News today, Politics, social life

ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ


የሩሲያ እና የቱርክ ፕሬዝደንቶች በትናንትናው እለት በሩሲያ ሶቺ ከተማ ተገናኝተው መክረዋል

ሩሲያ እና ቱርክ፤ በሩሲያው ገንዘብ ሩብልስ ለመገበያየት ተስማምተዋል፡፡

የሩሲያ እና ቱርክ መሪዎች በትናንትናው እለት በሩሲያዋ ሶቺ ከተማ ባደረጉት ውይይት የኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት መፈረማቸውን የሩሲያ አርቲ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ያለባትን የውጭ ሀገራት እዳ በራሷ ገንዘብ “ሩብል” እንደምትከፍል አስታወቀች
ስምምነቱ መፈረሙን የገለጹት የቱርኩ ፕሬዝደንት ረሲፕ ተይፕ ኤርዶጋን ናቸው፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬንን የማደራደር ሚያ ያላት ቱርክ ከሩሲያ ጋር በሩብልስ ለመገበያየት መስማማቷን ፕሬዘደንት ኤርዶጋን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አርብ ዕለት በቱርክ እና በሩሲያ ልዑካን መካከል የተካሄዱት ስብሰባዎች ፍሬያማ እንደነበሩ እና በሩሲያ በሚያደርጉት ጉብኝት በሶሪያ ስላለው ሁኔታ ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል።

ሩሲያ በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ ሩሲያ አሜሪካን ጨምሮ ከምእራባውያን ጋር ሁሉን አቀፍ ፍጥጫ ውስጥ ገብታለች፡፡

አሜሪካን ጨምሮ ምእራበውያን ሀገራት ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ማእቀብ ሁሉ በሩሲያ ላይ አዝንበዋል፤ ሩሲያ ማእቀቡን ለመመከት ምእራባውያን ሀገራት ጋዝ በሩብል እንዲገዙ አስገድዳለች፡፡