ በናይሮቢ የመጀመሪያውን ሾው ሩም እ.ኤ.አ. መስከረም 2022 ለመክፈት የሚያስችለውን የዝግጅት ሂደት አጠናቅቋል ፡፡

እንዲሁም ፤ በደንበኞቹ ጥያቄ መሰረት ፤ የሆቴልና የአፓርትመንት ፕሮጄክት ቅንጡ ፈርኒቸሮችን በማስመጣት በኬንያ ፤ በደቡብ ሱዳን ፤ በናይጄሪያና በታንዛኒያ ለሚገኙ ደንበኞቹ በማቅረብ ! ለአስመጪነት ስራው የሚያውለው ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጭምር የውጭ ምንዛሪ ገቢ በማስገኘትና ለዜጎች የስራ እድል በመክፈት ረገድ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል ፡፡

ኢንጂ ፈርኒቸር በአሁነ ጊዜም ምርትና አገልግሎቱን በውጤታማ ስልትና በላቀ ደረጃ በማስተዋወቅ ቢዝሱን በከፍተኛ ጥራትና ቅልጥፍና ለማሳደግ ፤ “ ተወዳጇን አርቲስት ሃናን ታሪክን ታዋቂ ኢትዮጵያዊ የኩባንያው የብራንድ አምባሳደር አድርጎ በዛሬው ዕለት በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል አስፈርሟል።


ቴዲሾው መልቲ ሚዲያ
ህጋዊ ሰውነት አግኝቶ በማስታወቂያ የስራ ዘርፍ የተሰማራው ቴዲ ሾው መልቲ ሚዲያ፤ ባለፉት አምስት አመታት ባደረገው ጥረት፤ በርካታ የቪዲዮና የድምፅ ማስታወቂያ ክርኤቲቭ ፕሮዳክሽን ስራዎችን በጥራት በማከናወን ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ደንበኞች አስረክቧል፡፡

ከዚህ አንፃር ቴዲ ሾው የማስታወቂያ ኢንዱስትሪውን ከተቀላቀለ ወዲህ ማከናወን ከቻላቸው ስራዎች የሚከተሉት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፤

• ከ300 በላይ የቴሌቪዥን ማስታወቂያዎችን ለአገር ውስጥ ድርጅቶች ሰርቶ አስረክቧል

• ከ225 በላይ የሬዲዮ ማስታወቂያዎችን ለአገር ውስጥ ድርጅቶች ሰርቶ አስረክቧል

• 7-የቪዲዮና የኦዲዮ ፕሮዳክሽንኖችን በመስራት፤ በውጭ አገር ለሚገኙ ዓለም-አቀፍ ጅርጅቶች አስረክቧል

• እስካሁን 8-የብራንድ አምባሳደር ማስታወቂያ ስራዎችን የስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ያዘጋጀ ሲሆን፤ በዛሬው እለትም ባዘጋጀው ዘጠንኛው የብራንድ አምባሳደር ፊርማ ስነ-ስርአት፤ አናን ታሪክ የተባለቸውን ታዋቂ ኢትዮጵያዊ አርቲስት ከቡሩል ትሬዲንግ ጋር በከፍተኛ የኢትዮጵያ ብር በማፈራረም ስራ አስጀምሯል፡፡

News today

ሩሲያ

ሩሲያ በድል ላይ ድል እያደረገች ነው አሁን ደግሞ በአርክቲክ ባህር ላይ 82 ሚሊየን ቶን ጋዝ አግኝታለች

Ethiopia ሩሲያ መላውን ሉሀንስክ ተቆጣጠረች በዚህም የሞስኮ ኗሪዎች ሀገራቸው ደል በማድረጓ አዲስ ውሳኔ ወስነው አክብረዋል በዚህም መሰረት የአሜሪካ ኤምባሲ የሚገኝበትን አከባቢ የዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ሲሉ የኢንግሊዝ ኤምባሲ ደግሞ የሉሀንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ሲሉ ሰይመውታል።
News today, Politics

ቱርክዬ በሽብር የተከሰሱ ኩርዶች ተላልፈው እንዲሰጧት

ቱርክዬ በሽብር የተከሰሱ ኩርዶች ተላልፈው እንዲሰጧት ለስዊድን ያቀረበችው ጥያቄ ውድቅ ሆነ

አንካራ 70 የኩርድ ታጣቂዎችን እንድትሰጣት ስዊድንን ብትጠይቅም ተቀባይነት አለማግኘቷ ተገልጿል፡፡
ሆኖም ስዊድን እና ፊንላንድ የአንካራን ጥያቄዎች የማያሟሉ ከሆነ የኔቶ አባልነታቸው ጥያቄ ውስጥ እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን አስጠንቅቀዋል፡፡
ስዊድን እና ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን ተፈራርመዋል፡፡ አባልነታቸውን ተቃውማ የነበረችው ቱርክዬም የኋላ ኋላ ጥያቄያቸውን ተቀብላለች፡፡
አሁን ግን ጥያቄዎቿ ካልተሟሉ ወደ ድጋፏን ልታነሳ እንደምትችል ነው አንካራ የዛተችው፡፡

News today, social life

ስለቀጠለው የወለጋ ጥቃት

አቶ ደመቀ መኮንን ”በወለጋ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል ይደረጋል” አሉ

ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ በዜጎች ላይ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት በሁሉም አካባቢዎች ተጋላጭ ቀበሌዎችንና መንደሮችን በመለየት አስፈላጊው ጥበቃ እንደሚደረግ ገለጹ።

ከዚህ ባለፈም ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል የሚሊሻ እና የኮሙኒቲ ፖሊሲንግ ስርዓት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚደረግም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት።