News today, Technology

ቻይና “አሜሪካ 10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ፈጽማብኛለች” አለች

ቻይና የተፈፀመባት የመረጃ ጠለፋ በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም የተመራ ነው ብላለች

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ተቋም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃቶቸን እንደፈጸመባት ቻይና ገለጸች።

በአሜሪካ የሳይበር ጥቃቶችም 140 ጊጋ ባይት ጠቃሚ መረጃዎች መሰረቃቸው እንዳልቀረ የቻይና ብሄራዊ የኮምፒውተር ቫይረስ ግብረ መልስ ኃይል እና ኪሆ የተባለው የኢንተርኔት ደህንነት ተቋም ባጋራ ባካሄዱት ምርመራ አስታውቀዋል።

ተቋማቱ ምርመራውን ማካሄድ የጀመሩት የቻይና ሰሜናዊ የፖሊ ቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር ላይ የሳይበር ጥቃት እንደተፈፀመበት ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

ተቋማቱ ጥቃቱን የፈፀመውን ኔትዎርክት ዱካ ተከትለው ባደረጉት ምርመራም ጠላፊው በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም አካል በሆነው ትሮይድ አክሰስ ኦፕሬሽን ቢሮ እንደተፈጸመ ደርሰንበታል ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲ ላይ በተፈፀመው የሳይበር ጥቃት በቀጥታ 13 ሰዎች መሳተፋቸው እና የመረጃ ጠላፊዎ የዩኒቨርሲቲዉን የመረጃ ደህንነት መጠበቂያ (ፋየርዎል) ለማለፍ ከ41 በላይ መሳሪያዎችን መጠቀማቸው ተነግሯል።

ጠላፊዎቹ ማንነታቸውን ለመሸፈን ኢራን፣ ደቡብ ኮሪ እና ጃፓንን ጨምሮ በ17 ሀገራት አይ.ፒ እቀያየሩ ሲጠቀሙ ነበርም ብሏል ተቋማቱ ባወጡት መረጃ።

ምርመራውያን ያካሄዱት ተቋማት ወደፊት የአሜሪካ የመረጃ ጠለፋ እና የስለላ ዘዴቆች እና መሰሳሪያዎችን ዝርዝር ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርመራ ውጤቱን ተከትሎ ምለሽ ሰጠ ሲሆን፤ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ፤ ቻይና ኢንዲህ አይነት ተጋባራትን በጽኑ ታወግዛለች ብለዋል።

አሜሪካ ከሳይበር ጥቃት ተግበሯ ልትታቀብ ይገባል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ቻይና የኔትዎርክ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከዓለም አቀፉ ማህበረስበ ጋር ትሰራለች ሲሉም ተናግረዋል።

News today, Technology

ሁዋዌይ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሳተላይት የሚሰራ ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ አደረገ

ሁዋዌይ ሜት 40 ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ይፋ የተደረገው

የቻይናው የቴክኖሎጂ ቁሶች አምራች ሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልኩን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉ ተነግሯል።

አዲሱ የህዋዌይ ስማርት ስልክ ከዚህ በፊት በስማርት ስልኮች ላይ ያልተለመደ የሳተላይት ኮሙዩኒኬሽን የተገጠመለት መሆኑን ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

በዚህም ስማርት ስልኩ ከጂ.ፒ.ኤስ ተመሳሳይነት ባለው በቻይናው ቤይ-ዶው ናቪጌሽን ሳተላይት ሲስትም (BDS) ኔትዎርክ አማኝነት በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚባይል ኔትዎርክ ባይኖርም መስራት ይችላል።

 በተጨማሪም አዲሱ ሜት 50 ስማርት ስልክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአሜሪካው የጎግል አንድሮይድ ስማርት ስልክ በመላቀቅ ቻይና በራሷ ባመረተችው አዲስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ለገበያ የሚቀርብ ይሆናል ነው የተባለው።

ይህም ባትሪው ሊዘጋ 1 ፐርሰት እየቀረው 3 ሰዓት እንደቆይ ማድረግ እንደሚያስችልም ኩባያው አስታውቋል።

አዲሱ የሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልክ የባትሪ አቅም 4460 mAh መሆኑን ኩባያው አስታውቋል።

ስማርት ስልኩ ከጀርባው 4 የካሜራ ሌንሶች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሌንሶቹም 50 ሜጋ ፒክስል፣ 13 ሜጋ ፒክሰል እና 12 ሚክስል ናቸው።

ከፊትለፊት አሊያም ሰለፊ ካሜራው ደግሞ 1 ሲሆን፤ የሌንሱ ምስል የማንሳት ጥራትም 13 ሜጋ ፒከስል ነው ተብሏል።

ሁዋዌይ ሜት 40 የተባለ ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ የተደረገው።

በርካቶቸ ሁዋዌይ ስማርት ስልኩን ይፋ ሳያደርግ ይህን ያክል የቆየው አሜሪካ በኩንያው ላይ በጣለችው ማእቀብ ሳቢያ ሳይሆን እንዳልቀረ ያምናሉ።