News today, social life

ሱዳን በጎርፍ ተጥለቀለቀች

በመስከረም ወር ተጨማሪ ዜጎች ለጎርፍ አደጋ ሊጋለጡ እንደሚችሉ ተገልጿል

በሱዳን በጎርፍ የተወሰዱ ሰዎች 112 ደርሷል።

በሱዳን ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 112 ማሻቀቡን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የዓባይ ወንዝ የውሃ መጠን በመጪዎቹ ቀናት የበለጠ ሊጨምር እንደሚችልም የገለፁት የሃገሪቱ የአደጋ መከላከል ባለስልጣናት አስጠንቅቀዋል።

በሱዳን በጎርፍ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 100 ደረሰ
ባለስልጣናቱ በዚህ ወር ብቻ ባጋጠመ አደጋ 112 ሱዳናውያን መሞታቸውንና 115 ሰዎች ደግሞ መጎዳታቸውን አስታውቀዋል።በድምሩ 84 ሺ 40 ቤቶች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መውደማቸው እና መጎዳታቸውንም ተናግረዋል ባለስልጣናቱ።

መሠል የጎርፍ አደጋዎች ለሱዳን አዲስ አይደሉም። ክረምት በመጣ ቁጥርም ያጋጥማል። ሆኖም ዘንድሮ በ1940ዎቹ ካጋጠመውና የከፋ ነበር ከተባለለት የበለጠ የጎርፍ አደጋ ማጋጠሙ ነው የተነገረው።

አደጋው ካለፉት ሁለት የክረምት ወራት ይልቅ በነሐሴ እና መስከረም ወራት ይከፋል መባሉም ብዙዎችን አስግቷል።

የጎርፍ አደጋው በስድስት ግዛቶች እየከፋ የመጣ ሲሆን የሀገሪቱ ወታደራዊ መንግስትም በነዚህ ግዛቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል።

ናይል፣ ዋይት ናይል፣ ኮርዶፋን፣ ዳርፉር እና ካሳላ ግዛቶች በጎርፍ አደጋው ክፉኛ ተጎድተዋል ተብሏል፡፡

እስካሁን ባለው የጎርፍ አደጋ ከ250 ሺህ በላይ ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን በቀጣዮቹ ሳምንታት ተጨማሪ ጉዳት ሊከሰት እንደሚችል ተጠቅሷል።

News today, Politics

ሰሜን ኮሪያ ጥላትን ለማሳሳት በማለት 8 አንድ አይነት ቤተመንግሥት ሰራች


2022/8/29 11:38 GMT

ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን

ቤተ መንግስቶቹ ተመሳስለው የተገነቡት ፕሬዝዳንቱ ያሉበት እንዳይታወቅ እንደሆነ ተገልጿል

ከምዕራባዊያን ጋር እሰጣ አገባ ውስጥ ያለችው ሰሜን ኮሪያ ጠላትን ለማሳሳት በሚል ስምንት ተመሳሳይ ቤተ መንግስቶችን መገንባቷ ተገልጿል።

እንደ ዴይሊ ሜይል ዘገባ ከሆነ ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን ደህንነትን ለመጠበቅ ሲባል በሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ ተመሳሳይ ቅርጽ ያላቸው ቤተመግስቶችን ገንብታለች።

ሰሜን ኮሪያ በጎረቤቷ ደቡብ ኮሪያ አማካኝነት እና በምዕራባዊያን የተቀናጀ ጥረት በፕሬዝዳንቱ ላይ ግድያ ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት አላት።

ይሄንን ስጋቷን ለማስወገድ እና ፕሬዝዳንቷን ለመጠበቅ ተመሳሳይ ቅርጽ፣ የቀለም ቅብ፣ መሰረተ ልማት እና ሌሎች ሚስጢራዊ ግንባታዎችን የያዘ ቤተ መንግስት መገንባቷን ዴይሊ ሜጠይል የሳተላይት ምስሎችን ዋቢ አድርጓል።

እነዚህ ቅንጡ ስምንት ቤተ መንግስቶች በመሃል ፒዮንግያንግ ቻንግ ክዋንግሳን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሀገሪቱ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት መገንባቱ ተገልጿል።

ቤተ መንግስቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች ለሌሎች የሀገሪቱ ዜጎች ዝግ መሆኑን ተከትሎ አካባቢው “የተከለከለ ከተማ” ወይም ፎርቢድን ሲሰቲ የሚል ስምም ተሰጥቶታል ተብሏል።

የሰሜን ኮሪያ ሀገራዊ ሚስጢራት እና ወታደራዊ እቅዶች በነዚህ ቤተመንግስቶች ውስጥ እንደሚረቀቁም ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ኪም እና አስተዳድራቸው በሰሜን ኮሪያ ዋነኛ ስጋቷ ከሀገሬው ህዝብ ወይም ፖለቲከኞች ሳይሆን ከውጭ ሀገራት የሚሰነዘር እንደሚሆን እርግጠኛ ናቸው።

ይሄንንም ስጋት ለመቀልበስ ጥቃቱ በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እና ወታደራዊ ተቋማቸው ላይ ስለሚሆን ጠላቶችን ለማሳሳት አጠቃላይ እንቅስቃሴያቸውን ገድበው በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ኪም ራሳቸውን እና ሀገራቸውን ከአደጋ ለመጠበቅ በጠዋት እና በምድር ውስጥ የተዘጋጁ መጓጓዣዎችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ኪም ከሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ በተጨማሪ በመላው የሀገሪቱ ክፍል 13 ቤተ መንግስቶች አሏቸው የተባለ ሲሆን እነዚህ ቤተመንግስቶች በወዳጆቻቸው እና ዘመዶቻቸው ይጠበቃሉም ተብሏል።

News today, Politics

ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ ነው

ጀርመን ወደ ሞስኮው ልኡክ የምትልከው ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከሩሲያ ጋር ለመምከር ነው
ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ መሆኑ ተሰምቷል።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦርን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲጠያ ጋር በተቀሰቀሰው ጦርነት የዓለም ነዳጅ ዋጋ አሻቅቧል።
40 በመቶ የነዳጅ ፍጆታቸውን ከሩሲያ የሚሸምቱት አውሮፓዊያን በዩክሬን ጉዳይ አጣብቂኝ ውስጥ ወድቀዋል።

ከአውሮፓ ሀገራት መካከል ጀርመን ደግሞ የሩሲያ ነዳጅ ጥገኛ ከሆኑ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነዳጅ እንደበፊቱ ማግኘት አልቻለችም።

በዚህም ምክንያት የፕሬዝዳንት ፑቲን ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የቀድሞቀው የጀርመን ፕሬዝዳንት በጌራልድ ሽሮደር የሚመራ ልኡክ ወደ ሞስኮ ልትልክ መሆኑን አስታውቃለች።

የወቅቱ የጀርመን ፕሬዝዳንት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ወደ ጀርመን የምትልከውን ነዳጅ መጠን እንዳትቀንስ የሚያግባባ ልኡክ ወደ ሞስኮ እንደሚልኩ ሮይተርስ ዘግቧል።

ይህን በነዳጅ ግብይት ዙሪያ ለመምከር ወደ ሞስኮ የሚያቀናውን ልኡክ የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሾልደር ሊመሩት እንደሚችሉ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

ወደ ሞስኮ የሚያቀናው የጀርመን ልኡክም በዋናነት ተልዕኮው ሩሲያ በኖርድ ስትሪም አንድ ተብሎ በሚጠራው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ነዳጅ በበቂ መጠን እንድትልክ ማግባባት እንደሚሆን ተገልጿል።

የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሽሮደር ወደ ሞስኮ አቅንተው ፕሬዝዳንት ፑቲንን ያገኙ ሲሆን የጀርመን መንግስት ከዚህ በፊት ነዳጅ ከሩሲያ የሚያገኝበት ኖርድ ስትሪም አንድን ትቶ ወደ ሁለት እንዲያተኩር አሳስበው ነበር።

ጌራልድ ሽሩደር ጀርመንን ከፈረንጆቹ 1998 ጀምሮ እስከ 2005 ድረስ በፕሬዝዳንትነት ማገልገላቸው አይዘነጋም።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 170ኛ ቀኑ ላይ ሲሆን እስካሁን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ሀገራቸውን ጥለው ወደ ጎረቡት ሀገራት መሰደዳቸውን ተመድ ከሰሞኑ ገልጿል።

News today, Politics

ጀርመን በማሊ ያሰማራችውን ሰላም አስከባሪ ጦር ልታስወጣ መሆኗን አስታወቀች

ጀርመን በባማኮ የነበራትን ሰላም ማስከበር ስራ ያቋረጠችው ማሊ ከሩሲያ ጋር መስራቷን ተከትሎ ነው
ጀርመን በማሊ ያሰማራችውን ሰላም አስከባሪ ጦር ልታስወጣ መሆኗን አስታወቀች።

የአውሮፓ ሀገራት ከዘጠኝ ዓመት በፊት በምዕራብ አፍሪካ የሽብርተኞችን ጥቃት ለመከላከል በሚል በፈረንሳይ አስተባባሪነት ለሚመራው የተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ጦራቸው አዋጥተው ነበር።

 ማሊ፣ቡርኪና ፋሶ፣ኒጀር እና ቻድ ደግሞ ከአምስት ሺህ በላይ የአውሮፓ ሀገራት ጦር የሰፈረባቸው ሀገራት ናቸው፡፡
ይሁንና በማሊ በኮለኔል አስሚ ጎይታ የሚመራው ወታደራዊ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ምዕራባውያን ሀገራት ደስተኛ ሊሆኑ አልቻሉም።

ጀርመንም ከነዚህ ሀገራት መካከል ወነኛዋ ስትሆን የሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች በማሊ መታየታቸውን ተከትሎ ወታደሮቿን ከማሊ ለማስወጣት መወሰኗን የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።

የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ክሪስቲን ላምምበርችት እንዳሉት ከምንም በላይ የወታደሮቻችን ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል ።

ጀርመን ከአንድ ወር በፊት 60 ወታደሮቿን ከማሊ ያስወጣች ሲሆን የማሊ ወታደራዊ መንግሥት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ስጋት እንደደቀነባቸውም ተገልጿል።

የማሊ ወታደራዊ መንግሥት ከዚህ በፊት የምዕራባውያን ሀገራት በሰላም ማስከበር ስም በርካታ ሰራዊት መስፈራቸውን እና የማሊን ሉዓላዊነት ሊጥሱ እንደማይገባ ገልጾ ነበር
ለተመሳሳይ ተልዕኮ በሚል በማሊ በሶስት ካምፖች ሰፍሮ የነበረው የፈረንሳይ ጦር ከወራት በፊት ለቆ መውጣቱ ይታወሳል።

የፈረንሳይ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እስካለፈው ሰኔ ወር ድረስ በምእራብ አፍሪካ አገራት ያለውን አብዛኛውን ጦር ወደ ፓሪስ የመመለስ እቅድ መያዙን ከዚህ በፊት መናገራቸውም አይዘነጋም፡፡
የአውሮፓ አገራት ሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሳህል ቀጠና የሚሰማራው ከምዕራብ አፍሪካ አገራት ወደ አውሮፓ በመሻገር የሽብር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ያለመ ነበር ተብሏል፡፡

የማሊ እና ቡርኪናፋሶ ዜጎች ከዚህ በፊት በተለያዩ ከተሞች የፈርንሳይ ጦር አገራቸውን ለቀው እንዲወጡ የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄዳቸው ይታወሳል፡፡ 

News today, social life

ደቡብ ኮሪያ ለሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ዋና አስተዳዳሪ ምህረት አደረገች


አስተዳዳሪው ፈጽመውታል በተባለው ሙስና ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል

ደቡብ ኮሪያ ለቢሊየነሩ የሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ወራሽ እና ዋና አስተዳዳሪ ሊ ጄ ያንግን ምህረት አደረገች።

የግዙፉ የዓለማችን ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ባለቤት ሊ ጄ ያንግ ከፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል ነው ምህረቱን ያገኙት።

በቀድሞዋ የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ፓርክ ጊዩን ሃይ የስልጣን ዘመን ፈጽመውታል በተባለው የሙስና ቅሌት ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።

አንዱን ዓመት በእስር ያሳለፉም ሲሆን ባለፈው ዓመት ነሐሴ ላይ ለመታረም ቃል በመግባት ከእስር ቤት ወጥተው ነበር። የተፈረደባቸው የእስር ጊዜም ከሳምንት በፊት ተጠናቋል። ሆኖም የክስ መዝገባቸው ሙሉ በሙሉ አልተዘጋም። በክሱ ያጡትን ሙሉ መብት እና ነጻነት መልሶ ለማግኘት ምህረትን ማግኘት የግድ ይላቸው ነበር።

ይህን ተከትሎም ከፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል ምህረት ተሰጥቷቸዋል። ፕሬዝዳንታዊ ምህረቱ

ከሶስት ቀናት በኋላ የሚከበረውን የሃገሪቱን የነጻነት በዓል አስመልክቶ የተሰጠ ነው።ሌሎች 1 ሺ 691 ገደማ እስረኞችም የፕሬዝዳንት ዮል ምህረት አግኝተዋል።

ሊ ጄ ኩባንያቸው የቻይናን ጨምሮ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ ኩባንያዎች ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ነው ምህረቱን ያገኙት።

በጥሩ ተወዳዳሪነቱ ለመቀጠል የሚያስችል አመራርን ሊሰጡ ይችላሉ በሚል ምህረቱን ስለማግኘታቸውም ተነግሯል።

ሃገሪቱ የገጠማትን ምጣኔ ሐብታዊ ጫና ለማቅለልና በተሻለ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱም ስለመታዘዛቸውም የሃገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

ደቡብ ኮሪያ ለሃገሪቱ ምጣኔ ሃብታዊ ግንባታ የጎላጰአበርክቶ ላላቸው የቢዝነስ ሰዎች በእንዲህ ዐይነት መንገድ ምህረት የማድረግ ልምድ እንዳላትም ተነግሯል።

News today, social life

ቤይሩት ውስጥ በመሳሪያ አስገድዶ ገንዘቡን ከባንክ የወሰደው ጀግና ተባለ

መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው ግለሰብ ጀግና ተብሏል።
የምስሉ መግለጫ,መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው ግለሰብ ጀግና ተብሏል

ከ 3 ሰአት በፊት

መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው የሊባኖስ ዜጋ በሕዝቡ ጀግና ተብሎ ተወደሰ።

ሊባኖስ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ባንኮች ደንበኞቻቸው ወጪ በሚያደርጉት ገንዘብ ላይ ገደብ ጥላለች።

ይህ ግለሰብ ግን መሳሪያ ታጥቆና ባንክ ውስጥ ነዳጅ አርከፍክፎ ለሆስፒታል ክፍያ ለመፈጸም የሚያስፈልገው ገንዘቡ እንዲሰጠው በኃይል መጠየቁን ኤኤፍፒ ዘግቧል።

በግለሰቡ እና በባንኩ መካከል ለስድስት ሰዓታት ከቆየ ፍጥጫ በኋላ ግለሰቡ የጠየቀውን ገንዘብ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ማግኘት ችሏል።

ይህ በስም ያልተጠቀው ግለሰብ ተግባርም በሕዝቡ ዘንድ አድናቆትን አስገኝቶለታል። ከባንኩ ውጪ ተሰብስበው የነበሩ ሰዎች “ጀግና ነህ” እያሉ ጠርተውታል።

የግለሰቡ ወንድም ለጋዜጠኞች ሲናገር፤ “ወንድሜ በባንክ ሂሳቡ 210ሺህ ዶላር አለው። የሆስፒታል ወጪውን ለመሸፈን 5ሺህ 500 ዶላር ፈልጎ ነበር” ብሏል።

ከባንኩ ውጪ የነበሩት የግለሰቡ ወንድም እና ባለቤት፤ “ሁሉም ሰው ሊያደርገው የሚገባው ይሄን ነው። የራሳቸው የሆነውን ማግኘት አለባቸው” ብለዋል።

ኤልቢሲ የተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ የግለሰቡ ቤተሰብ አባላት በሆስፒታል እንደሚገኙ እና ገንዘብ እጅጉን ያስፈልጋቸው እንደነበር ዘግቧል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው ጨምሮ እንደዘገበው ወደ ባንኩ በኃይል ከገባው ግለሰብ ጋር ድርድር ከተደረገ በኋላ ከቁጠባ ሂሳቡ 35ሺህ ዶላር ተሰጥቶታል።

ፖሊስ ግለሰቡን እና በእገታ ስር የቆዩ የባንክ ሠራተኞችን ከአካባቢው ይዞ የወጣ ሲሆን በግለሰቡ ላይ ክስ ይመሰረት እንደሆነ እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

እአአ 2019 ላይ ሊባኖስ የገጠማትን ምጣኔ ሃብታዊ ቀውስ ለመቋቋም ያስችለኛል ብላ ተግባራዊ ካደረገቻቸው ውሳኔዎች መካከል ሰዎች ከቁጠባ ሂሳባቸው ወጪ በሚያደርጉት የገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣል ነው።

ከዚህ በተጨማሪም ከአገር ውጪ በሚላክ የገንዘብ መጠን ላይም ገደብ ተጥሏል። ይሁን እንጂ እነዚህ ክልከላዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።

በሊባኖስ የተከሰተው ምጣሄ ሃብታዊ ቀውስ የአገሪቱ ገንዘብ ዋጋውን ከ90 በመቶ በላይ እንዲያጣ አድርጎታል።

የዋጋ ግሽበት ጣሪያ ነክቷል፤ እንደ መድሃኒት እና ስንዴ ባሉ ምርቶች ላይ እጥረት አጋጥሟል። የተባበሩት መንግሥታት ከአምስት ሊባኖሳዊያን አራቱ በድኅነት ውስጥ ይኖራሉ ይላል።

News today, Politics

የኬንያ የምርጫ አፈጻጸም በሁሉም መመዘኛዎች ጥሩ የሚባል ነው – የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን


ዶ/ር ሙላቱ ፤ አልፎ አልፎ የታዩት መስተጓጎል ለማስቀረት የምርጫ ቁሳቁስ አቅርቦትን በትክክል መፈጸሙን ማረጋገጥ እንደሚያሰፈልግ ተናግረዋል

ኬንያ ያካሄደችው ምርጫ ከዝግጅቱ ጀምሮ ጠንካራ የሚባልና የምርጫ አስተዳደር አፈጻጸሙ በሁሉም መመዘኛዎች የሚበረታታ ነው ሲል የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን ገለጸ፡፡

ባለፈው ማክሰኞ ናይሮቢ የደረሰውና በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን የኬንያ ምርጫን ቅድመ ዝግጅትና የምርጫ ሂደቱን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡
የታዛቢ ቡድኑ መሪ ዶ/ር ሙላት ተሾመ፤ የኬንያ የምርጫ እና የድንበር ጉዳዮች በሁሉም መመዘኛዎች ጥሩ ነው የሚባል የምርጫ ዝግጅት ማድረጉንና ምርጫ ማካሄዱን ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ሙላቱ፤ ኬንያ ቀደም ሲል ባካሄደቻቸው ምርጫዎች፤ ከመራጮች ማንነት ማወቅና እና የውጤት ስርጭት ጋር በተያያዘ ይነሱ ነበሩ ችግሮች የሚቀርፍ ቴክኖሎጂ በዚህ ምርጫ ላይ ተግባራዊ መደረጉ እንዲሁም የሴቶችና ወጣቶች የምርጫ አስፈታሚዎች ውክልና መሻሻሉ በምርጫው ከታዘብናቸው በጎ እርምጃዎች ውስጥ ናቸውም ብለዋል፡፡

“የምርጫ ጣቢያዎችን አደረጃጀት እና የዳስ አቀማመጥ ፣ የድምጽ መስጫ ሚስጥራዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉና በየምርጫ ጣቢያው የሚኖሩ ረጃጅም ሰልፎች የሚያስቀሩ በቂ የዳስ ቤቶች መኖራቸው ታዛቢ ቡድኑ ከተመለከታቸውና ከተሻሻሉ ወሳኝ የምርጫ ዝግጅቶች መካከል ናቸው” ሲሉም አክለዋል፡፡

ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፤ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የታየውን አይነት መስተጓጎል ለማስቀረት የምርጫ ቁሳቁስ አቅርቦትን በትክክል መፈጸሙን በማረጋገጥ ረገድ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡

ከምርጫ አስተዳደር ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማስተናገድ እና የህዝብን እምነት በማሳደግ እስከ ምርጫው ቀን ድረስ የፍትህ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደነበርም ገልጸዋል የኢጋድ ታዛቢ ቡድን መሪው ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ።

ከተመለከትናቸው ጉዳዮች አንዱ በእጅ መመዝገቢያ አጠቃቀምን በተመለከተ የፍተህ አካላት የነበራቸው ሚና ነው ያሉት ዶ/ር ሙላቱ፤ በኬንያ ዲሞክራሲን ከማጠናከር አንጻር የኬንያ የፍትህ አካላት በህዝብ ያላቸውን ተአማኒነት እንደ ተጨባጭ ስኬት እንቆጥረዋለንም ብለዋል።

በመጨረሻም የኬንያ ህዝብ ምርጫው ሰላማዊ፣ ግልጽ እና ስርዓት ባለው መንገድ ለመሳተፍ ላሳየው ትዕግስት እና ቁርጠኝነት አመስግነዋል።

የኢጋድ ታዛቢ ቡድኑ ከቀጣናዊው ተቋም ስድስት አባል ሃገራት ማለትም ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከሱዳን፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ እና ከኡጋንዳ የተውጣጡ ሰባት ዋና እና 24 ጊዜያዊ አባላት የተዋቀረ መሆኑ ይታወቃል፡፡

News today, Politics

ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ የአፍሪካ ህብረትን የሚደግፉ የአፍሪካ ታዋቂ ሰዎች ቢካተቱ እንደማይቃወም መንግስት አስታወቀ


መንግሥት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎት ለማስጀመር በቅድመ ሁኔታነት እንደማያስቀምጥ ገለጸ

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የፌደራል መንግሥት ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ የመሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማስጀመር በቅድመ ሁኔታነት እንደማያስቀምጥ ተናግረዋል።

የፌደራል መንግስት እና ህወሓት ድርድር ተስፋ እና ስጋቶች
“አገልግሎቶችን ለማስጀመር ዋናው መሰረታዊ ነገር ቅድመ ሁኔታ ሳይሆን ምክክር እና ዝርዝር ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል” ብለዋል።

ከዚህ በፊት ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሌሎች የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች አገልግሎቱን ማስጀመር የሚያስችል አስተማማኝ ሰላም እና መተማመን መፈጠር እንደሚያስፈልግ አምባሳደር መለስ ገልጸዋል።

ቃል አቀባዩ አክለውም የፌደራል መንግስት ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ በቦታ እና ጊዜ እንደማይወሰን ገልጸው በድርድሩ ላይ የአፍሪካ ህብረትን አቋም የሚደግፉ ታዋቂ አፍሪካዊያን ቢሳተፉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው አክለዋል።

መንግሥት ከህወሃት ጋር ያደርገዋል የተባለው ንግግር የሚመራው በአፍሪካ ሕብረት ብቻ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል።

ህወሓት በበኩሉ በቃል አቀባዩ በኩል በሰጠው መግለጫ፤ የአፍሪካ ሕብረት ከኦባሳንጆ ይልቅ፤ ኡሁሩ ኬንያታን ወይም ታቦ ኢንቤኬን ወይም ሌላ ሰው ከሰየመ ችግር እንደሌለበት ገልጿል።

ህወሓት በኬንያ ድርድር ለማድረግ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን በሊቀ መንበሩ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ማስታወቁ ይታወሳል።

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ በመግለጫቸው አክለውም፤ እስካሁን ባለው ጊዜ በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ 70 ሺህ የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የውጭ ሀገራት ዜጎችን የመመዝገብ ስራው እስከ ነሀሴ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ መራዘሙ ተገልጿል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ስለ “ድርድር” ምን አሉ?
ምዝገባው የተራዘመበት ምክንያት በቀነ ገደብ በተለያዩ ምክንያቶች ያልተመዘገቡ የዉጭ ሀገራት ዜገች ዕድሉን ለመስጠት እንደሆነም ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

የውጭ ሀገራት ዜጎችን መመዝገብ ያስፈለገው ምን ያህል የውጭ ሀገራት ዜጎች በኢትዮጵያ እንዳሉ ለማወቅ እና ከተመዘገቡ በኋላ ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት በማስፈለጉ ነው ተብሏል።

እስካሁን ባለው ምዝገባ ከካናዳ፣ አሜሪካ፣ ኮንጎ፣ ናይጄሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቻይና፣ ኤርትራ፣ ቡሩንዲ ፣ ጋና፣ ባንግላዲሽ፣ ሕንድ፣ ላይቤሪያ፣ ካሜሮን እና ጣሊያን የመጡ ህገወጥ ዜጎች ተመዝግበዋል።

News today, Politics

ላቲቪያ ሩሲያን በሽብርተኝነት ፈረጀች

ሌላኛዋ የሩሲያ ጎረቤት ኢስቶኒያ ድንበሯን ለሞስኮ ዝግ አድርጋለች

የላቲቪያ ፓርላማ

ላቲቪያ ሌሎች የአውቶፓ ሀገራት ሩሲያ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቃለች

የቀድሞ የሶቪየት ህብረት አንድ አካል የነበረችው እና የምስራቅ አውሮፓዋ ላቲቪያ ሩሲያን በሽብርተኝነት ፈርጃለች።

የሀገሪቱ ፓርላማ ዛሬ እንደወሰነው ከሆነ በፕሬዝዳንት ፑቲን የሚመራው የሩሲያ መንግስትን በሽብርተኝነት ፈርጇል።

ከሁለት ሚሊዮን ያልበለጠ ህዝብ ብዛት ያላት ላቲቪያ የሩሲያ እና ቤላሩስ ዜግነት ያላቸው መንገደኞች በአውሮፓ ሀገራት እንዲዘዋወሩ የሚፈቅደው የሸንገን ቪዛን እንዳይጠቀሙም እገዳ መጣሏን ሮይተርስ ዘግቧል።

ሩሲያ በዩክሬን ዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እያደረሰች ነው በሚል የምትከሰው ላቲቪያ ሁሉም የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ላይ ተመሳሳይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ጥሪ አቅርባለች።

ሌላኛዋ የቀድሞ የሶቪየት ህብረት አንድ አካል የነበረችው ኢስቶኒያ ድንበሯን ለሩሲያ ዜጎች የዘጋች ሲሆን ምክንያቷ ደግሞ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወረራ እና በዜጎቿ ላይ ስቃይ እያደረሰች ነው በሚል ነው።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ከስድስት ወራት በፊት ከሩሲያ ጋር ወደ ጦርነት የገቡት።

በዚህ ጦርነት ምክንያት የዓለም የምግብ እና ነዳጅ ዋጋ ያሻቀበ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ደግሞ ወደ ጎረቤት ሀገራት መሰደዳቸውን ተመድ ከሰሞኑ ሪፖርት ማድረጉ ይታወሳል።

News today, Politics

ቭላድሚር ፑቲን፤ ከማሊ የሽግግር መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር መወያየታቸውን ገለጹ


ምዕራባውያን፤ ሩሲያ በማሊ የምታደርገው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው ሲገልጹ ነበር
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከማሊ የሽግግር መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ።


ቭላድሚር ፑቲንና የማሊው መሪ አሲሚ ጎይታ፤ በሁለትዮሽ ትብብር ማለትም በንግድ፣ በኢኮኖሚና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው ተገልጿል።
የማሊው መሪ አሲሚ ጎይታ፤ ሩሲያ ላደረገችላቸው ድጋፍ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ማመስገናቸውም ተሰምቷል።


መሪዎቹ፤ የሩስያ የምግብ፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ምርቶች ወደ ማሊ መድረስ በሚችሉባቸው ነጥቦች ላይም መነጋገራቸው ተሰምቷል።
የሚመለከታቸው የሩሲያ እና የማሊ ተቋማት የሥራ ክፍሎች የሁለቱን ሀገራት ትብብር እንዲያጠናክሩ ስምምነት ተደርጓል ተብሏል።


መሪዎቹ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጭምር ያለው የሩሲያ እና የማሊ የውጭ ግንኙነት ትብብር እንዳስደሰታቸውም ገልጸጸዋል ተብሏል።
የማሊው የሽግግር መንግስት መሪ አሲሚ ጎይታ በማሊ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለማረጋጋትና በአሸባሪ ቡድኖች እርምጃ ለመውሰድ የታቀደውን ዕቅድ ጨምሮ፤ በማሊ ውስጥ የተከናወኑ ስራዎችን ለፕሬዝዳንት ፑቲን ገልጸውላቸዋል ተብሏል።


ቭላድሚር ፑቲን ፤ እ.ኤ.አ. በ 2023 በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሊካሄድ የታቀደው የሩሲያ አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ከመላው አፍሪካ ሀገራት ጋር ያለውን ወዳጅነት ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልጸዋል።


ምዕራባውያን ሀገራት፤ ሩሲያ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በነበረችው ማሊ ውስጥ የምታደርገው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱም እንዳሳሰባቸው ሲገለጽ ቆይቷል።
በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ምክንያት 40 ሚሊየን አፍሪካዊያን ለምግብ እጥረት እንደሚጋለጡ አሜሪካ ገለጸች


የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጂን ይቭስ ሊ ድሪያን የካቲት ወር ላይ፤ በማሊ መፈንቅለ መንግሥት ያካሄደው ወታደራዊ ኃይል “ሕገ ወጥ እና ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ነው” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎም የማሊ ወታደራዊ መሪዎች፤ በማሊ የነበሩት የፈረንሳይ አምባሳደር ጆል ሜየር በ 72 ሰዓት ውስጥ ከማሊ እንዲወጡ ማድረጋቸው ይታወሳል።

News today, Politics

ቻይና በዩክሬን ለተፈጠረው ቀውስ “ዋና ቀስቃሽ” አሜሪካ ናት አለች



ቻይና እና ሩሲያ በመካከላቸው “ገደብ የለሽ አጋርነት” እንዲኖር በመስማማት በጋራ እየሰሩ ያሉ ሀገራት ናቸው
በታይዋን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር መካረር ውስጥ የገባችው ቻይና፤ በዩክሬን ለተፈጠረው ዩክሬን ቀውስ “ዋና ቀስቃሽ” አሜሪካ ናት አለች፡፡


በሞስኮ የቻይና አምባሳደር ዣንግ ሃንሁዊ ረቡዕ ታትሞ ከወጣው የሩስያ መንግስት የዜና ወኪል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፤ ዋሽንግተን በኔቶ የመከላከያ ህብረት ተደጋጋሚ መስፋፋት በማድረግና እና ዩክሬንን ከአውሮፓ ህብረት ጋር ለማስማማት ለሚፈልጉ ሃይሎች ድጋፍ በመስጠት ሩሲያን ወደ ጥግ እየገፋቸው ነው በማለት ከሰዋል። 


አምባሳደር ዣንግ “ዋሽንግተን የዩክሬን ቀውስ ዋና አነሳሽ እና ቀስቃሽ ናት፤ አሁንም በሩሲያ ላይ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ አጠቃላይ ማዕቀብ መጣልንና ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እና ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ቀጥላበታለች” ሲሉ መናገራቸውም ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡
“የእነሱ (አሜሪካውያን) የመጨረሻ ግባቸው ሩሲያን በተራዘመ ጦርነት እና በማዕቀብ ማዳከም ነው”ም ብለዋል፡፡


የሩስያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በየካቲት ወር ወደ ቤጂንግ ተጉዘው ከቻይናው አቻቸው ዢ ጂንፒንግ ጋር ባደረጉት ምክክር በሀገራቱ መካካል “ገደብ የለሽ አጋርነት” እንዲኖር መስማማታቸው የሚታወስ ነው፡፡
የሀገራቱን ወቅታዊ ግንኙነት በተመለከተ የተጠየቁት አምባሳደር ዣንግም የሲኖ-ሩሲያ ግንኙነት “በታሪክ ውስጥ እጅግ በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል” ብለዋል፡፡


የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሀገራቸው የሩሲያን ሉዓላዊነት እና ደህንነትን እንደምትደግፍ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት በቅረቡ መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡
ቤጂንግ “በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር ፈቃደኛ ነች”ም ነበር ያሉት ዢ፡፡


የሩሲያ እና የቻይና ወዳጅነት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የትብብር ምሳሌ መሆኑን ፕሬዘዳንት ፑቲን ከወራት በፊት ከቻይናው አቻቻው ጋር በነበራቸው የበይነ መረብ ውይይት መናገራቸውም የሚታወስ ነው።
ሀገራቱ በወታደራዊ፣ በቴክኖሎጂ፣ በጠፈር ሳይንስ፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ በሌሎች ሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ ይታወቃል፡፡ 

News today, social life

የሕዳሴ ግድበ 2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት ጀመረ

ዛሬ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው
ሲጠናቀቅ ከአፍሪካ ትልቅ ግድብ እንደሚሆን የሚጠበቀው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ 2ኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።


የሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው ን ዛሬ በይፋ ጀምሯል።


ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
ባሳለፍነው ጥር 25 2014 ዓ.ም በዚህም ግድቡ ካሉት ተርባይኖች ውስጥ አንዱ የሆነው እና ዩኒት 10 የሚል መጠሪያ ያለው ተርባይን 375 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል።


ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ግድብ ለመገንባት የመረሰት ድንጋይ ካስቀመጠች አንድ አመት በኋላ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግብጽና ሱደን በግድቡ ላይ ስጋት እንዳላቸው ጥያቄ አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ፣ሱዳንና ግብጽ በግድቡ አስተዳደር ጉዳይ የሶስትዮች ንግግር እና ድርድር ከመጀሩ ቆይተዋል፤ ነገርግን እስካን ከስምምነት አልደረሱም፡፡


የኢትዮጵያ መንግስት ግድቡን እየገነባ ያለው ለልማት አላማ ብቻ መሆኑን እና በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ላይ የጎላ ተጽእኖ እንደማያደርስ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ ግብጽና ሱዳን ግን በግድቡ ዙሪያ የየራሳቸው አቋም አላቸው፡፡


በተለይም ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን የተፈረመ ስምምነትን ጭምር በመጥቀስ፤ ታሪካዊ የሆነ የውሃ ድርሻዋ ላይ ተጽእኖ እንሚያሳድር እና ግድቡ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድርባት ትገልጻለች፡፡


በ2013 ዓ.ም በአሜሪካ ዋሽንግተን ሲደረግ የነበረው የሶስትዮሽ ድርድር ከፈረስ በኋላ ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት አመቻችነት እንዲካሄድ ተስማምተዋል፡፡


ድርድርሩ ወደ አፍሪካ ህብረት የመጣው ኢትዮጵያ፤ ድርድሩ ሳይጀመር የታዛቢነት ሚና የነበራቸው አሜሪካና የአለም ባንክ ሚናቸውን ወደ አደራዳሪነትና ወደ የስምምነት ሰነድ አርቃቂነት ከፍ በማድረጋቸው እና ኢትዮጵያም ይህን አልቀበልም በማለቷ ነው።


ኢትዮጵያ የግድቡ ጉዳይ የልማት ጉዳይ ነው ብትልም ፤ግብጽና ሱዳን የግድቡን ጉዳይ የጸጥታ ጉዳይ ነው በማለት ለተመድ የጸጥታው ም/ቤት በማቅረብ ም/ቤቱ ወይይት አድርጎበት ያውቃል።

News today, social life

ሲም ካርድ ያለው ሁሉ ገንዘብ መበደር የሚችልበትን ዕድል ለመፍጠር ያቀደው ቴሌብር

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ

ከአስራ አራት ወራት በፊት ወደ አገልግሎት የገባው ቴሌብር የተሰኘው የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለፈው ሳምንት አርብ ከቁጠባ እና ብድር ጋር የተያያዙ አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት ጀምሯል።

ከቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶች በፋይናንስ ሥርዓት ያልተሸፈነውን 60 በመቶ የሚሆን የኅብተረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል።

የነዳጅ ድጎማ እና የግብር ክፍያን ጨምሮ ባለፉት 14 ወራት ገንዘብ ለመላላክ፣ የግብይትና የአገልግሎት ክፍያን ለመፈጸም እንዲሁም ከውጭ አገራት ገንዘብ ለመቀበል ሲውል የነበረው ቴሌብር አሁን ደግሞ  ‘መላ’፣ ‘እንደኪሴ’ እና ‘ሰንዱቅ’ የተሰኙ አገልግሎቶችን ይፋ አድርጓል።

ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር ደንበኞች ገንዘብ እንዲቆጥቡ፣ ሲያስፈልጋቸው እንዲበደሩ የሚረዱት አዳዲሶቹን አገልግሎቶች ለማስጀመር አስራ አራት ወራት በላይ ዘግይቷል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም እነዚህን አገልግሎቶች ለማስጀመር ከአንድ ዓመት በላይ የዘገየበትን ምክንያት ሲያስረዱ “የተሰጠን ፍቃድ እሱን አልፈቀደልንም ነበር። ስለዚህ በቴሌ ብር ሌሎቹን አገልግሎቶች እየሰጠን ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ለማግኘት ሥራዎችን ስንሰራ ቆይተናል” ብለዋል። 

ለመሆኑ አገልግሎቶቹ ምንድን ናቸው?

የቴሌብር ቁጠባና ብድር

በቴሌብር አማካኝነት በቅርቡ የተጀመሩት ሦስት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ያለዋስትና/ማስያዣ እንዲበደሩ ወይም እንዲቆጥቡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

  • ሳንዱቅ

ይህ የቴሌብር አገልግሎት ደንበኞች ገንዘብ የሚቆጥቡበት ሲሆን፣ ለተቀማጭ ገንዘብ ወለድ የሚከፈልበትን እና ከወለድ ነጻ የሆነ አመራጮችን አካቷል።

እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ፣ ወለድ የሚከፈልበት ቁጠባ በየቀኑ የሚሰላ እና ደንበኞች በቀን ያገኙትን መጠን የሚያመላክት ነው።

  • እንደ ኪሴ

የቴሌብር ደንበኞች ግብይት እየፈጸሙ ገንዘብ በሚያንሳቸው ጊዜ ቀሪውን ገንዘብ የሚያገኙት ሥርዓት ደግሞ እንደኪሴ ይሰኛል። 

እንደኪሴ ደንበኞች ለግብይት ከሚያጥራቸው ገንዘብ በተጨማሪ እንደ የኤሌክትሪክ እና ውሃ ያሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመፈጸምም ያስችላል።

ይህ አሰራር ደንበኞች ለክፍያ የጎደላቸውን እስከ 2 ሺህ ብር የሚሸፍንም ነው።  

  • መላ

ቴሌብር መላ፣ ደንበኞች የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት መንገድ ሲሆን ግለሰቦችን እና የንግድ ተቋማትን የሚያካትት ነው።

በቴሌብር መላ ግለሰቦች በወር እስከ 10 ሺህ ብር፣ የንግድ ተቋማት ደግሞ እስከ 100 ሺህ መበደር እንደሚችሉ የሚያስረዱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ግለሰቦች የተበደሩትን በቀን፣ በሳምንት እና በወር መመለስ የሚችሉበትን አሰራር ማቀፉን ጠቅሰዋል።

ለንግድ ተቋማት ደግሞ ለግለሰቦች ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ በተጨማሪ የ3፣ የ6 እና የ9 ወር የሚመልሱበትን አሰራር አካትቷል።

ቴሌብር መላ “ለሥራ ማስኬጃ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳብ ኖሯቸው ወደ ንግድ መግባት ለሚፈልጉ ሰዎችን ታሳቢ አድርጎ የቀረበ ነው። ለዚያ ነው በፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነውን ማኅበረሰብ፣ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይሆናል ብለን ያሰብነው” ሲሉም አክለዋል።   

መላ፣ እንደ ኪሴ እና ሰንዱቅ በተሰኙት የቴሌብር አገልግሎቶች በመጀመሪያ ዓመት ውስጥ በየወሩ በአማካኝ ከ3 እስከ 4 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል እና ከ19.5 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለማንቀሳቀስ ማቀዱን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል።

ከዚህም ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የብድር አገልግሎቱ ወይም ቴሌብር መላ ሲሆን 9.8 ቢሊዮን ብር ይሸፍናል።

6.4 ቢሊዮን ብር ክፍያን ለማጠናቀቅ ወይም እንደ ኪሴ ለተባለው አገልግሎት እንዲሁም 3.3 ቢሊዮን ብር ደግሞ በቁጠባ ወይም ሳንዱቅ በተሰኘው አገልግሎት የሚጠቃለል ነው።

ደጋግመው ብድር የሚወስዱ ደንበኞችን ጨምሮ በዓመት 108 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል ማታቀዱንም አስረድተዋል።

አገልግሎቶቹ በተጀመሩ በቀናት ውስጥ የዕለት ብድር ወስደው የሚመልሱ እንዲሁም የሚቆጥቡ ደንበኞች መኖራቸውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተስፋ ሰጪ እና “አስገራሚ” ሁኔታዎች መኖራቸው ገልጸዋል።

በቴሌብር መላ የሚሰጠው ብድር በሙሉ ዋስትና ወይም ማስያዣ እንደማይጠየቅበትም ጨምረው አስረድተዋል።

News today, social life

የኦሮሚያ ክልል ባህልና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኦንላይን ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ ተከፈተ

የኦሮሚያ ክልል ባህልና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኦንላይን ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ ተከፈተ
የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ያዘጋጀው “የቱሪዝምና ቴክኖሎጂ” ሳምንት ዛሬ ተከፈተ
በፎቶግራፍና በተንቀሳቃሽ ምስል የተደገፈው ኤግዚቢሽኑ “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ መታየት ጀምሯል

የኦሮሚያ ክልል ባህል እና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኢንተርኔት (ኦንላይን) ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ በይፋ ተከፍቷል።

በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን አዘጋጅነት የተሰናዳው ይህ የኢንተርኔት (ኦንላይን) ኤግዚቢሽን “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” መተግበሪያ ላይ የሚገኝ መሆኑ ተነግሯል።

በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው ወንጪ ሐይቅ ምርጥ የቱሪዝም መንደር ሆኖ በተመድ ተመረጠ
የኦንላይን ኤግዚቢሽኑ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረው “የቱሪዝምና ቴክኖሎጂ” ሳምንት ላይ በይፋ የተከፈተ ሲሆን፤ ኤግዚቢሽኑንም የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አስጀምረውታል።

በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ነጋ ዱፌራ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ 21 የተለያዩ የክልሉን ባህል እና እሴት የሚያሳዩ ይዘቶች መጫናቸውን አስታውቀዋል።
“በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ የተጫኑት 21 ይዘቶች በክልሉ ባህላዊ መገልገያዎች፣ ምግቦች እና አለባበሶች ላይ ያተኮሩ መሆኑን አቶ ነጋ ዱፌራ አስታውቀዋል።

ሁሉም ይዘቶች “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” መተግበሪያ ላይ መቀመጡን እና ማንኛውም ሰው መተግበሪያውን በማውረድ፤ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ አሊያም ቪዚት ኦሮሚያ ሲል እነዚህ በምስል እና በጽሁፍ የተደገፉ ይዘቶች ማይት ይችላል ብለዋል።

“ጥምቀት በውኃ ላይ” በደምበል (ዝዋይ) ኃይቅ ላይ የተከበረው የከተራና ጥምቀት በዓል
እነዚህ ይዘቶች በቋሚነት እንደ ዲጂታል ሙዚየም በመተግበሪያው ላይ የሚቀመጡ መሆኑን እና በየትኛውም የዓለም ክፍል ያለ ሰው በማንኛውም ሰዓት ከፍቶ ሊመለከት የሚችለው እንደሆነ አቶ ነጋ ለአል ዐይን ገልጸዋል።

በተያያዘ የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ያዘጋጀው የቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ ሳምንት በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ ተከፍቷል።

News today, Politics

የቡድን ሰባት አባል ሀገራት፤ ሩሲያ ዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን ለዩክሬን ልትሰጥ ይገባል አሉ

የቡድን ሰባት አባል ሀገራት፤ ሩሲያ ዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን ለዩክሬን ልትሰጥ ይገባል አሉ
ሩሲያ፤ በዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያ ዙሪያ የጸጥታው ም/ቤት እንዲሰበሰብ ጠየቀች
ሞስኮ፤ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጣትም ጠይቃለች

ሩሲያ፤ የዛፖሪዥያ ኒውክለር ጣቢያን፤ ለዩክሬን አሳልፋ ልትሰጥ እንደሚገባ የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ጠየቁ።

የሀገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ በዛፖሪዥያ ያለውን የኒውክለር ጣቢያ መያዝና መቆጣጠር ያለባት ዩክሬን ናት ብለዋል።

ሩሲያ፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ “ዛፖሪዥያ ኒውክሌር ጣቢያ” ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰች
ሚኒስትሮቹ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ፤ የኒውክለር መሳሪያዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ለሚያደርገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

ምንም እንኳን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሞስኮ በዛፖሮዝሂ ያለውን የኒውክለር ጣቢያ እንዳትቆጣጠርና ለዩክሬን አሳልፋ እንዲሰጥ ቢጠይቁም ሩሲያም ሌላ ቅሬታ አሰምታለች።

ሞስኮ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት፤ በኒውክለር ጣቢያው ዙሪያ ስብሰባ እንዲያደርግ ጠርታለች።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሩሲያ ቋሚ መልዕከተኛ ጽ/ቤት፤ የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት አባል ሀገራት በዛፖሪዥያ ኒውክለር ጣቢያ ዙሪያ ስብሰባ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

በዚህ ስብሰባ ላይም ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እና የተባበሩት መምግስታት የኒውክለር ተቆጣጣሪ ማብራሪያ እንዲሰጧት ሞስኮ ጠይቃለች።

ዩክሬን በኒውክለር ጣቢያው ላይ የድሮን ጥቃት እያደረገች ነው ስትል ሞስኮ ብትከስም፤ ዩክሬን ግን ይህንን አስተባብላለች። ዩክሬን በበኩሏ ሩሲያ የኒውክለር ጣቢውን በመጠቀም ትቃት እየሰነዘረች ነው ስትል ትከሳለች።

ሩሲያ በግዝፈቱ ሁለተኛ የሆነውን የዩክሬን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች
የዩክሬን ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት፤ሩሲያ የኒውክለር ጣቢያውን ለወታደራዊ ምሽግ እየተጠቀመች ነው ሲል ወቅሷል። የሩሲያ ከባድ መሳሪያዎች እና ወታደራዊ ሰዎች በዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያ መኖራቸውንም ዩክሬን ገልጻለች።

የቡድን አባት አባል ሀገራት የዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን በሚመለከት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳሉ ገልጸዋል።

News today, Politics

ቻይና፤ አሜሪካ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገለጸች

ቤጅንግ፤ ከዋሸንግተን ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ማቋረጧን መግለጿ ይታወሳል

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት በአሜሪካ እና ቻይና መካከል ከፍተኛ ውጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል

ቻይና፤ አሜሪካ ከዚህ በኋላ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ፡፡

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ ዋሸንግተን በቻይና ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያነጣጠረ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች እንደማይታገስ ገልጿል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢን ዛሬ በመግለጫቸው አሜሪካ፤ ቻይናን ለመያዝ ታይዋንን ከመጠቀም እንድትቆጠብ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ 

የቻይና ባለስልጣናት አሜሪካ ፤ ታይዋንን በመጠቀም፣ የቤጅንግ ብሔራዊ ጥቅም እየጎዳች መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለጹ ናቸው፡፡ ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢንም ይህንኑ ሃሳብ በዛሬ ድጋሚ አንስተውታል፡፡ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፤ የናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ጸብ አጫሪ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ በኋላ ግን ለጸብ የሚያነሳሳ ድርጊት ከዋሸንግተን ከመጣ ቻይና አጸፋውን ለመመለስ መዘጋጀቷን ተናግረዋል፡፡ 

ቻይና ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ወታደራዊ ትብብር ማቋረጧን ተከትሎ ዋሸንግተን ድርጊቱን አውግዛ ነበር፡፡ ቤጅንግ ግን ሁሉንም እርምጃዎች የወሰደችው አሜሪካ ጸብ አጫሪ ድርጊትን ከፈጸመች በኋላ በመሆኑ የወሰደቻቸው እርምጃዎች ሚዛዊና ትክክል መሆናቸውን ገልጻለች፡፡

ቻይና እና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብርን ጨምሮ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያም ንግግርና ውይይት የነበራት ቢሆንም በፔሎሲ ጉብኝት ምክንያት ሁሉንም ላለማድረግ ውሳኔ ማሳለፏን ማሳወቋ ይታወሳል፡፡ 

ከዚህ ባለፈም የፕሬዝዳንት ዢ ሺን ፒንግ አስተዳደር፤ ሀገሪቱ ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን የማጓጓዝ፣ አደገኛ ዕጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን ማቋረጡን ገልጿል፡፡

ቻይናና አሜሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ የበላይነትን ለማስፈን ከሚደረግ ሽኩቻ ባለፈ በንግድና ኢኮኖሚ ላይ ያተኮረ እሰጥ አገባ የነበራቸው ቢሆንም ታይዋን ግን የሀገራቱን ግብ ግብ የበለጠ እንዲካረር አድርጋዋለች ተብሏል፡፡ 

News today, Politics

ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” አሉ

ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” አሉ
“በዙሪያየ ያሉ ሰዎች ሁሉ ኢላማ ሲደረጉ ዝም ከማለት “ምንም አማራጭ አል

የኒውዮርክ አቃቤ ህግ ዶናልድ ትራምፕ የሚያስተዳድሩትን ተቋም የግብር እና ብድር እፎይታ ለማግኘት በሚል ” የሚያሳስት እና ያልተገባ የንብረት ግምገማ” በማድረግ አጭበርብረዋል ሲል መክሰሱ የሚታወቅ ነው፡፡

በዚህም መሰረት ኒውዮርክ ወደ ሚገኘው ፍርድ ቤት የቀረቡት ዶናልድ ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት መሰረት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” ማለታቸው ተሰምቷል፡፡

ትራምፕ ጉዳዩን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ “በአሜሪካ ህገ መንግስት ለእያንዳንዱ ዜጋ በተሰጡት መብቶች መሰረት፤ ጥያቄዎች ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆንኩም”ብለዋል።

ትራምፕ መልስ ላለመስጠታቸው “ቤተሰብ፣ ድርጅት እና በዙሪያየ ያሉ ሰዎች ሁሉ የፖለቲካ ፍለጎት ባላቸው ጠበቆች፣ በዐቃብያነ-ህግ የሚደገፉ የሀሰት ዜና የሚያሰራጩ ሚድያዎች ዒላማ ሲሆኑ፣ ምንም አማራጭ አልነበረኝም” የሚል ምክንያት ማቅረባቸውም ነው ፍራንስ-24 የዘገበው፡፡

በፍሎሪዳ የሚገኘውን የአሜሪካ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ) ከቀናት በፊት የዶናልድ ትራምፕ መኖሪያ ቤትመበርበሩ የሚታወስ ነው፡

ፍተሻው ዶናልድ ትራምፕ ምናልባትም በደጋፊዎቻቸው ከተፈጸመው የካፒቶል ሂል ጥቃት ጋር በተያያዘ ከቤተ መንግስት ያሸሹት ሚስጥራዊ ሰነድ ይኖር ይሆን በሚል የተካሄደ ነው መሆኑን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል፡፡

ትራምፕ ኒውዮርክ በሚገኘው ህንጻቸው ላይ ሳሉ ነው መኖሪያቸው የተፈተሸው።

“ማር-ኤ-ላጎ የሚገኘው ቅንጡ መኖሪያ ተከቦ ነው የሚገኘው፤ በብዙ የኤፍ.ቢ.አይ ፖሊሶች ተወርሮም ይገኛል” ሲሉም ነበር ዶናልድ ትራምፕ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘ ማህበራዊ ሚዲያቸው በወቅቱ ያስታወቁት።

ድርጊቱ በቀጣዩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ (2024) እንዳይወዳደሩ ለማድረግ በማሰብ የተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

K^አወዛጋቢው ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2024 በሚካሄደው ምርጫ ለመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ፍንጭ መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡

News today, Politics

የቻይና ጦር በታይዋን ዙሪያ ሲያካሂድ የነበረውን ወታደራዊ ተልዕኮ ማጠናቀቁን አስታወቀ


“ለውጊያ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ለመሆን” ያለመው ልምምድ እንደሚቀጥል የቻይና ጦር አስታውቋል

ቻይና በታይዋን ዙሪያ ስታካሂዳቸው የነበሩትን የተለያዩ ወታደራዊ ተልዕኮዎችን ማጠናቀቋን አስታወቀች።

የቻይና ጦር፤ “አሁን ያለው ሁኔታ በታይዋን የባህር ዙሪያ ያለውን ለውጥ በቅርበት መከታተል ይፈልጋል” ሲል አሳስቧል።

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን አቋረጠች
የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው
ጦሩ “ለውጊያ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ለመሆን” ወታደራዊ ልምምድ ማድረጉን እንደሚቀጥል መጠቆሙም ቻይና ደይሊ ግሎባል ታይምስ ዘግቧል።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በታይዋን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ፤ በሩቅ ምስራቅ የነገሰው ውጥረት እንደቀጠለ ነው።

አፈ ጉባኤዋ ባሳለፍነው ሳምንት ታይዋንን የጎበኙ ሲሆን ድርጊቱ ቻይናን እንዳስቆጣ የዓለም ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል።

ይሄንን ተከትሎም ቻይና በታይዋን ባህር ዙሪያ ለቀናት የሚዘለቅ ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆኗን አሳውቃ ነበር።

ቻይና ባሳለፍነው ሳምንት ልምምድ ላይ ዶንግ ፋንግ የተሰኘው የቻይና የረጅም እና አጭር ርቀት ባልስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ታይዋን ባህር ተኩሳ እንደነበርም ሚታወስ ነው።

በታይዋን ስድስት አቅጣጫዎች ምንም አይነት የባህር እና አየር ላይ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ቻይና አስቀድማ ማስጠንቀቋ ይታወሳል።

በቻይና ድርጊት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የገባቸው ታይዋን በበኩሏ ቻይና “ለወረራ እየተዘጋጀች” መሆኑን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በመናገር ላይ ናት፡፡

የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆሴፍ ዉ ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መሆኗን መግለጻቸው ኤኤፍፒ ማክሰኞ እለት ዘግቧል፡፡

ጆሴፍ ው የቻይናን የሶሞኑ ወታደራዊ እንቅስቀሴ በማስመልከት በታይፔ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ቤጂንግ በእስያ-ፓሲፊክ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመቀየር እየሰራች ነው ብለዋል።

ቻይና፤ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተች
የቤጂንግ የጦርነት ጨዋታ “የታይዋንን መብት የሚጻረር” እና በታይዋን ዙሪያ ያለውን ውሃ እና ሰፊውን የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነው” ብለዋል ጆሴፍ ው።

ቤጂንግ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ” ስታስጠነቅቅ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡

እናም በምስራቅ ታይዋን የባህር አከባቢ የተፈጠረው ውጥረት ወዳልተፈለገ የጦር መማዘዝ እንዳያመራ ተሰግቷል።

News today, Politics

ኢዜማ የመንግስት ተሿሚ አባላቱ በያዙት ኃላፊነት እንዲቀጥሉ መወሰኑን አስታወቀ

ዶ/ር ኦንጋይ ኦዳን የደቡብ ክልል የኢዜማ የመሪ ክንፍ ተጠሪ ሆነው እንዲሰሩም ወስኗል
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመንግስት የተሾሙ አመራርና አባላቱ በተረከቡት ስልጣን ይቀጥሉ ሲል ወሰነ።
 ፓርቲው በፌስቡከ ገጹ ባወጣው መግለጫ ወሳኔው በአርባ ምንጭ ከተማ ለሁለት ቀናት ተሰብስበው በነበሩት የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እና የፓርቲው ሊቀመንበር ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የተሰጠ ነው።


ከስብሰባቸው ጎን ለጎን ከፌደራል እስከ ወረዳ ባሉ የመንግስት መዋቅሮች ተካተው ሕዝብን በማገልገል ላይ ከሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ጋር በሥራ አፈጻጸም እና በአደረጃጀት ጉዳዮች ላይ የተወያዩት ከፍተኛ አመራሮቹ ጉዳዩን የተመለከተ ውሳኔ አሳልፈዋል።
በውሳኔው መሰረትም መንግስት አብሮ ለመሥራት ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ በመዋቅሩ ተካተው ሥልጣን ተረክበው ሕዝብን በማገልገል ላይ የሚገኙ የኢዜማ አባላት አርአያ መሆን የሚችሉ ስለሆኑ በኃላፊነታቸው እንዲጥሉ መደረጉን መግለጫው ጠቅሷል፡፡


በመልካም ሥነምግባር የታነጹ፣ ሌብነትን የሚጸየፉ፣ በሥራ ትጋታቸው እና በአፈጻጸም ብቃታቸው የተመሠከረላቸው እና አርአያ መሆናቸውን እንዲቀጥሉም ማሳሰብያ ተሰጥቷል እንደ ፓርቲው ገለጻ።
የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በስብሰባቸው በደቡብ ክልል በመንግስት መዋቅር ውስጥ ስለተካተቱ አባላት አደረጃጀት እና ተጠሪነት የመከሩም ሲሆን ኦንጋይ ኦዳ (ዶ/ር) በደቡብ ክልል የኢዜማ የመሪ ክንፍ ተጠሪ ሆነው እንዲሰሩ መወሰናቸው ተገልጿል፡፡
ኢዜማ በመጀመርያ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ከመንግስት የቀረበውን የአብረን እንስራ ጥሪ ተቀብሎ መንግስት ለከፍተኛ አመራሮቹ ጭምር የሰጠውን ሹመት መቀበሉ ይታወሳል።


በዚህም የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በፌዴራል መንግስት ካቢኔ ውስጥ ተካተው በትምህርት ሚኒስትርነት ሲሾሙ፤ የፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ካቢኔ ተካተው የአስተዳደሩ የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሆነው ተሾመው በማገልገል ላይ ናቸው።
በደቡብ ክልል የመንግስት መዋቅር ውስጥ የተካተቱ የድርጅቱ አባላትም አሉ።


ሆኖም ይህ ኢዜማ የበለጠ እንዲዳከምና “የመንግስት ተለጣፊ” ሆኖ እንዲታይ አድርጎታል የሚሉ ወቀሳዎች ከራሱ ከፓርቲው ሰዎች ጭምር እንዲሰነዘሩ ምክንያት ሆኗል።
ጉዳዩ፤ የፓርቲው አቋምና አካሄድ ጭምር በፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ሳይቀር የልዩነት ምንጭ ሆኖ ፓርቲውን አመራር ለመቀየር እስከሚያስችል ምርጫ እስከማካሄድ አድርሶት እንደነበር ይታወሳል።


ይህን ተከትሎ የፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንን መሪ እና ምክትል መሪ አድርጎ መምረጡ የሚታወስ ነው፡፡

News today, social life

የዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ


በዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ። ከተሞቹ ምርጥ የተባሉት ለኑሮ ባላቸው ምቹነት መሠረት ነው።

አውሮፓዊቷ አገር የኦስትሪያ ዋና ከተማ ቪዬና ቀዳሚዋ የዓለማችን ምቹ ከተማ ተብላለች።

በተከታይነት ደግሞ የዴንማርክ ኮፐን ሃገን እና የስዊትዘርላንድ ዙሪክ ከተሞች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

የካናዳ ከተማ የሆኑት ካልጋሪ እና ቫንኩቨር ደግሞ በአራተኝነት በቀጣይ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ሲሆን፤ የስዊትዘላንዷ ጄኔቫ፣ የጀርመኗ ፍራንክፈርት፣ የካናዳዋ ቶሮንቶ፣ የኔዘርላንድስ አምስተርዳም፣ የጃፓን ኦሳካ እና የአውስትራሊያዋ ሜልበርን ቀዳሚዎቹን አስር ደረጃዎች ለመያዝ በቅተዋል።

ይህንን ደረጃ ይፋ ያደረገው ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት እንደሚለው ከሆነ ከተሞች ለኑሮ ያላቸው ምቹነት ቢጨምርም ዓለም አቀፉ አማካይ ግን አሁንም ዝቅተኛ ነው ብሏል።

ለኑሮ ምቹነት ከታዩት ጉዳዮች አንዱ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ተጽዕኖ መሆኑን ተጠቁሟል።

የዩክሬን ጦርነት ደግሞ ኪዬቭ ከጥናቱ ውጪ እንድትሆን ሲያስገድዳት፣ በሩሲያዎቹ ሞስኮ እና ሴንት ፒተርስበርግ ውጤት ላይም ተጽዕኖ አሳድሯል።

በዚሁ ጦርነት ምክንያት የምሥራቅ አውሮፓ ከተሞች ደረጃም ዝቅ ብሏል።

የምዕራብ አውሮፓ እና የካናዳ ከተሞች ደረጃውን በመምራት ቀዳሚ ሆነዋል።

ደማስቆ፣ ትሪፖሊ እና ሌጎስ ደግሞ ከማኅበራዊ አለመረጋጋት፣ ሽብር እና ግጭት ጋር ተተያይዞ በደረጃው መጨረሻ ላይ ለመገኘት ተገደዋል።

በዘንድሮው ጥናት 33 አዳዲስ ከተሞች ተካተዋል።

በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ከተሞች ብዙ መሻሻል አላሳዩም ተብሏል።

የሶሪያዋ ደማስቆ በደረጃው የመጨረሻው ስፍራን ይዛለች።

ቴህራን፣ ዱዋላ፣ ሃራሬ፣ ዳካ፣ ፖርት ሞርስባይ፣ ካራቺ፣ አልጀርስ፣ ትሪፖሊ፣ ሌጎስ እና ደማስቆ ናቸው የመጨረሻዎቹን አስር ደረጃዎች የያዙት።

ለኑሮ ባላቸው ምቹነት መሻሻል ያሳዩ ከተሞችም ታይተተዋል።

እነዚህ ከተሞች በአብዛኛው በምዕራብ አውሮፓ የሚገኙ የጀርመን፣ የዩናይትድ ኪንግደም እና የፈረንሳይ ከተሞች ናቸው።

ፍራንክፈርት ካለፈው ዓመት 32 ደረጃዎችን በማሻሻል ሰባተኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ በቅታለች።

ሃምቡርግ ደግሞ ከ31ኛ ወደ 16ኛ ተመንድጋለች።

የኒውዚላንድ እና የአውስታራሊያ ከተሞች ደግሞ ደረጃው ላይ ማሽቆልቆል አስመዝግበዋል።

በዚህም ዌሊንግተን እና ኦክላንድ 46 እና 33 ደረጃዎችን ለመውረድ ተገደዋል።

ድርጅቱ ይህን ደረጃ ለማውጣት የከተሞቹን መረጋጋት፣ የጤና ዘርፍ፣ ባህል እና አካባቢ፣ ትምህርት እና መሠረተ ልማት ከግምት ያስገባል።

ይህንን ደረጃ ይፋ ያደረገው ተቋም የዩክሬን ጦርነት እና ኮቪድ በሚቀጥለው ዓመት በሚኖረው የከተሞች ለኑሮ ምቹነት ደረጃ ላይ ተጽዕኖ ይኖራቸዋል ብለዋል።

ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት ላለፉት 70 ዓመታት ኢኮኖሚያዊ ትንታኔዎች በመስጠት የሚታወቀው ሲሆን የዘ ኢኮኖሚስት ጋዜጣ እህት ኩባንያ ነው።

News today, Technology

የባህር ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪው አዲሱ የቻይና ድሮን


ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ድሮኑ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል
ድሮኑ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘር ይችላል

ቻይና በአይነቱ ለየት ያለ ባህር ስር እንደ ሰርጓጀ አየር ላይ ደግሞ ድሮን የሚሆን መሳሪያ እየሰራች መሆኑ ተሰምቷል።

የቻይና ተመራማሪዎች እየሰሩት ነው የተባለው አዲሱ ስተሊዝ ድሮን ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ሲሆን፤ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል።

ሚሳዔል አስወንጫፊው የቻይና CH-7 የውጊያ ድሮን
በዓለም ላይ ካሉ “በጣም አደገኛ” የጦር መርከቦች አንዱ የሆነው የቻይናው “ለሃሳ” መርከብ
የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አሁን ላይ ለናሙና የሚሆን አዲሱን ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪ ድሮን በመስራት ሙከራ እያደረጉበት መሆኑም ታውቋል።

ሳውዝ ቻይና ሞኒተሪንግ ፖስት ጋዜጣ ባወጣው መረጃ፤ ድሮኑ አራት ተሸከርካሪ ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሁለቱ ከፊት ሁለቱ ደግሞ ከኋላ የተገጠሙ ናቸው።

ደሮኑ በባህር ስር በሚሆንበት ጊዜ ሁለቱ ክንፎቹን በማጠፍ የሚቀዝፍ ሲሆን፤ ይህም በጣም ዘመናዊ የሆነ የሰርጓጅ መርከብ ቅርጽ እንዲላበስ የሚያደርገው ነው።
ከባህር በመውጣት አየር ላይ በሚንሳፈፍበት ወቅት ደግሞ ክንፎቹን የሚዘረጋ ሲሆን፤ በሰዓት እስከ 120 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር የሚችል መሆኑንም የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታውቀዋል።

ድሮኑ በባህር ስር እንዲሁም በአየር ላይ ፈጣን እና የረጅም ርቀት ተልእኮዎችን በቀላሉ መከወን የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር አንግ ሂሶንግ ገልፀዋል።

“J-20” ዘመናዊዎቹ የቻይና ተዋጊ ጄቶች
አዲሱ ድሮን ከራዳር እይታ ውጪ እንዲሆን ታስቦ መሰራቱን የሚያነሱት የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ትክክለኛ ጥቅሙ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር መቻሉ እንደሆነም ተናግረዋል።

ድሮኑ መቼ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የቻይና ጦር ይታጠቀዋል በሚል ላይ እንዲሁም ድሮኑ ምን አይነት መሳሪያዎችን መታጠቅ ይችላል በሚለው ላይ የወጣ መረጃ የለም።

News today, Politics

አሜሪካ የአልሻባብ ተዋጊዎችን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት መፈጸሟ ተነገረ

የአልሻባብ ታጣቂዎች

ከ 5 ሰአት በፊት

የአሜሪካ ጦር በሶማሊያ ማዕከላዊ ሒራን ክልል በአልሻባብ ተዋጊዎች ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሙን የሶማሊያ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘገበ።

መገናኛ ብዙኃኑ እንዳለው ጥቃቱ የተፈፀመው የሶማሊያ መንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ተከትሎ ነው።

የአየር ድብደባ ስለመፈፀሙ ግን የአሜሪካ እና አፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ አስተያየት አልሰጠም።  

የአሜሪካ ባለሥልጣናት በሰኔ እና በሐምሌ ወር በተፈፀሙ ሁለት የአየር ድብደባዎች ሰባት የጂሃዲስት ቡድኑ ተዋጊዎች መገደላቸውን መናገራቸው ይታወሳል።

ከቅርብ ወራት ወዲህ አልሻባብ በመንግሥት ኢላማዎች ላይ የሚፈጽመው ጥቃት የጨመረ ሲሆን በቅርቡም ድንበር በመሻገር በኢትዮጵያ ደንገተኛ ጥቃት ፈጽሟል።

አሜሪካ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት በአል ሻባብ ቡድን ላይ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን በሰው አልባ አውሮፕላኖች ስትፈጽም ቆይታለች።

በተለይም የቡድኑን አመራሮች ኢላማ በማድረግ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች ከፍተኛ መሪዎቹን ጨምሮ በርካታ የቡድኑ አባላትን መግደሏ መዘገቡ ይታወሳል።

ሐምሌ 13/2014 ዓ.ም እስላማዊ ታጣቂዎቹ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንባቸው የድንበር ከተሞች የከፈቱትን ጥቃት ተከትሎ ከባድ ውጊያ ተካሂዶ ነበር።

ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለው አልሻባብ ጥቃቱን የፈፀመው ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ግዛት በኩል በሚገኙት ዬድ እና አቶ ላይ ነው።

ከኢትዮጵያ ጋር በሚዋሰኑት የሶማሊያ ድንበር አካባቢዎች ነበሩ በተባሉ የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት ጋር በተካሄደው በዚህ ከባድ ውጊያም በሁለቱም ወገን ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናት ተናግረዋል።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ ዑመርም እስላማዊ ታጣቂ ቡድኑ የከፈተውን ጥቃት የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች መክተው መመለሳቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ድንበር ተሻግረው ጥቃት ከሰነዘሩት የአልሻባብ አባላት መካከል ከ800 በላይ የሚሆኑ መገደላቸውንና በርካቶች መማረካቸውን ገልጿል።

ቀደም ሲልም የኢትዮጵያ ሠራዊት በቡድኑ ላይ ወሰዳቸው ወታደራዊ እርምጃዎች በአሜሪካ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ ግለሰብን ጨምሮ ሦስት ከፍተኛ የአልሻባብ ከፍተኛ አመራሮችን መግደሉን አሳውቋል።

በተያያዘ ዜና የአልሻባብ ታጣቂ ቡድን የቀድሞ መሪ የሆነው ሙክታር ሮቦው አዲስ በተቋቋመው ካቢኔ ውስጥ የሶማሊያ የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር በመሆን ባለፈው ሳምንት ተሹመዋል።

የእርሳቸው ሹመትም የአል ሸባብን ጽንፈኛ ርዕዮተ ዓለም ለመመከት የተደረገ ሙከራ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል።

News today, Politics

የዩክሬን ጦርነት “ክሬምያን ነጻ በማውጣት” መጠናቀቅ አለበት -ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ


ዘሌንስኪ ‘‘በክሬምያ የተጀመረው ጦርነት፤ ክሬምያን ነጻ በማውጣት መጠናቀቅ አለበት” ብለዋል
የዩክሬን አካል የነበረቸው ክሬምያ እንደፈረንጆቹ 2014 በተካሄደው ህዝበ ውሳኔን ወደ ሩሲያ መቀላቀሏ የሚታውስ ነው

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘሌንስኪ፡የዩክሬን ጦርነት ክሬምያን ነጻ በማውጣት መጠናቀቅ አለበት አሉ፡፡

ዘለንስኪ በሰጡት መግለጫ ‘‘ክሬምያ ዩክሬናዊት ናት፤ አንተዋትም’’ ሲሉም ተደምጠዋል፡፡

የዩክሬን አካል የነበረቸው ክሬምያ፤ እንደፈረንጆቹ 2014 የተካሄደውና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተቀባይነት ያላገኘው ህዝበ ውሳኔን ተከትሎ ወደ ሩሲያ መቀላቀሏ የሚታውስ ነው፡፡

በርካታ ዩክሬናውያን አሁን ላይ ከሩሲያ ጋር እየተደረገ ያለው ጦርነት የተጀመረው ያኔ ክሬምያ ወደ ሩሲያ ስትሄድ ነበር ብለውም ያምናሉ፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በትናንትናው እለት በክሬምያ ሳኪ ተብሎ በሚታወቅ የሩሲያ ወታደራዊ ማዕከል ከባድ ፍንዳታ እንዳጋጠመ እየተነገረ ነው፡፡

ሩሲያ፤ ባይረጋገጥም ጥቃቱን የፈጸመችው ዩክሬን ከሆነች መዘዙ ከባደ ነው ስትል ማስጠንቅቋ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ስለ ፍንዳታው ከመናገር የተቆጠቡት ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ ግን፤ አሁንም ክሬምያ ተመልሳ የዩክሬን ግዛት መሆኗ የማይቀር እንደሆነ በመዛት ላይ ናቸው፡፡

‘‘ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት የተጀመረው በክሬምያ ነው፤ መጠናቀቅ ያለበትም በክሬምያ ነው….ነጻ ሆና’’ም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፡፡

ክሬምያን ወደ ዩክሬን የመመለስ ፍላጎት የሚያመላክተው የፕሬዝዳንቱ ንግግር፤ ከዚህ በፊት ይሉት ከነበረ የተለየ ይዘት ያለው እንደመሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡

ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ በወርሃ የካቲት 21 ቀን፤2022 በሰጡት መግለጫ ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸው ግዛቶች ለቃ ከወጣች ዩክሬን ሰላም እንደምትቀበልና “ክሬምያ ቅድመ ሁኔታ እንደማትሆን” መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

News today, Politics

ሩሲያ ‘ካያም’ የተሰኘችውን የኢራን ሳተላይት ወደ ህዋ አመጠቀች


ሳተላይቷ የመጠቀችው ከደቡብ ከዛኪስታን ነው

አሜሪካ፤ ኢራን በሳተላይቷ በእስራኤል እና በሌላው አለም ወታደራዊ ኢላማ ለመለየት ያስችላታል የሚል ፍርሃት አላት

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ጠቅላይ መሪ የሆኑት አያቶላ አሊ ካሜኔ በጋራ ለመስራት ቃል ከገቡ ከሶስት ሳምንታት በኋላ ሩሲያ የኢራንን ሳተላይት በትናንትናው እለት ከደቡብ ካዛኪስታን ወደ ምህዋር አምጥቃለች፡፡

ሩሲያ ሳተላይቷን ያመጠቀችው ሁለቱ መሪዎች ምእራባውያንን በጋራ ለመመከት ከተስማሙ በኋላ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ኢራን የእስራኤልን የስለላ ኔትወርክ መያዟን አስታወቀች
በ11ኛው ክፍለ ዘመን በፋርስ ገጣሚ እና ፈላስፋ ኦማር ካያም ስም የተሰየመችው የሪምት ካያም ሴንሲንግ ሳተላይት በሩሲያዋ ሶዩዝ ሮኬት ነው የተመነጨፈችው፡፡ በካዛኪስታንከሚትገኘው የሩሲያ ባይኮኑር ኮስሞድሮም የተወነጨፈችው ሳተላይቷ በተሳካ ሁኔታ ወደ ኦርቢት መግባቷን የሩሲያ ስፔስ ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡

የኢራን ስፔስ ኤጀንሲ የመጀመሪያ የሆነው ቴሌሜታሪ ዳታ ከሳተላይት መቀበሉን የአራን ዜና አገልግሎት(ኢርና) ዘግቧል፡፡

ቴህራን፤ ሩሲያ ሳተላይቷን ከዩክሬን ጋር ለምታደርገው ጦርነት የሚጠቅም መረጃ ለመብሰብ ትጠቀምባታለች የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጋለች፡፡ ኢራን ሳተላይቷን ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ እንደምትቆጣጠር ገልጻለች፡፡

የአሜሪካውን የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣን ጠቅሶ እንደዘገበው የአሜሪካ ባለስልጣናት በሩሲያ እና በኢራን መካከል ያለው የስፔስ ትብብር አሳስቧታል፤ ምክንያቱም ሳተላይቷ ሩሲያ በዩክሬን የምታደርገውን ጦርነት መርዳት ብቻ ሳይሆን በእስራኤል እና በሌላው አለም ወታደራዊ ኢላማ ለመለየት ታስችላለች የሚል ፍርሃት አላት፡፡

News today, Technology

በስህተት የጣለውን ቢትኮይን በ13 ሚሊዮን ዶላር እያፈላለገ ያለው ግለሰብ


ከ10 ዓመታት በፊት ነው። ጄምስ ሃዌልስ ያስቀመጠውን ቢትኮይን ረስቶ የኮምፒውተሩን የመረጃ ቋት (ሃርድ ድራይቭ) አውጥቶ ጣለው።

ጄምስ ተዝናግቶ የወረወረው ቢትኮይን ዘንድሮ ባለው ገበያ 184 ሚሊዮን ዶላር ሊያወጣ ይችላል።

ይህ የከነከነው ጄምስ ከዓመታት በፊት የጣለውን ቢትኮይን ሚሊዮን ዶላር ከፍሎ ሊያስቆፍረው አስቧል።

የሰውዬው ‘ሃርድ ድራይቭ’ ኒውፖርት በተሰኘችው የዩናይትድ ኪንግደም ከተማ ቆሻሻ መጣያ ሥፍራ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል።

ጄምስ ይህ ውድ ቁስ ከተገኘለት ከቢትኮይኑ 10 በመቶውን ቆንጥሮ ከተማዋን የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቃል ገብቷል።

ነገር ግን የከተማዋ ምክር ቤት የቆሻሻ መጣያውን መቆፈር ሥነ-ምኅዳራዊ (ኢኮሎጂካል) ቀውስ ያስከትላል እያለ ነው።

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (አይቲ) ባለሙያው ጄምስ ከዘጠኝ ዓመት በፊት በፈረንጆቹ 2013 ነበር፤ 8 ሺህ ቢትኮይን ያቀፈውን ሃርድ ድራይቭ ጠርጎ የጣለው።

ወቅቱም ቢትኮይን የተሰኘው ዲጂታል የመገበያያ ገንዘብ ብቅ ብቅ ማለት የጀመረበት ነበር።

ቢትኮይን ገበያው ላይ የሚታወቀው በሚዋዥው ዋጋው ነው።

ለምሳሌ የጄምስ ቢትኮይን ዋጋ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት [2021] 256 ሚሊዮን ዶላር ደርሶለት ነበር።

ነገር ግን ከዘንድሮው ዓመት መባቻ ጀምሮ ዋጋው አሽቆልቁሏል።

ጄምስ በተደጋጋሚ ለኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ቆሻሻ ማከማቻው ይቆፈርልኝ ብሎ ቢያመልክትም ጥያቄው ሰሚ አጥቷል።

ይህ ያታከተው ግለሰብ አሁን ሃርድ ድራይቩ ከተገኘ 10 በመቶ ገቢውን ለከተማዋ የክሪፕቶከረንሲ ማስፋፊያ ለመስጠት ወስኗል።

ነገር ግን የጄምስን መዳፍ የምታክል ቁስ ለማግኘት ሲል ከተማ አስተዳደሩ በርካታ ወጪ አውጥቶ ለዓመታት የተከማቸውን ቆሻሻ ይቆፍር እንደሁ አልታወቀም።

ከተማ አስተዳደሩ የቆሻሻ ማከማቻውን ማመስ አካባቢውን ሊበክለው ይችላል የሚል ስጋት አለው።
ጄምስ ደግሞ “እኔ ማከማቻውን የማስቆፈር አቅም እንዲሁም አደጋ ሳያደርስ የሚያስስ ባለሙያ አለኝ” ይላል።

“እርግጥ ነው ቆሻሻ ማከማቻ መቆፈር ራሱን የቻለ ትልቅ ሥራ ነው” ይላል ጄምስ።

“ነገር ግን ማስቆፈሪያ ወጪውን እችላለሁ። የሰው-ሠራሽ ልኅቀት [አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ] ባለሙያ አስመጥተናል። ሃርድ ድራይቩን ነቅሎ የሚያወጣ ቴክኖሎጂ አለ።”

ግለሰቡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከበቢያዊ አደጋን የሚመረምር ቡድን ማዘጋጀቱን ይገልጣል።

“በሁሉም ዘርፍ የተካኑ ልምድ ያላቸው ሙያተኞች ይዣለሁ። ከተፈቀደላቸው ይህንን ሥራ በብቃት መከውን የሚችሉ ናቸው።”

ነገር ግን ሃርድ ድራቩን ማግኘት ብቸኛው ሥራ አይደለም። ይህ የመረጃ ማከማቻ ቁስ ቢገኝ እንኳ ለመሥራቱ ማስተማመኛ የለም።

ይህ በርካታ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን ያቀፈው ቁስ ቢገኝ ጄምስ ሚሊየነር ይሆናል። ነገር ግን የቢትኮይንን የገበያ ዋጋ መገመት ከባድ ነው።

ቢሆንም የ37 ዓመቱ ግለሰብ የበርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ባለቤት ሊሆን ይችላል።

ጄምስ ገንዘቡ ተቆፍሮ ይውጣለት እንጂ፣ ያደገባትን ከተማ የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቆርጦ ተነስቷል።

“ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ሥራ ለመሥራት የሚያስችል ዕቅድ አስቀምጫለሁ” ይላል።

“አንደኛው ሥራ የቆሻሻ ማከማቻውን ማዘመን ነው። ከተቻለ በአካባቢው በነፋስ ኃይል የሚሠራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ እንገነባለን።”

የኒውፖርት ማኅበረሰብ የሚጠቀምበት የክሪፕቶከረንሲ ገበያ ለመዘርጋት ነው የጄምስ ዓላማ።

ለእያንዳንዱ የኒውፖርት ነዋሪ 61 ዶላር ዋጋ ያለው ቢትኮይን ለመስጠትም ቃል ገብቷል። በተከማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ደግሞ ክሪፕቶ ላይ የተመሠረቱ ፌርማታዎች ለመግንባትም አስቧል።

የኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ግን በተደጋጋሚ የሰውዬውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።

የከተማዋ ቃል አቀባይ “ቆሻሻ ማከማቻን በተለመከተ የተቀመጠ ሕግ አለን። ይህን ሕግ መከተል አለብን” ብለዋል።

“አንደኛው ጉዳይ ይህ የቆሻሻ ማከማቻ ከተቆፈረ በአካባቢው ማኅበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ሥነ ምኅዳራዊ አደጋ ነው። የጄምስ ዕቅድ ደግሞ ይህን አደጋ የሚያስከትል ነው። ይህን ልንቀበለው አንችልም። በሕጉ መሠረት እንዲያውም ከግምት ውስጥ ልናስገባው የምንችለው ሐሳብ አይደለም።”

News today, Technology

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን መገጣጠም ሊጀምር መሆኑን ግሪን ቴክ አፍሪካ ገለፀ


እስካሁን 320 በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ሀገር ቤት ገብተዋል
ግሪን ቴክ አፍሪካ በወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን መገጣጠም እጀምራለሁ ብሏል

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ በሁለት ወይም ሶስት ወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም እንደሚጀምር አስታወቀ።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚይ ኢንጅነር ቅደም ተስፋዬ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኩባንያው የአሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈም በሀገር ቤት ለማምረት ማቀዱን አስታቀዋል።

በዚህም መሰረት ድርጅቱ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች የመኪና መገጣጠም ስራን ይጀምራል ነው ያሉት።
አሁን ለይ ከ320 በላይ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት መቻሉን የገለጹት ኢ/ር ቅደም፤ ተሸከርካሪዎቹ 100 በ 100 በባትሪ የሚሰሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።

የተሸከርካሪዎቹ ዋጋ በነዳጅ ከሚሰሩት መኪኖች ጋር ተቀራራቢና እኩል እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የጉምሩክ፣ ሱርታክስታና ተጨማሪ እሴት ታክስ ባይኖር ግን ዋጋቸው ከዚህ ይቀንስ እንደነበር ገልጸዋል።

ተሸከርካሪዎቹን ከውጭ ሀገራት እያሰገቡ ከመሸጥ ባለፈም በሀገር ውስጥ ለመገጣጠም መታቀዱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።ይህም በሶስት ወይም በሁለት ወራት ውስጥ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

የመገጣጠሙ ሂደት በዚህ ሲቀጥል፤ በአምስት አሊያም በስድስት ዓመታት ውስጥ 60 በመቶ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት እንደሚቻል ነው የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው።

መኪኖቹን በሀገር ቤት ከመገጣጠም የሚያስችል የሰለጠነ የሰው ኃይል በቻይና እየሰለጠ እንደሆነ የገለጹት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፤ ተጠቃሚዎች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ብለዋል።
መኪኖቹን በቤት ውስጥ ቻርጅ ማድረግ እደሚቻልና ከ 4 እስከ 6 ሰዓታት ውስጥ ተሽከርካሪዎቹ 80 በመቶ ቻርጅ እንደሚያደርጉም ነው የተገለጸው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በፍጥነት ቻርጅ እንዲያደርጉ ለማድረግ 40 ቦታዎች ተዘጋጅተዋል ተብሏል፡፡

አንዱ ፈጣን ቻርጀር ማድረጊያ በአንድ ጊዜ ሁለት መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ የሚችል ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ 80 መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ ይቻላል ተብሏል።

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ የአህጉሩ ሕዝብ የኢነርጂ ሃይል ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በምስራቅ፣ በምእራብ እና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት ውስጥ እየሰራ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለአል ዐይን አማርኛ አስታውቀዋል።

ኩባንያው፤ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ አፍሪካ ሀገራት በማስገባት ስራውን መጀመሩን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው፤ ከዚህ ባለፈም ድርጅታቸው፤ በታዳሽ ሃይል እና በአዳዲስ የኢነርጂ ምንጮች ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

News today, Politics

ተመድ በእስራኤል-ጋዛ ጉዳይ አስቸኳይ ስበሰባ አደረገ


ድርጅቱ ተኩስ አቁሙ እምብዛም አስተማማኝ እንዳይደለ አስታውቋል
የማይከበር ከሆነ የከፋ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችልም ነው ያስጠነቀቀው

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በእስራኤል እና በእስላማዊ ጂሃድ ታጣቂዎች መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱን ተከትሎ አስቸኳይ ስበሰባ አደረገ፡፡

ስብሰባው በድርጅቱ የጸጥታው ምክር ቤት የተደረገ ነው፡፡

የድርጅቱ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ተኩስ አቁም ቢደረግም እምብዛም አስተማማኝ አለመሆኑን በመጠቆም ሁለቱ አካላት ዳግም ወደ ግጭት የሚገቡ ከሆነ ጉዳቱ ሊከፋ ይችላል ሲሉ በስብሰባው ተናግረዋል፡፡

ሁለቱም ወገኖች አጸፋዊ ምላሽ ሊሰጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ ሁኔታዎችን የበለጠ ሊያከፋ እንደሚችልም ነው ልዩ መልዕክተኛው የተናገሩት፡፡

መፍትሔዎችን ለመፈለግ የሚደረጉ ጥረቶችን ሊያወሳስብ ይችላልም ብለዋል፡፡

እስራኤል ካሳለፍነው አርብ ጀምሮ በነበሩ ተከታታይ ሶስት ቀናት ዒላማ ባደረገቻቸው የታጣቂዎቹ ይዞታዎች ከባድ ድብደባዎችን ፈጽማለች፡፡ ታጣቂዎቹም በመልሱ 1100 ገደማ ሮኬቶችን አስወንጭፈዋል፡፡ በዚህም 15 ህጻናትን ጨምሮ 44 ሰዎች ሲገደሉ 360 ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡

ሆኖም ከተተኳሾቹ 20 በመቶ ያህሉ በተለያዩ የጋዛ ሰርጥ አካባቢዎች መውደቃቸውን ነው ልዩ መልዕክተኛው ቶር ውንስላንድ በድንገት ለተሰበሰው ምክር ቤት የተናገሩት፡፡

እስራኤል ከየትኛውም አቅጣጫ የሚወነጨፉ ሮኬቶችንና ሌሎች ተተኳሾችን ለማምከን የሚያስችል አይረን ዱምን መሰል ዘመናዊ መሳሪያዎችን መታጠቋን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡

የእስራኤልን የደህንነት ስጋት ያነሱት ልዩ መልዕክተኛው ታጣቂዎቹ ተመጣጣኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ ይልቅ ሮኬቶችን ማስወንጨፋቸውን ኮንነዋል፡፡

በተመድ የእስራኤል አምባሳደር ጊላድ ኤርዳን ታጣቂዎቹ በንጹሃን መካከል በመሸሸግ ወደ ንጹህ እስራኤላውያን መተኮሳቸውን በማውገዝ ሙሉ ኃላፊነቱን ሊወስዱ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካ ተወካይ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድም ቢሆኑ እስራኤል ዜጎቿን ከአሸባሪዎች ጥቃት የመጠበቅ መብት አላት ብለዋል፡፡

ሆኖም በድርጅቱ የፍልስጤም አምባሳደር ሪያድ መንሱር የእስራኤል ድርጊት ወረራ ነው በሚል ጥቃቱን ተቃውመዋል፡፡ ስንት ንጹሃን እስኪገደሉ ነው በሚልም ተመድ በቃ እንዲል ጠይቀዋል፡፡

ለሶስት ተከታታይ ቀናት የዘለቀው ውጊያ በግብጽ አግባቢነት ለጊዜው እንዲቆም ስምምነት ላይ መደረሱ ይተቃወሳል፡፡

News today, Politics

ታይዋን፤ ቻይና “የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር እየሰራች ነው” አለች


ታይዋን ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መሆኗን ገለጸች
ጆ ባይደን አሜሪካ ታይዋንን ከቻይና ወረራ ለመጠበቅ “ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል” መግለጻቸው ይታወሳል

በአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት የተበሳጨችው ቤጂንግ፤ የጦር አውሮፕላኖቿንና መርከቦቿ በታይዋን ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆናቸው የእየተነገረ ነው፡፡

በዚህ ስጋት የገባቸው የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆሴፍ ዉ ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መግለጻቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡
ጆሴፍ ዉ፡ የቻይናን የሶሞኑ ወታደራዊ እንቅስቀሴ በማስመልከት በታይፔ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ፤ቤጂንግ በእስያ-ፓሲፊክ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመቀየር እየሰራች ነውም ብለዋል፡፡

“የቻይና እውነተኛ አላማ በታይዋን የባህር ዳርቻ እና በጠቅላላው አካባቢ ያለውን ሁኔታ መለወጥ ነው”ሲሉም ተናግረዋል፡፡

“ቻይና ልምምዱን እና ወታደራዊ መጫወቻ ደብተሩን ለታይዋን ወረራ ለማዘጋጀት ተጠቅማበታለች” በማለትም ቤጂንግን የከሰሱት ከሰዋል ጆሴፍ ዉ፤በተጨማሪም የታይዋን የህዝብን ሞራል ለማዳከም መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ልምምዶችን እና የሚሳዔል ጥቃቶችን እንዲሁም የሳይበር ጥቃትን፣ የሀሰት መረጃ ዘመቻን እና ኢኮኖሚን የማዳከም ስራ እየሰራች ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

የዉ ጋዜጣዊ መግለጫ የመጣው የታይዋን ጦር በደሴቲቱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የራሱን ወታደራዊ ልምምድ ማድረግ ከጀመረ በኋላ መሆኑ ነው።

ጆሴፍ ዉ፡ የቤጂንግ የጦርነት ጨዋታ “የታይዋንን መብት የሚጻረር” እና በታይዋን ዙሪያ ያለውን ውሃ እና ሰፊውን የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነው”ም ብለውታል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጆሴፍ ዉ፤ የምዕራባውያን አጋሮችን ቻይናን መቃወማቸውንም አመስግነዋል።

“የተቀረው ዓለም አቋም ዴሞክራሲ ለአምባገነንነት ዛቻ እንደማይንበረከክ ለዓለም ግልጽ መልእክት ያስተላለፈ ነው”ም ብለዋል፡፡

ቤጂንግ፤ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ” ስታስጠነቅቅ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡

እናም በምስራቅ ታይዋን አከባቢ የተፈጸረው ውጥረት ወዳልተፈለገ የጦር መማዘዝ እንዳያመራ ተሰግቷል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ፤ ታይዋንን ከቻይና ወረራ ለመጠበቅ ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል ፕሬዝዳንት ጆ-ባይደን ከወራት በፊት በጃፓን ጉብኝታቸው መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡

ጆ-ባይደን “ቻይና ታይዋንን በተመለከተ ኃይል የምትጠቀም ከሆነ እኛም መጠቀማችን አይቀርም” ነበር ያሉት፡፡

News today, Technology

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን
በሱፐርሶኒክ ፍጥነት የሚበረው አውሮፕላኑ በሰዓት ከ1 ሺህ 200 ኪ.ሜ በላይ ይጓዛል
እስከ 16 ሺህ ኪ.ግ ቦምቦችንና ክሩዝ ሚሳዔሎችን ታጥቆ ያለምንም ችግር መብረር ይችላል

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በገጠመችው ጦርነት ከተጠቀመችባቸው የጦር አውሮፕላኖች ውስጥ “Tu-160” አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

በጣም ግዙፍ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጦር አውሮፕላን በሶቪየት ህብረት ወቅት ማለትም በፈረንጆቹ 1981 ወደ አገልግሎት የገባ ሲሆን፤ በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት እስካሁን እያገለገል ይገኛል።

በሰዓት ከ6 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚምዘገዘገው ሃይፐርሶኒክ ሚሳዔል
ሩሲያ አውሮፕላኑ ላይ በፈረንጆቹ 2008 አዳዲስ ማሻሻዎንብመ በማድረግ ይፋ ያደረገች ሲሆን፤ Tu-160R በሚል ስያሜ የአየር ኃይሏን ዳግም አስታጥቃለች።
ለመሆኑ ግዙፉ Tu-160 የጦር አውሮፕላንን ምን የተለየ ያደርገዋል?

የአወሮፕላ ቁመት 54.1 ሜትር ሲሆን፤ ክንፉ ርዝማኔም 35.6 ሜትር ይረዝማል፤ ክንፎቹ ላይ አራት ኩዜንትዞቭ NK-321 ቱርቦፋን ሞተሮች ተገጥመውለታል።

አውሮፕላኑ ከመሬት እስከ 52ሺ ገጫማ ወደላይበመነሳት መብረር ይችላል ተብሏል።

ሱፐርሶኒክ ፍጥነት እንዳለው የተነገረው Tu-160 የጦር አውሮፕላን በሰዓት 1,236 ኪሎ ሜትሮች መብረር የሚችል መሆኑም ይነገርለተል።

“አደገኛው” የሩሲያ “ዛላ ኬ.ዋይ.ቢ” ድሮን
Tu-160 የጦር አውሮፕላን 16,330 ኪ.ግ የሚመዝኑ ቦምቦችን ተሸክሞ በሱፐርሶኒክ ፍጥነት መብረር የሚችል ነው ተብሏል።

አውሮፕላኑ ከቦምቦች በተጨማሪም Kh-101 እና Kh-102 የሚባሉ ክሩዝ ሚሳኤሎችን መታጠቅ የሚችል እና ኢላማውን በአግባ የሚመታ መሆኑም ተነግሯል።

News today, Politics

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፤ “አፍሪካ ምን መምረጥ እንዳለባት አሜሪካ አታዝም” አሉ


“በአፍሪካ ለታየው ዋጋ ንረት ምክንያት ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ነው” የሚለውን ክስ ብሊንከን ውድቅ አደረጉ
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ አፍሪካ ምን መምረጥ እንዳለባት አሜሪካ “አታዝም” አሉ።

ሩሲያን ከዓለም ለመነጠል ያለመ በተባለው የአፍሪካ ጉብኝት ላይ የሚገኙት አንቶኒ ብሊንከን፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ ሀገራት ይበጃል ያሉትን አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ አቅርበዋል።

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ
ብሊንከን ባቀረቡት ጽሁፍ፡ የአፍሪካ ሀገራት ለገዛ እድገታቸው የሚታገሉ ሳይሆን የሌሎች መሳሪያ እንደሆኑ ተደረገው ሲታዩ መቆየታቸውም አንስተዋል።

“የአፍሪካ ሀገራት ከህዝቦቻቸው ፍላጎት ውጭ በሆነ መልኩ፤ የዓለም ኃያላን ፉከክር በሚያደርጉበት ጉዳይ ላይ አቋም እንዲይዙ ሲነገራቸው ነበር” ነው ያሉት ብሊንከን።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ብሊንከን፤ ሀገራቸው አሜሪካ መሰል ጫና እንደማትደገፍ የገለጹ ሲሆን፤ አሜሪካ አሁንም ቢሆን በአፍሪካ ቅድሚያ ሰጥታ የምትሰራባቸው ጉዳዮች ቢኖሩ “ዴሞክራሲ፣ ሰላም እና ጸጥታ” ናቸው ብለዋል።

አንቶኒ ብሊንከን፤ በዛሬው እለት ምርጫ በማካሄድ ላይ ያለችውን ኬንያ አንስተው ሲናገሩም፤ “አፍሪካ ችግሮች ያሉባት፤ አሜሪካ ደግሞ መፍትሄ ሰጪናት” ብለው እንደማያስቡ ፤ ነገር ግን በጋራ በመሆን ችግሮችን ለመፍታት ለሚደረጉ ጥረቶች አሜሪካ እውቅና እንደምትሰጥ አስረድተዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በሊቢያ፣ ማሊ እና ማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ስለሚገኙና የ“ዋግነር” ቡድን በመባል ስለሚታወቁ የሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች ያላቸው አስተያየትም ሰንዝረዋል።

ብሊንከን፡ በክረምሊን የሚደገፈው የ“ዋግነር” ቡድን፤ ” በአለመረጋጋት ውስጥ ሃብትን የሚዝቅና በደል የሚፈጽም ቡድን ነው” ሲሉ ከሰውታል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ ላለው የዋጋ ንረት ዋና ምክንያት ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ነው ለሚለው ክስም ምልሽ ሰጥተዋል።

ብሊንከን በሰጡት ምልሽ “ፕሬዝዳንት ፑቲን ወረራ ከመጀመራቸው በፊትም ቢሆን ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ 193 ሚሊዮን ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸው ነበር” የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል።

ያም ሆኖ የዓለም ባንክ ከነበረው 193 ሚሊዮን በተጨማሪ በጦርነቱ ምክንያት ለ40 ሚልዮን ህዝብ ሰብዓዊ እርዳታ ያሰፈልጋል ባለው መሰረት፤ አሜሪካ የምግብ እጥረት ያጋጠማቸው ሀገራት ስትደግፍ፤ ሩሲያ ግን ችግር በመፍጠር ላይ መሆኗ ተናግረዋል፡፡

በደቡብ አፍሪካ ቆይታ ያደረጉት ብሊንከን ቀጣይ ጉዞዋቸውን ወደ ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ መሆኑ ተገልጿዋል።

ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics

ዩክሬን በሩሲያ ጦር ላይ ድል እየተቀዳጀች መሆኑን ገለጸች


የዩክሬን ጦር በሩሲያ ጦር ተይዞ የነበረ አንድ ከተማ በመልሶ ማጥቃት መረከቡን አስታውቋል
የሩሲያ ጦር በካርኪቭ በኩል ኢዙም የሚባለውን አካባቢ ለመቆጣጠር ቢሞክርም ተምትቶ መመለሱ ተገልጿል

ዩክሬን ወደ ግዛቷ በገባው የሩሲያ ጦር ላይ ድል እየተቀዳጀች መሆኑን ገለጸች፡፡

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ከሩሲያ ጋር ወደለየለት ጦርነት የገባችው።

ሩሲያ ከኔቶ ለዩክሬን የተለገሱ 45 ሺህ ቶን ጥይት አወደምኩ አለች
168ኛ ቀኑ ላይ በሚገኘው በዚህ ጦርነት ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን ክፍል በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር ውሏል።

ዩክሬን ከምዕራባዊያን በሚደረግላት የጦር መሳሪያ እና የገንዘብ ድጋፍ ሩሲያን በመመከት ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።

የዩክሬን ጦር በሩሲያ ጦር እጅ ስር ባለችው ካርኪቭ አቅራቢያ ባደረገው የመልሶ ማጥቃት ዶቭሄንክ የተባለች ከተማን ዳግም መቆጣጠሩን ሮይተርስ ዘግቧል።

በአካባቢው ያለችው ኢዙም እና አካባቢውን ለመቆጣጠር በማጥቃት ላይ የነበረው የሩሲያ ጦር በዩክሬን ጦር በደረሰበት ማጥቃት ማፈግፈጉም ተጠቅሷል።

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ አማካሪ የሆኑት ኦለክሲ አርሴቶቪች እንዳሉት ካርኪቭ ከተማን ከሩሲያ ለመንጠቅ ከፍተኛ ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የአሜሪካ መከላከያ ፖሊሲ ምክትል ጸሀፊ በበኩላቸው በዩክሬን ምድር እስከ 80 ሺህ የሩሲያ ወታደሮች እንደተገደሉባት እና እንደቆሰሉባት አክለዋል።

የሩሲያ መከላከያ በበኩሉ በደበባዊ ዩክሬን የሚገኘው ዛፖሪዝህዚያ የኑክሌር ማዕከልን ባሳለፍነው መጋቢት ላይ የተቆጣጠረችው ቢሆንም የዩክሬን ጦር ይሄንን ማዕከል ሀላፊነት ከሩሲያ ለመረከብ ሀላፊነት በጎደለው መንገድ ተኩስ መክፈቷን አስታውቃለች።

ዩክሬን በሩሲያ ላይ ድልን እንድትቀዳጅ ከአሜሪካ እና ምዕራባውያን ሀገራት የጦር መሳሪያ እየተደረገላት ይገኛል።

አሜሪካ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ለዩክሬን እንደምትሰጥ አስታውቃለች።

በአጠቃላይ አሜሪካ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 18 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያቆች ለዩክሬን መስጠቷን ዘገባው አክሏል።

የሩሲያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ኔድሜዴቭ በበኩላቸው ሩሲያ በዩክሬን ያሰበችውን እቅድ ማሳካቷ አይቀርም ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

News today, Politics

የአሜሪካ ፖሊስ የዶናልድ ትራምፕን መኖሪያ ቤትን ፈተሸ


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ቤት በኤፍ ቢ አይ ተፈተሸ

የአሜሪካ ፖሊስ የቀድሞውን የሃገሪቱን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መኖሪያ ቤትን በርብረዋል፡፡

በፍሎሪዳ የሚገኘውን የትራምፕን መኖሪያ የፈተሸው የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ) መሆኑን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡

ፍተሻው ዶናልድ ትራምፕ ምናልባትም በደጋፊዎቻቸው ከተፈጸመው የካፒቶል ሂል ጥቃት ጋር በተያያዘ ከቤተ መንግስት ያሸሹት ሚስጥራዊ ሰነድ ይኖር ይሆን በሚል የተካሄደ ነው መሆኑን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል፡፡

ትራምፕ ኒውዮርክ በሚገኘው ህንጻቸው ላይ ሳሉ ነው መኖሪያቸው የተፈተሸው።

“ማር-ኤ-ላጎ የሚገኘው ቅንጡ መኖሪያ ተከቦ ነው የሚገኘው፤ በብዙ የኤፍ.ቢ.አይ ፖሊሶች ተወርሮም ይገኛል” ሲሉ ዶናልድ ትራምፕ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘ ማህበራዊ ሚዲያቸው አስታውቀዋል።

በቀጣዩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ (2024) እንዳይወዳደሩ ለማድረግ በማሰብ የተደረገ መሆኑንም ነው የገለጹት።

ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2024 ለሚካሄደው ምርጫ ለመወዳደር ያላቸውን ፍላጎት በይፋ ባይገልጹም፣ ባለፉት ጥዊት ወራት ለመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ትራምፕ ከካፒቶል ሂሉ ጥቃት እንዲሁም የተሸነፉበትን የምርጫ 2020ን ውጤት በኃይል ለመቀየር ሞክረዋል፤ ሌሎች ሚስጥራዊ ሰነዶችንም አሽሽተዋል ከመባሉ ጋር በተያያዘ በምርመራ ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

News today, Politics

ብሊንከን ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለመመከት ያለመ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለማሳደግ የምታደርገውን የዲፕሎማሲ ጥረት ለመመከት ያለመ ጉብኝት ጀመሩ።

ብሊንከን በዚህ ጉብኝታቸው ወደ ሦስት የአፍሪካ አገራት እንደሚጓዙ ይጠበቃል።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከደቡብ አፍሪካ በኋላ ወደ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ቀጥሎ ደግሞ ወደ ሩዋንዳ ይሄዳሉ ተብሏል።

የብሊንከን የመጀመሪያ መዳረሻ የሆነችው ደቡብ አፍሪካ በዩክሬኑ ጦርነት ሞስኮን ለማውገዝ የምዕራባውያንን ጥሪዎች ሳትቀበል ገለልተኛ ሆና ቆይታለች።

ከሁለት ሳምንታት በፊት የሩሲያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ስድስት ቀናትን በፈጀ ጉብኝት አዲስ አበባን ጨምሮ ወደ ተለያዩ አገራት ተጉዘው ነበር።

ላቭሮቭ የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በግብጽ ጀምረው ቀጥሎም ወደ ኮንጎ ብራዛቪል፣ ዩጋንዳ እና ኢትዮጵያ ተጉዘው ከባለስልጣናት ጋር ተገናኝተዋል።

በቆይታቸውም በተለይም በዩክሬኑ ጦርነት ምክንያት በአፍሪካ በተከሰተው የስንዴ አቅርቦት እጥረት ላይ ትኩረት ሰጥተው ንግግሮችን አካሂደው ለምግብ እጥረቱ ተጠያቂዎቹ ምዕራባዊያን አገራት ናቸው ሲሉም ተደምጠዋል።

“ምዕራባውያን አገራት የበላይነታቸውን በሌሎች ላይ ለመጫን እየሞከሩ ነው” ሲሉም ከሰዋል። እንዲሁም ሞስኮ የዓለምን የምግብ ቀውስ አስከትላለች የሚለውን ወቀሳ አጣጥለውታል።

News today, Politics

ቻይና፤ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተችየቻይና መከላከያ ሚኒስቴር “በታይዋን የባህር ወሽመጥ ላይ ላለው ውጥረት አሜሪካ ኃላፊነቱን ትወስዳልች” ብሏል


የፔንታጎን፣ የስቴት ዲፓርትመንት እና የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የቻይና እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ሲሉ በማውገዝ ላይ ናቸው

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት እጅጉን ያስቆጣት ቻይና፣ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተች፡፡

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዉ ኪያን በኦን ላይን ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፡ “በታይዋን የባህር ወሽመጥ ላይ ያለውን ውጥረት በትንኮሳ እንዲፈጠር ያደረገቸው አሜሪካ ናት፣ ስለዚህም አሜሪካ ለድረጊቷ ኃላፊነት በመውሰድ የሚከተሉ አስከፊ መዘዝ መሸከም ይኖርባታል” ብለዋል፡፡

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን አቋረጠች
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቻይና ወታደራዊ መርከቦች፣ አውሮፕላኖች እና ሰው አልባ አውሮፕላኖች በደሴቲቱ እና በባህር ሃይሏ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን የታይዋን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

“ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት” አውሮፕላኖችን እና መርከቦችን መላካቸውንም ጭምር አስታውቋል ታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር፡፡

በፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት የተቆጣችው ቻይና ለአሜሪካ ምላሽ ነው በሚል አስካሁን በታይፔ ላይ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን የመተኮስ ሙከራዎች ከማድረግ በተጨማሪ ከአሜሪካ ጋር የነበሯት የመከላከያ ፖሊሲ ማስተባበሪያን እና የባህር ኃይል-ወታደራዊ ምክክርን ያካተቱ መደበኛ ንግግሮችን መሰረዟ ባሳለፍነው አርብ ይፋ አድርጋለች፡፡

የፔንታጎን፣ የስቴት ዲፓርትመንት እና የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የቻይና እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ነው ሲሉ አውግዘውታል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፤ቻይና የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማቆም አደንዛዥ እጾች፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ በስምንት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ የወሰደችው አጸፋዊ እርምጃ፤ አሜሪካን ብቻ ሳይሆን ዓለምን የሚቀጣ ነው ሲሉ ከቀናት በፊት መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

ብሊንከን “የአየር ንብረት ትብብርን ማገድ አሜሪካን ብቻ ሳይሆን ዓለምን በተለይም በማደግ ላይ ያሉትን ሀገራት የሚቀጣ ነው።በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው ልዩነት ምክንያት ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ትብብሮችን እንደ መያዣ መጠቀም የለብንም” ሲሉ መደመጣቸውም ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ቻይና በታይዋን ዙሪያ እየፈጸመች ያለውን አደገኛና በቀጠናው አለመረጋጋት ሊፈጥር የሚችል ድርጊትን በተመለከተ ዋሽንግተን ከአጋሮቿ እየሰማች ነው ያሉት ብሊንከን ፤ “ ዋሽንግተን ጉዳዩን በምታስተናግድበት መንገድ እያስተናገደች ጸንታ ትቀጥላለች”ም ብለዋል ብሊንከን፡፡

News today, Politics

ሩሲያ፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ “ዛፖሪዥያ ኒውክሌር ጣቢያ” ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰች

ሩሲያ፤ ዩክሬን የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ ላይ የከፈተችው ተኩስ “ከባድ መዘዝ” የሚያስከትል ነው ስትል አስጠንቅቃለች

ዩክሬን በበኩሏ ክሬምሊንን በዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ላይ “የኒውክሌር ሽብር” ፈጽማለች ስትል ከሳለች

የሩሲያ ቤተ መንግስት ክሬምሊን፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ የዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰ።

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን የሚገኘው ዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ በአውሮፓ ትልቁና በዓለም ላይ ካሉት 10 ትላልቅ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያዎች መካከል አንዱ ነው።

እናም ሩሲያ ፤ የዩክሬን ጦር ግዙፉን የኒውክሌር ጣቢያ ለማውደም ተኩስ ከፍተዋል በማለት ኪቭን ከሳለች።

ሩሲያ፤ ዩክሬን ግዙፉን አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ጣቢያ ማውደሟ “አሰቃቂ መዘዝ” ይዞ ሊመጣ እንደሚችል ልታውቅ ይገባል ስትል አስጠንቅቃለች።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “የዩክሬን ታጣቂ ሃይሎች የኒውክሌር ጣቢያን ማውደም ከዩክሬን ባለፈ ለአውሮፓ ምድር እጅግ አደገኛ ሊሆን የሚችል ተግባር ነው”ሲሉ ተደምጠዋል።

የዩክሬን አጋሮች “እንዲህ ዓይነቱ የዩክሬን እርምጃ እንዳይቀጥል ተጽእኖ ያድርጉ” ሲሉም ጠይቀዋል ቃል አቀባዩ።

ሩሲያ ይህን ትበል እንጅ ዩክሬን በተቃራኒው፤ የሩሲያ ኃይሎች በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ኩባንያው ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል የሚል ክስ በማቅረብ ላይ ናት።

ጥቃቱን ተከትሎ መግለጫ የሰጡት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ “የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጠንካራ ምላሽ” እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርበዋል።

ፕሬዝዳንቱ፤ በሞስኮ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦች ለመጣል በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ከአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ጋር መነጋገራቸውንም አስታውቋል ።

ክሬምሊንን “የኒውክሌር ሽብር” ፈጽማለች ሲሉም ከሷል ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ።

News today, Politics

የዩክሬኗ ዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ


የዛፖሮዝሂ ክልል በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን ትገኛለች
እስካሁን በዛፖሮዝሂ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ የዘገቡት የሩሲያ ሚዲያዎች ናቸው

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን የምትገኘው የዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ሕዘበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ግዛቲቱ ወደ ሩሲያ ለመጠቃለል ሕዝበ ውሳኔ እንደምታደርግ አስተዳዳሪው መግለጻቸውን የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

የሩሲያ ጦር የተቆጣጠራቸው የዩክሬን ግዛቶች ወደ ሩሲያ ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ሊያካሂዱ ነው
የግዛቲቷ አስተዳዳሪ ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል የሚስችል ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ ያስታወቁት ዛሬ ነው፡፡

የግዛቲቱ ደቡባዊ ክፍል አሁን ላይ በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን ሙሉ ግዛቱ ግዛቱ ሕዝበ ውሳኔ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሕዝበ ውሳኔው ከዩክሬን ጋር መቀጠል ወይስ ወደ ሩሲያ ግዛት መጠቃለል የሚሉ ምርጫዎች እንዳሉትም ነው የተገለጸው፡፡

የግዛቲቱ አስተዳዳሪ ኢቭጌኒ ባሊትስኪ ጉባዔ በተደረገበት ወቅት ሕዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ተብሏል፡፡

የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን የሆኑት ሩሲያ ቱዴይ እና ታስ እንደዘገቡት ከሆነ ከ700 በላይ የሚሆኑ ተወካዮች ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አጽድቀዋል ብለዋል፡፡

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በምትገኘው ዛፖሮዚ ግዛት ይደረጋል የተባለው ሕዝበ ውሳኔ በመስከርም ወር ሊካሄድ እንደሚችል ፍንጭ ተሰጥቷል፡፡

በዛፖሮዚ ግዛት ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ውሳኔ መተላለፉን በተመለከተ የዘገቡት የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ብቻ ናቸው፡፡

ሩሲያ በምስራቅ ዩክሬን ውስጥ ላሉ ተገጣይ ግዛቶች እውቅና ሰጠች
አሁን ላይ ሕዝበ ውሳኔ ይደረግባታል ተብላ የምትጠበቅ ግዛት ግማሽ ክፍል በሩሲያ ወታደሮች የተያዘው ገና ሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በጀመሩ ሰሞን ነበር፡፡

የተወሰነው የግዛቲቲ ክፍል ብቻ በዩክሬን ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት አራት ወራትን የተሻገረ ሲሆን አሁንም አልተቋጨም፡፡

News today, Politics

ሩሲያ፤ ፑቲንና ዘለንስኪ የሚገናኙበት ምክንያት እንደሌለ አስታወቀች

ሁለቱ ፕሬዝዳንቶች መገናኘት ካለባቸው እንኳን ተደራዳሪዎች ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ነው ተብሏል
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭለድሚር ፑቲን እና የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ሊገናኙ የሚችሉበት ምክንያት እንደሌለ ክሬምሊን አስታወቀ፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፒስኮቭ ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር የሚገናኙበት ምንም መሰረት እንደሌለ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

ፒስኮቭ መሪዎቹ መገናኘት ካለባቸው እንኳን የሚገናኙት የተሰየሙት ተደራዳሪዎች ስራቸውን ከሰሩ በኋላ ብቻ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬን ከጦርነት በኋላ ድርድር የጀመሩ ቢሆንም እስካሁን ግን ትልቅ ለውጥ ያመጣ ውሳኔ አልተወሰነም፡፡

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣኢብ ኤርዶሃን ጦርነት ውስጥ የገቡት የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተነናኝተው እንዲመክሩ ሀሳብ አቅርበው ነበር፡፡

ይሁንና ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፒስኮቭ፤ ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር ሊነጋገሩ ቢችሉ እንኳን ተደራዳሪዎች የተሰጣቸውን የቤት ስራ ሰርተው ካጠናቀቁ በኋላ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ሁለቱም ወገኖች የተጀመረው ድርድር ውጤት አለማምጣቱን ቢናገሩም ውጤት ላለመገኘቱ ግን እርስ በእርስ ግን እየተወነጃጀሉ ነው፡፡

ዲሚትሪ ፒስኮቭም አሁን ላይ እየተደረገ ያለ ንግግር እንደሌለና ለዚህም ተጠያቂዎቹ ዩክሬንን የወከሉ ተደራዳሪዎች እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ሞስኮ እና ኪቭ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ይፋዊ ድርድር ጀምረው የነበረ ቢሆንም ዩክሬን፤ የሩሲያ ኃይሎች ከክሪሚያ ጭምር እንዲወጡ ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት አማካሪ አሌክሰይ አርስቶቪች ሀገራቸው፤ የሩሲያ ወታደሮች ከክሬሚያ እና ዶንባስ ግዛቶች እንዲወጡላት እንደምትፈልግ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

“አሁን ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር መገናኘታቸው አስፈላጊ አይደለም” ያሉት የፑቲን ቃል አቀባይ፤ በዩክሬንም ሆነ በሩሲያ ወገን ያሉት ተደራዳሪዎች ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ምናልባት ሁለቱ ፕሬዝዳንቶች የመገናኘት ዕድል ሊኖራቸው ይችላል ብለዋል፡፡

News today, Politics

የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ “ሩሲያ በዩክሬን ያላትን አላማ ታሳካለች” አሉ


ሜድቬድየቭ “ምዕራባውያን ሩሲያን ለማጥፋት የረዥም ጊዜ እቅድ አላቸው” ሲሉም አስጠነቅቀዋል
የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ “ሩሲያ በዩክሬን ያላትን አላማ ታሳካለች” አሉ፡፡


የፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ ሰው እንደሆኑ የሚነገርላቸው ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ ፤ “ምዕራባውያን ሩሲያን ለማጥፋት የረዥም ጊዜ እቅድ አላቸው” ሲሉም ከሩሲያው ኒውስ ኤጀንሲ ታሳ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ተናግረዋል፡፡


ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ የጸጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ፤ “ሩሲያ በዩክሬን ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ እያካሄደች ነው እናም በምትፈልገው መልኩ ሰላምን እያመጣች ነው” ማለታቸውም ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ሜድቬድየቭ፤ እንደፈረንጆቹ የ2008 የጆርጂያ ጦርነት ፣ የኔቶ ወታደራዊ ህብረት ማጠናከር እና የአሁኑ የዩክሬን ጦርነት፤ አሜሪካ ና አጋሮቿ ሩሲያን ለማጥፋት እስካሁን ያደረጓቻ ሙከራዎች አካል መሆናቸውም በአብነት አንስተዋል።


“ዓላማው አንድ ነው፤ ሩሲያን ለማጥፋት” ሲሉም አክለዋል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ፡፡
በዩክሬን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በእቅዳቸው መሰረት እየሄደ መሆኑን ፕሬዝዳንት ፑቲን ቀደም ሲል ገልጸው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
“በዩክሬን ያለው ጦራችን በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተልዕኮውን በሚገባ እየፈጸመ ነው፣ በዩክሬን መስራት ያለብንን ስራዎች ሁሉ እያከናወኑ ነው”ም ነበር ያሉት ፕሬዘዳንት ፑቲን፡፡


የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቪላድሚር ፑቲን ከወራት በፊት በሰጡት አጭር መግለጫ “ሊስቆመን የሚሞክር፣ በሀገራችን እና በህዝባችን ላይ ተጨማሪ አደጋ የሚጥል ማንኛውም አካል በታሪኩ አይቶት የማያውቀው እጣፋንታ ይገጥመዋል” ሲሉ ምእራባውያን ማስጠንቀቃቸውም አይዘነጋም፡፡
የሩሲያ ምላሽ ፈጣን እንደሚሆን የገለጹት ፕሬዝዳንት ፑቲን የወታደራዊ ዘመቻው አላማ በኪቭ አስተዳደር ለበርካታ አመታት ጥቃት እና የዘርማጥፋት ሲፈጸምባቸው የነበሩትን ዜጎች መታደግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

News today, social life

የአውስትራሊያው አየር መንገድ ባለሥልጣናት ሻንጣ በማውረድና በመጫን እንዲያግዙት ጠየቀ

ሻንጣ እያወረ ያለ ሰው

የአውስትራሊያው አየር መንገድ ካንታስ የጉልበት ሠራተኞች እጥረት ስላጋጠመው የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ሻንጣ በመጫን እና በማውረድ እንዲያግዙት ጠየቀ።

የአየር መንገዱን የዕለት ከዕለት የመንገደኞች ማስተናገድ ሥራውን የሚካታተለው ክፍል እንደገለጸው፣ ሲድኒ እና ሜልበርን ውስጥ በሚገኙ አየር ማረፊያዎች ቢያንስ 100 በጎ ፈቃደኛ የጉልበት ሠራተኞችን እንደሚፈልግ አስታውቋል።

ካንታስ የሚፈልጋቸው የጉልበት ሠራተኞች ሻንጣዎችን ከአውሮፕላኖች ላይ በማውረድና በመጫን እንዲሁም ሻንጣ የሚጫንባቸው ተሽከርካሪዎችን በአየር ማረፊያዎች ውስጥ የሚያንቀሳቅሱ ሾፌሮችን ነው።

በኮሮናቫይረስ ምክንያት አገራት ድንበሮቻቸውን ለአየር በረራዎች ዝግ አድርገው ከቆዩ በኋላ አሁን መክፈት በመጀመራቸው፣ ካንታስን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ አየር መንገዶች የተለያዩ ፈተናዎች እየገጠሟቸው ነው።

“ጉንፋን እና ኮቪድ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራጨቱ እና በገበያው ላይ ሠራተኞችን ለማግኘት ያለው ፈተና አየር መንገዶች ሥራቸውን በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዳያከናውኑ እንቅፋት ፈጥሯል” ሲሉ የካንታስ ባለሥልጣን የሆኑት ኮሊን ሁግስ ለቢቢሲ በኢሜይል ገልጸዋል።

“ያለው አማራጭ በከፍተኛ ኃላፊነት ላይ ሙሉ ጊዜያቸውን ወደሚሰሩ ሰዎች ፊትን ማዞር ነው” ሲሉም ሁግስ አክለዋል።

በዚህም ሳቢያ የካንታስ አየር መንገድ ሥራ አመራሮች ለቀጣይ ሦስት ወራት በፈረቃ፣ በቀን ለስድስት ወይም ለአራት ሰዓታት፣ በሳምንት ለሦስት ወይም ለአምስት ቀናት ሻንጣ የመጫን እና የማውረድ ሥራን እንዲያከናውኑ ተጠይቀዋል።

ካንታስ ባሰራጨው መልዕክት ላይ ለሻንጣ ጫኝነት እና አውራጅነት የሚያመለክቱ ኃላፊዎች ብቻቸውን አስከ 32 ኪሎ ግራም የሚመዝን ክብደት የማንሳት አቅም ሊኖራቸው ይገባል።

“አስካሁን ባለው ሥራችን የደንበኞቻችንን ፍላጎት እና የሚጠበቀውን ደረጃ ማሟላት እንዳላቻልን ግልጽ ነው፣ ስለዚህ ሥራችንን ለማሻሻል ሁሉንም ነገሮች ማድረግ ይጠበቅብናል” ሲሉ የካንታስ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

አየር መንገዱ ከዚህም በፊት ከፍተኛ የመንገደኞች ቁጥር ለማስተናገድ በተገደደበት ጊዜ 200 የሚደርሱ የቢሮ ውስጥ ሠራተኞቹን በተመሳሳይ ሥራ ላይ እንዲያግዙት ማድረጉን አመልክቷል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት አገራት የአየር ክልሎቻቸውን መዝጋታቸውን ተከትሎ ከባድ ቀውስ ከገጠማቸው አየር መንገዶች መካከል ካንታስ አንዱ ነው።

በዚህም ሳቢያ በመላው ዓለም ያሉ አየር መንገዶች በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞቻቸውን መቀነሳቸው ይታወሳል።

አገራት የወረርሽኙን መስፋፋት ለመግታት ወስደዋቸው የነበሩትን ጥብቅ እርምጃዎችን በአሁኑ ወቅት ማላላት በመጀመራቸው ካንታስ እና ሌሎች አየር መንገዶች ሥራቸውን በቀደመው መልኩ ለማካሄድ ፈተና ገጥሟቸዋል።

News today, social life

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው

ዶ/ር ቴድሮስ እንዳልተከተቡ የሚሳዩ ናቸው በሚል የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ሃሰተኛ መሆናቸውንም ድርጅቱ አስታውቋል
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው።

ዶ/ር ቴድሮስ አለመከተባቸውን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች (ቪዲዮ) ተለቀዋል።
የምስሎቹን እውነተኛነት ያጣጣለው የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ አልተከተቡም መባሉን ያለ ሲሆን፤ የድርጅቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ሳይቀሩ ጉዳዩን በማስተባበል ላይ መሆናቸውም ነው የተነገረው።

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በመሆን በድጋሚ ተመረጡ 
በተለያዩ የማህበረሰብ ትስስር ገጾች በመዘዋወር ላይ ያለው ቪዲዮ ዶ/ር ቴድሮስ በአንድ ጆን ኮኸን በተባለ ሰው መቼ እንደተከተቡ ሲጠየቁ እና ክትባቶቹ በአፍሪካ በተለይም ኢትዮጵያ እስከሚደርሱ ድረስ ሳይከተቡ እንደሚቆዩ ሲናገሩ ያሳያል።

ሆኖም ቪዲዮው ሃሰተኛ ነው ሲል ድርጅታቸው አስተባብሏል። እንዲህ ዐይነቱ የፈጠራ ወሬ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አሁንም በመደረግ ላይ ያሉ ጥረቶችን ይጎዳል ሲልም ነው ጉዳዩን ባስተባበለበት ጽሁፉ የገለጸው።
እንደ ድርጅቱ ከሆነ ዶ/ር ቴድሮስ ባለፈው ዓመት ግንቦች ላይ የመጀመሪያውን ክትባት ወስደዋል። ከዚያም ወዲህ የማጠናከሪያ ክትባቶችን ተከትበዋል።

የድርጅት ቃል አቀባይ ጋቢ ስተርን ትናንት እሁድ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ “ውሸታሞች ሲዋሹ እና ህይወትን አደጋ ላይ ሲጥሉ እርምጃ መወሰድ አለበት” ብለዋል፤ መጻፋቸው በዶ/ር ቴድሮስ ላይ የተነዛውን ውሸት ለማስተባበል እንደሆነ በመጠቆም።
“ቁም ነገሩ ክትባቶች ህይወትን መታደጋቸው ነው”ም ብለዋል ቃል አቀባዩ።
ዶ/ር ቴድሮስን ጠያቂው ጆን ኮኸን ዋና ዳይሬክተሩ አልተከተብኩም በሚል የተናገሩት ነገር እንደሌለ ተናግሯል።

ባሳለፍነው ሰኔ በሳይንስ መጽሄት ላይ የወጣ መጣጥፍ ዶ/ር ቴድሮስ በባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት 2021 ግንቦት ላይ መከተባቸውን ያትታል።
ክትባቶች እያሉ ቀደም ብለው ለምን እንዳልተከተቡ የተጠየቁት ዋና ዳይሬክተሩ “ኢትዮጵያ ከምትባል ደሃ ሃገር እና አፍሪካ ከሚባል ደሃ አህጉር መምጣቴን አውቃለሁ፤ ስለሆነም አፍሪካ እና ሌሎች ደሃ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሃገራት ክትባቱን እስከሚያገኙ ለመጠበቅ እፈልግ ነበር” ሲሉ መመለሳቸውንም ያስቀምጣል።

“ከኮሮና ክትባቶች ጋር በተያያዘ ዓለም ‘አስከፊ’ የሞራል ውድቀት እየደረሰበት ነው”- ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር)
በሌላ አገላለጽ ኢ-ፍትሐዊውን የክትባቶች ስርጭት በድርጊት እየተቃወሙ መሆኑንም ነው ዶ/ር ቴድሮስ የሚናገሩት።

ሆኖም አሁን በማህበራዊ ሚዲያዎች በመዘዋወር ላይ ያለው አጭር ቪዲዮ ይህን ምላሻቸውን በማካተት ከተዘጋጀ ዘጋቢ ፊልም (ዶክመንታሪ) ላይ ብዙዎችን ሊያሳስት በሚችል መልኩ ተቀንጭቦ መለቀቁን ነው ተቋማቸው ያስታወቀው።

News today, Politics

የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው


ቻይና የአሜሪካ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታዋንን መጎብኝቷን ተከትሎ ነበር የጦር ልምምዱን የጀመረችው

የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው

ቻይና በታይዋን አቅራቢያ የጀመረችው የጦር ልምምድ እንደቀጠለ ነው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ጨምሮ አምስት የእስያ ሀገራትን መጎብኘታቸውን ተከትሎ በሩቅ ምስራቅ የነገሰው ውጥረት እንደቀጠለ ነው።

አፈ ጉባኤዋ ባሳለፍነው ሳምንት ታይዋንን የጎበኙ ሲሆን ድርጊቱ ቻይናን እንዳስቆጣ የዓለም ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል።

ይሄንን ተከትሎም ቻይና በታይዋን ባህር ዙሪያ እስከ ቀጣዩ ትናንት ድረስ የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆኗን አሳውቃ ነበር።

ይሁንና የቻይና ወታደራዊ የጦርነት ልምምድ ትናንት ያበቃል ተብሎ ቢጠበቅም ልምምድ ዛሬም እንደቀጠለ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል።

የቀጠለው ወታደራዊ ልምምድም የአየር፣የባህር እና የየብስ ጦርነት ልምምድ ሲሆን ታይዋን እና የቡድን ሰባት ሀገራት ልምምዱን ተችተዋል።እንደ ዘገባው ከሆነ ቻይና በታይዋን 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በስድስት አቅጣጫ የጦርነት ልምምዱ እንደቀጠለ ይገኛል ተብሏል።

ቻይና ባሳለፍነው ሳምንት ልምምድ ላይ ዶንግ ፋንግ የተሰኘው የቻይና የረጅም እና አጭር ርቀት ባልስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ታይዋን ባህር ተኩሳለች።

በታይዋን ስድስት አቅጣጫዎች ምንም አይነት የባህር እና አየር ላይ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ቻይና አስቀድማ ማስጠንቀቋ ይታወሳል ።ታይዋን የቻይና ድርጊት የጦርነት ትንኮሳ መሆኑን አስታውቃ እስከ እሁድ የሚቆየውን የጦር ልምምድ እንደማትታገሰው አስቀድማ ተናግራም ነበር።

በቀጠለው የቻይና በታይዋን ባህር አቅራቢያ የጀመረችው የጦር ልምምድ ታይዋን እስካሁን በይፋ የሰጠችው መግለጫ የሌለ ሲሆን ቻይናም ልምምዱ እስከመቼ እንደሚቀጥል አላሳወቀችም።

News today, Politics

ተጠባቂው የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ነገ ይካሄዳል


August 8, 2022
በዚህ ምርጫ ላይ 22 ሚሊየን ኬንያዊያን በመራጭነት ድምጽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል
ተጠባቂው የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ነገ ይካሄዳል።
ኬንያን በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ለመምራት የምረጡኝ ቅስቀሳቸው ሲያካሂዱ የነበሩ እጩ ፕሬዝዳንቶች ምርጫ ነገ እንደሚካሄድ ቢቢሲ ዘግቧል።
ኬንያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት አራት እጩዎች የቀረቡ ሲሆን ባለፉት ምርጫዎች ላይ ለአራት ጊዜ ተወዳድረው ሽንፈትን ያስተናገዱት የኦሬንጅ ዲሞክራቲክ ሙቭመንቱ ራይላ ኦዲንጋ ዋነኛው ተፎካካሪ ናቸው፡፡

ራይላ ኦዲንጋ በፈረንጆቹ 1997 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራቸውን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት እጩ የነበሩ ሲሆን በምርጫው ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡
በነዳጅ እና ሀይል ልማት ዘርፍ ነጋዴ የሖኑት የ77 ዓመቱ ኦዲንጋ ላለፉት አራት ተከታታይ ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ወቅቶች ላይ እጩ ቢሆኑም አብላጫ የህዝብ ድምጽ ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
ውጤታቸውን ተከትሎም ራይላ ኦዲንጋ ከፕሬዝዳናታዊ ምርጫ ራሳቸውን ማግለላቸውን ከአምስት ዓመት በፊት ቢናገሩም ዘግይተው በሰጡት መግለጫ ለአምስተኛ ጊዜ ለፕሬዝዳንትነት መልሰው እንደሚወዳደሩ አሳውቀዋል፡፡
ኬንያን አሁን ላይ በምክትል ፕሬዝዳንትነት እያገለገሉ ያሉት የዲሞክራቲክ ዩኒየኑ ዊሊያም ሩቶ ሌላኛው እጩ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የራይላ ኦዲንጋ ዋነኛ ተፎካካሪ ናቸው ተብሏል፡፡
የ55 ዓመቱ ሩቶ ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በግጭት ውስጥ ሲሆኑ የጸባቸው መንስኤ ደግሞ ፕሬዝዳንቱ ለራይላ ኦዲንጋ ድጋፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው፡፡
ከራይላ ኦዲንጋ እና ዊሊያም ሩቶ በተጨማሪ ለኬንያ ፕሬዝዳንትነት እየተፎካከሩት ያሉት ቀሪዎቹ እጩዎች ዳቪድ ዌሂጋ ጆርጅ ዋጃኮያህ ናቸው፡፡
የሬጌ ሙዚቃ ወዳጅ እንደሆኑ የሚናገሩት እጩ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዋጃኮያህ የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
እጩ ፕሬዚዳንቱ በምርጡኝ ቅስቀሳቸው ላይ ማሪዋና የተሰኘው አደገኛ እጽ ማንኛውም አርሶ አደር እንዲያመርተው እና ምርቱን መጠቀም የፈለጉ ሁሉ በነጻነት እንዲጠቀሙት አደርጋለሁ፣ እንዲሁም ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ እንሲያስገኝ አደርጋለሁ ብለዋል።

የእባብ መርዝ በስፋት በማምረት ለኬንያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ መንገድ አደርጋለሁ ማለታቸው የብዙ ኬንያዊያንን ትኩረት እንዲስቡ ማድረጋቸውም ተገልጿል።
ኬንያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት 55 እጩዎች ቀርበው የነበሩ ቢሆንም በመጨረሻም አራት ብቻ ቀርተዋል።
ኬንያን ላለፉት 10 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የመሩት ኡሁሮ ኬንያታ የስልጣን ጊዜያቸውን ከሁለት ጊዜ በላይ ማራዘም ስለማይችሉ ለተመራጩ ፕሬዝዳንት እንዲያስረክቡ የሀገሪቱ ህገ መንግስት ያስገድዳቸዋል።

News today, Politics

እስራኤል በጋዛ ባደረሰችው ጥቃት ሁለት የታጣቂ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ፍልስጤማውያን ተገደሉ

Ke alemi zuriya-ከዓለም ዙሪያ

በአየር ጥቃቱ የፈረሰ ቤት

7 ነሐሴ 2022

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን (ፒአይጄ) ሁለት አመራሮች አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ፍልስጤማውያን ተገደሉ።

አመራሮቹ ካሊድ መንሱር እና ጣይር ጃብሪ፣ በርካታ የቡድኑ ተዋጊዎችና ስድስት ህፃናትን ጨምሮ 32 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸው ተዘግቧል።

ከአርብ ጀምሮ ወደ 400 የሚጠጉ የፍልስጥኤም ሮኬቶች እና ሞርታሮች በእስራኤል ላይ መተኮሳቸውን የእስራኤል ባለስልጣን ተናግረዋል።

እስራኤል ወታደራዊ ዘመቻ ብላ የምትጠራውን ይህንን የአየር ጥቃት የጀመረችው የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን በደቀነው ከፍተኛ ስጋት ነው ብላለች።

ባለፈው አመት ግንቦት ወር ለ11 ቀናት በዘለቀው እና ከ200 በላይ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም በርካታ እስራኤላውያን ከተገደሉበት ግጭት ወዲህ ይህ በቅርቡ በእስራኤልና በጋዛ መካከል የተከሰተ አሳሳቢ ግጭት አድርጎታል።

‘ብሬኪንግ ዳውን’ ( መሰባበር) የሚል የኮድ ስም እስራኤል የሰጠችው ወታደራዊ ዘመቻ ለአንድ ሳምንት ሊቆይ እንደሚችል ባለስልጣናቷ አስጠንቅቀዋል።

በሁለተኛው ቀን ጥቃት ትናንት ቅዳሜ በደቡባዊ ጋዛ ራፋህ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ከፍተኛ የፒአይጄ መሪ ካሊድ መንሱርን መግደሏን አስታውቃለች።

ከጋዛ ውጭ ወታደራዊ ጥቃቶችን ፈጽሟል በማለት እስራኤል የምትከሰው ካሊድ መንሱር ከዚህ ቀደም በእስራኤል ጦር ከአምስት የግድያ ሙከራዎች ተርፎ ነበር።

ከሱ ሞት በፊት አርብ እለት ከፍተኛ የፒአይጄ አመራር የሆነው ታይሲር ጃባሪ በእስራኡል የአየር ጥቃት ተገድሏል።

እንዲሁም በጋዛ በተፈጸመው የአየር ጥቃት ድብደባ በርካታ የቡድኑ አባላት ከመገደላቸው በተጨማሪ እስራኤል ተቆጣጥራት ባለቸው የዌስት ባንክ በተደረገ ከበባ 19 የሚሆኑ የፒአይጄ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እስራኤል ገልጻለች።

የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለፍልስጥኤማውያን ሞት እንዲሁም ለቆሰሉት 203 ሰዎች “የእስራኤል ወራራን ተጠያቂ አድርጓል።

News today, Politics

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ደቡብ አፍሪካ ደርሰዋል

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን

ብሊንከን በአፍሪካ ጉብኝታቸው ከፕሪቶሪያ በተጨማሪ ኬንሻሳ እና ኪጋሊን ይጎበኛሉ ተብሏል

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መጀመራን ተከትሎ በሩሲያ ላይ ጫና ለመፍጠር ከወራት በፊት በመንግስታቱ ድርጅት በተጠራ ስብሰባ ላይ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጋቸው አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያንን አስቆጥቷል።

ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ ጊዜያት የአሜሪካ እና አውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ አፍሪካ በመጓዝ ጫና በማድረግ ላይ ናቸው።

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም የመነጠል ስራውን ለማጠናከር የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።

ብሊንከን ከሰዓታት በፊት ደቡብ አፍሪካ መዲና ፕሪቶሪያ የደረሱ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ስሪል ራሞፎሳ ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

ብሊንከን ከደቡብ አፍሪካ በተጨማሪም ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።

ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።

ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ከነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ በግጭት ውስጥ ያሉት ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል እንደሚሰሩም ተገልጿል።

እንዲሁም አንቶኒ ብሊንከን በኪጋሊ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ጋር በስህተት ስለታሰሩት የሆቴል ሩዋንዳ ፊልም ሰሪ ፖል ሩሴሳባጊና ጉዳይ እንደሚወያዩም ይጠበቃል ተብሏል።

የአንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት የሩሲያው አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ መሆኑ የጉዟቸው አላማ የሩሲያን ተጽዕኖ ከአፍሪካ ለመነጠል ያለመ እንደሆነ ሌሎች ዘገባዎች እየወጡ ይገኛል።

አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ

በጥቃቱ ከ265 የሚልቁ ሰዎችም ቆስለዋል ተብሏል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት

ከሟቾች መካከል ሁለት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን አመራሮች ይገኙበታል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ።

በየጊዜው ግጭት ውስጥ የሚገቡት እስራኤል እና ፍልስጥም አሁንም መልሰው ግጭት ውስጥ ገብተዋል።

የእስራኤል ጦር ባሳለፍነው ሰኞ የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን መሪ የሆኑት ባሳም አልሳዲን በዌስት ባንክ ማሰራቸውን ተከትሎ በጋዛ አውዳሚ ግጭት ተቀስቅሷል።

በጋዛ ሰርጥ ውስጥ እየተካሄደ ባለው በዚህ ጦርነት እስራኤል በተኮሰቻቸው የሮኬት ጥቃቶች የሞቱ ሰዎች ቁጥር 32 መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።

ከ265 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ዘገባው አክሏል።

ከሟቾች ውስጥ ስድስቱ ህጻናት ሲሆኑ አራቱ ደግሞ ሴቶች እንደሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የሟቾች እና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተጠቅሷል።

የእስራኤል ጦር የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን ምክትል መሪ ካሊድ ማንሱርን በጋዛ ሰርጥ በሮኬት ጥቃት መግደሏን አስታውቃለች።

የእስራኤል ጦር በፍልስጤም ጋዛ እንደሚንቀሳቀስ የተገለጸው የእስልሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን የሚለውን ለመስማት በሚል የተኩስ አቁም አውጇል።

የፍልስጤም ጤና ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ እስራኤል የምትተኩሳቸው የሮኬት ጥቃቶች ንጹሀንን እየገደለ መሆኑን ገልጿል።

News today, Politics

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ


ብሊንከን በአፍሪካ ጉብኝታቸው ከፕሪቶሪያ በተጨማሪ ኬንሻሳ እና ኪጋሊን ይጎበኛሉ ተብሏል
የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ።
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መጀመራን ተከትሎ በሩሲያ ላይ ጫና ለመፍጠር ከወራት በፊት በመንግስታቱ ድርጅት በተጠራ ስብሰባ ላይ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጋቸው አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያንን አስቆጥቷል።
“ሉዓላዊነትን እና ግዛታዊ አንድነትን ማክበር ለአፍሪካ ቀንድ መረጋጋትና ልማት አስፈላጊ ነው” – ብሊንከን 
ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ ጊዜያት የአሜሪካ እና አውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ አፍሪካ በመጓዝ ጫና በማድረግ ላይ ናቸው።
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም የመነጠል ስራውን ለማጠናከር የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።
ብሊንከን ከሰዓታት በፊት ደቡብ አፍሪካ መዲና ፕሪቶሪያ የደረሱ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ስሪል ራሞፎሳ ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።
ብሊንከን ከደቡብ አፍሪካ በተጨማሪም ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።
ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ከነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ በግጭት ውስጥ ያሉት ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል እንደሚሰሩም ተገልጿል።
እንዲሁም አንቶኒ ብሊንከን በኪጋሊ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ጋር በስህተት ስለታሰሩት የሆቴል ሩዋንዳ ፊልም ሰሪ ፖል ሩሴሳባጊና ጉዳይ እንደሚወያዩም ይጠበቃል ተብሏል።
አንቶኒ ብሊንከንና ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ተወያዩ 
የአንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት የሩሲያው አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ መሆኑ የጉዟቸው አላማ የሩሲያን ተጽዕኖ ከአፍሪካ ለመነጠል ያለመ እንደሆነ ሌሎች ዘገባዎች እየወጡ ይገኛል።
አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics, social life

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጣለች

የሞስኮ ማዕቀብ ካናዳ ከዚህ በፊት በሩሲያዊያን ላይ ለጣለችው ማዕቀብ የአጸፋ እርምጃ ነው ተብሏል

ሩሲ እና ካናዳ

ሩሲያ ካናዳዊያን ዲፕሎማቶች፣ የሀይማኖት መሪዎች፣ ፖለቲከኞችና ምሁራን ላይ ነው ማዕቀብ ጣለችው

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታውቃለች።

ሩሲያ ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ወደ ይፋዊ ጦርነት የገባችው።

 ይሄንን ጦርነት ተከትሎም በሩሲያ ላይ ከ6 ሺህ በላይ ማዕቀቦች ሲጣልባት ከ400 በላይ ዲፕሎማቶቿ ደግሞ ከተለያዩ ሀገራት ተሰናብተዋል።

ካናዳም የሩሲያ ዲፕሎማቶችን ከማባረሯ ባለፈ በሩሲያ ጋዜጠኞች ፣ ባለሀብቶች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

የሩሲያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ካናዳ ለወሰደችው ማዕቀብ ምላሽ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

ይህ ማዕቀብ የተጣለባቸው ካናዳዊያን ወደ ሩሲያ እንዳይገቡ እና በሩሲያ ያላቸው ሀብት እንዳይንቀሳቀስ እንደሚደረግ ሮይተርስ ዘግቧል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በሀገሪቱ እንዲሁም በተቋማቶቿ እና ባለሃብቶቿ ላይ ማዕቀብን ጨምሮ የተለያዩ እገዳዎችን የጣሉ እርምጃዎቹን የደገፉ ሀገራትን “ወዳጅ አይደሉም” ማለቷ ይታወሳል።

News today, Politics

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ተባብራ የምትሰራባቸውን ቁልፍ ጉዳዮች ማቋረጧን አስታወቀች

የቻይና የጦር አውሮፕላን
የምስሉ መግለጫ,ቻይና በታይዋን ዙሪያ በባሕር እና በአየር የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ እንደቀጠለ ነው

6 ነሐሴ 2022

የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን በታይዋን ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ቻይና በበርካታ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ጋር ተባባሮ የመሥራት ስምምነቷን ማቋረጧን አሳወቀች።

አሜሪካ እና ቻይና በዓለም የአየር ፀባይ ለውጥ፣ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ሊያደርጉ የነበረው ውይይት እና የዓለም አቀፍ ወንጀሎችን በመዋጋት በኩል ተባብሮ ለመሥራት ስምምነት ነበራቸው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሴ ግዛቴ በምትላት ታይዋን ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው ቻይና ከአሜሪካ ጋር ተባብሮ ለመሥራት የነበራትን እቅድ ለመቋረጥ የወሰነችው።

በተጨማሪም ቻይና ሉዓላዊ ግዛቴ ናት በምትላት ታይዋን ላይ ያላትን ይገባኝል በመቃረንም በአፈ ጉባኤ ፔሎሲ እና ቤተሰቦቻቸው ላይ ዕቀባን ጥላለች።

ቻይና እንደተገንጣይ ግዛትዋ የምትመለከታት ታይዋን እራሷን ከቻይና የተለየች ግዛት አድርጋ ትመለከታለች።

ቻይና ውሳኔዋን ያሳወቀችው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ሲሆን፣ በዚህም በአሜሪካ እና በቻይና የመከላከያ ባለሥልጣንት መካከል የሚካሄድ ውይይት ሲሰረዝ፣ ሕገ ወጥ ስደተኞችን የመመለስ ትብብር፣ የአየር ፀባይ ለውጥ፣ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ላይ በጋራ ምርመራ የማድረግ ሥራም እንዲቀቋረጥ ተደርጓል።

ሁለቱ ኃያላን አገራት የዓለም የአየር ፀባይ ለውጥን ለመከላከል በቀጣይ ዓመታት መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ደርሰው ነበር። ባለፈው ዓመት በተደረገው ጉባኤ ላይም ቻይና የበካይ ጋዝ ልቀትን ለመቀነስ ከአሜሪካ ጋር በጋራ ለመስራት ቃል ገብታ ነበር።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው ይህ ውሳኔ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፔሎሲ “የቻይናን ጠንካራ ተቃውሞ ችላ በማለት ባሳዩት ከባድ ምሳሌ” ምክንያት መሆኑን ገልጿል።

ቻይና በአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት የፔሎሲ ጉብኝትን “የከፋ ጠብ አጫሪነት” ነው በማለት ተቃውሞዋን ያሰማች ሲሆን፣ የቻይና የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ በትዊተር ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ ባለፈው ዓመት አሜሪካ ውስጥ በፖሊስ ተንቆ የተገደለውን ጥቁር አሜሪካዊን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

“አሜሪካ የዓለም ፖሊስ እንድትሆንና አገራትን በማስፈራራት እንደ ጆርጅ ፍሎይድ እንድታንቅ አንፈቅድም” ሲሉ ጽፈደዋል።

አርብ ዕለት የዋይት ሐውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ካሪን ጂን-ፔሪ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን የመሄድ “ሙሉ መብት ነበራቸው” በማለት፣ ቻይና የወሰደችውን እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ሲሉ ተቃውመውታል።

News today, Politics, social life

ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ


የሩሲያ እና የቱርክ ፕሬዝደንቶች በትናንትናው እለት በሩሲያ ሶቺ ከተማ ተገናኝተው መክረዋል

ሩሲያ እና ቱርክ፤ በሩሲያው ገንዘብ ሩብልስ ለመገበያየት ተስማምተዋል፡፡

የሩሲያ እና ቱርክ መሪዎች በትናንትናው እለት በሩሲያዋ ሶቺ ከተማ ባደረጉት ውይይት የኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት መፈረማቸውን የሩሲያ አርቲ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ያለባትን የውጭ ሀገራት እዳ በራሷ ገንዘብ “ሩብል” እንደምትከፍል አስታወቀች
ስምምነቱ መፈረሙን የገለጹት የቱርኩ ፕሬዝደንት ረሲፕ ተይፕ ኤርዶጋን ናቸው፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬንን የማደራደር ሚያ ያላት ቱርክ ከሩሲያ ጋር በሩብልስ ለመገበያየት መስማማቷን ፕሬዘደንት ኤርዶጋን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አርብ ዕለት በቱርክ እና በሩሲያ ልዑካን መካከል የተካሄዱት ስብሰባዎች ፍሬያማ እንደነበሩ እና በሩሲያ በሚያደርጉት ጉብኝት በሶሪያ ስላለው ሁኔታ ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል።

ሩሲያ በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ ሩሲያ አሜሪካን ጨምሮ ከምእራባውያን ጋር ሁሉን አቀፍ ፍጥጫ ውስጥ ገብታለች፡፡

አሜሪካን ጨምሮ ምእራበውያን ሀገራት ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ማእቀብ ሁሉ በሩሲያ ላይ አዝንበዋል፤ ሩሲያ ማእቀቡን ለመመከት ምእራባውያን ሀገራት ጋዝ በሩብል እንዲገዙ አስገድዳለች፡፡

News today, Politics

የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪ ሆቴል ውስጥ ሞተው ተገኙ

የሀገሪቱ መርማሪ ፖሊስ የኦው ያንግ የሞቱበትን ምክንያት በማጣራት ላይ መሆኑ አስታውቋል

የታይዋን መከላከያ ሚኒሰቴር “ኦው ያንግ የታይዋን የሚሳዔል የማምረት አቅምን ለማሳደግ ሲሰሩ የነበሩ ከፍተኛ ባለሙያ ናቸው”ብሏል

የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪና በወታደራዊ ባለቤትነት የተያዘው የናሽናል ቹንግ-ሻን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ምክትል ኃላፊ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ፤ ሆቴል ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን  የታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

እንደ የታይዋኑ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ዘገባ ከሆነ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ሞተው የተገኙው በደቡባዊ ታይዋን በሚገኝ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡

ከቤተሰቦቹ በተገኘ መረጃ መሰረት የ57 አመቱ ኦው ያንግ የሞት ምክንያት የልብ ድካም ሊሆን እንደሚችል ቢገለጽም፤ የሀገሪቱ መርማሪ ፖሊስ ትክክለኛው የሞት ምክንያት ለማወቅ አስፈላጊውን የማጣራት ሂደት ላይ መሆኑ አስታውቋል፡፡

ኦው ያንግ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ የተለያዩ የሚሳዔል ማምረቻ ፕሮጀክቶችን ለመከታተል በሚል ወደ ሃላፊነት የመጡ እንዲሁም ወደ ሃላፊነት ከመጡ ወዲህ የታይዋን የሚሳዔል የማምረት አቅምን ከእጥፍ በላይ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የቆዩ ከፍተኛ ባለሙያ እንደነበሩ የታይዋን መከላከያ ሚኒሰቴር መረጃ ያስረዳል፡፡

ታይና ከቻይና ሊቃጣባት የሚችለውን አደጋ ለመከላከል በሚል ሚሳዔልን በከፍተኛ ሁኔታ በማምረት ላይ ተጠምዳለች፡፡ በዚህ አመት ብቻ የሚሳዔል ማምረት አቅሟን ወደ 500 ለማሳደግ እየሰራች መሆኗም ይገለጻል፡፡

የወቅቱ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ ቻይና እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷ፤ የታይዋን መሪዎች ነገሮች በቅርበት እንዲከታተሉ ያስገደደና ሁኔታ መፈጠሩ የሚታወቅ ነው፡፡

በዚህም አሁን ላይ የናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት ተከትሎ ቻይና በምታደርገው የአየር ላይ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በሩቅ ምስራቅ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰ ሲሆን ታይዋን ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ እንዳወጀች ነው፡፡

የታይዋን ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን ሀገራቸው ማንንም እንደማትተነኩስና ነገርግን ራሷን እንደምትከላከል መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለታይዋን ብቻ ሳይሆን ለመላው አለም ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲም ነበር የተናገሩት ፕሬዝዳንቷ፡፡

News today, Politics, social life

በእስራኤል ጥቃት አንድ የታጣቂ ቡድን መሪን ጨምሮ አስር ሰዎች ተገደሉ


እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት አንድ የፍልስጤም ታጣቂዎች ቡድን መሪን እና አንዲት ህጻንን ጨምሮ 11 ሰዎች መገደላቸውን ሪፖርቶች አመለከቱ።

ይህን የእስራኤል ጥቃት ተከትሎ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ሮኬቶች ከጋዛ ወደ እስራኤል የተተኮሱ ሲሆን፣ በዚህም ሳቢያ በአካባቢው ከባድ ውጥረት ነግሷል።

ይህንንም ተከትሎ እስራኤል በወረራ በያዘችው የዌስት ባንክ አካባቢ ባደረገችው አሰሳ 19 የኢስላሚክ ጂሃድ ቡድን አባላት ናቸው የተባሉ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሏ ተገልጿል።

በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት 11 ሰዎች መካከል ታይሰር ጃባሪ የተባለ የታጣቂዎች መሪ ይገኝበታል።

የአየር ጥቃቱ ግለሰቡ የሚመራው የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ የተባለው ቡድን “ጥቃት ሊሰነዝር” መሆኑን ተከትሎ የተወሰደ እርምጃ ነው ስትል እስራኤል ምክንያቷን አሳውቃለች።

ከተገደሉት መካከል የአምስት ዓመት ታዳጊ የምትገኝበት ሲሆን፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸው የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት ተናግረዋል።

የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ የተባለው ቡድን ለእሰራኤል ጥቃት “የመጀመሪያ ምልሽ” ባለው አጸፋ ከ100 በላይ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ሌሊቱን ተኩሷል።

ከተተኮሱት ሮኬቶች አብዛኞቹ በእስራኤል የሚሳኤል መከላከያ አማካይነት መክሰማቸው የተነገረ ሲሆን፣ በበርካታ የእስራኤል ከተሞች ውስጥ ሌሊቱን በሙሉ የጥቃት ማስጠንቀቂያ ደውሎች ሲሰሙ አድረዋል።
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር እስከ ቅዳሜ ንጋት ድረስ የዘለቁ የሮኬት ጥቃቶችን ጋዛ ውስጥ በሚገኙ በርካታ የታጣቂዎቹ ይዞታዎች ላይ ሲፈጽም ማደሩን ኣሰውቋል።

ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ተመሳሳይ ግጭት ተከስቶ ከ200 በላይ ፍልስጤማዊያን እና በርካታ እስራኤላውያን ከተገደሉ በኋላ በግብፅ አደራዳሪነት የተኩስ አቁም መደረሱ ይታወሳል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ያይር ላፒድ ሠራዊታቸው ለአገራቸው ስጋት በሆኑ ኢላማዎች ላይ ፈጣን ፀረ ሽብር ጥቃት መፈጸሙን የገለጹ ሲሆን፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ደግሞ ግጭቱ የተራዘመ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን አመልክተዋል።

ጋዛ ውስጥ በእስላማዊ ቡድን ኢላማዎች ላይ ነው የተፈጸመው በተባለው ጥቃት “15 የሚሆኑ ታጣቂዎች” መገደላቸውን የእስራኤል ሠራዊት ቃል አቀባይ መናገራቸው ተዘግቧል።

የጋዛ የጤና ባለሥልጣንት ግን ታይሲር ጃባሪን ጨምሮ አራት የእስላማዊ ቡድኑ ታጣቂዎች በእስራኤል ጥቃት መገደላቸውን አረጋግጠዋል።

የእስራኤል የመከላከያ ኃይል ታይሲር ጃባሪ የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን “ከፍተኛ መሪ” መሆኑን እና “በርካታ የሽብር ጥቃቶችን” በእስራኤላውያን ሰላማዊ ሰዎች ላይ ፈጽሟል ሲል ይከሰዋል።

የጋዛ ባለሥልጣናት እንዳሳወቁት በጥቃቱ ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ 79 ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው መናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል።

የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን ዋና ፀሐፊ ዚያድ አል-ናኻላ ወደ ኢራን በጉዞ ላይ ሳሉ “ለተፈጸመው ጥቃት በሙሉ ኃይላችን ምላሽ እንሰጣለን፣ በአሸናፊነት የምንወጣበት ጦርነት ይሆናል። የማይነካ ቦታ አይኖርም፣ ቴል አቪቭ በሮኬቶቻችን ጥቃት ስር ትሆናለች” ማለታቸው ተዘግቧል።

የጋዛ ሰርጥን የሚያስተዳድረው ሐማስ የፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች ዝም እንደማይሉና በሚካሄደው ዘመቻ ውስጥ በአንድነት እንደሚቆሙ ገልጿል።

News today, Politics

ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቅ ለመፍታት ከመንግስት ጋር ተስማሙ


ታጣቂዎቹ ላለፉት 40 ገደማ ዓመታት ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ነበር
በሀገሪቱ መንግስት እና በታጣቂዎቹ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል

የሴኔጋል መንግስት እና ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች እርቅ አወረዱ።

በሴዛር አቶቴ ባዲያቴ የሚመራው የካሳማንቼ ኃይሎች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (MDFC) ላለፉት 40 ገደማ ዓመታት ነፍጥ አንግቦ በደቡባዊ ሴኔጋል ሲንቀሳቀስ ነበር።

ሆኖም አሁን ትጥቅ አውርዶ ሰላማዊ ትግል ለማድረግ መስማማቱን አስታውቋል።

ስምምነቱን በፀጋ የተቀበሉት ፕሬዝዳንት ማኪ ሳልም ከሴዛር አቶቴ ጋር ከትናንት በተስቲያ ሐሙስ ተፈራርመዋል እንደ ሲጂቲኤን ዘገባ።

ማኪ ሳል የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ናቸው።

ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እንደሚያስችል ተስፋ የተጣለበት የሰላም ስምምነት በጊኒ ቢሳው ነው የተፈረመው።

ስምምነቱ በሸምጋዮች ጥረት እውን የሆነ ሲሆን፤ ማኪ ሳል አማጺ ቡድኑን ከመንግስታቸው ጋር ለማሸማገል ላደረጉት ጥረት የጊኒ ቢሳውን ፕሬዝዳንት ዑማሮ ሲሶኮ ኢምባሎን አመስግነዋል።

የካሳማንቼ ኃይሎች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (MDFC) ነፍጥ አንግበው ለረጅም ዓመታት ከተንቀሳቀሱ የአፍሪካ አማፂ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው።

News today, Politics

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ቤጂንግ ለናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት በዚህ ደረጃ ምላሽ የመትሰጥበት “ምንም ምክንያት የለም” አሉ

ብሊንከን፤ ቻይና ታይዋንን በመክበብ የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ “ውጥረትን የሚያባብስ” ነው ሲሉ ኮንነዋል

2022/8/5 16:12 GMT

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን

በፔሎሲ ጉብኝት የተበሳጨችው ቻይና “ከአሜሪካ ጋር ስታደረግ የነበረው ወታደራዊ ማቋረጧን” ይፋ እስከማድረግ ደርሳለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ቻይና ታይዋንን በመክበብ የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ ‘ያለው ውጥረት የሚያባብስ’ ነው ሲሉ ኮነኑ።

ብሊንከን የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ላደረጉት ጉብኝት ምላሽ ለመስጠት በሚል ቤጂንግ ለጀመረችው ወታደራዊ ልምምድ የምታቀርበው “ምንም ምክንያት የለም” ማለታቸውም ኤፒ ዘግቧል።

ቻይና ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ተዋጊ ጄቶች እና የጦር መርከቦች በታይዋን ዙሪያ ማሰማራቷን ተከትሎ በዓለም ላይ እጅጉን የመርከብ መስመሮች የሚበዙበት ቀጠና አደጋ እንዳንዣበበበት እየተገለፀ ነው።

ከደቡብ ምስራቅ እስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ለመወያየት በበካምቦድያ መዲና ፕኖም ፔን የሚገኙት ብሊንከን ጉዳዩን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ “የቻይና ድርጊቶች ያለውን ውጥረት ትርጉም ባለው ደረጃ የሚያባብሱ ናቸው” ሲሉ ተደምጠዋል።

በቅርቡ በኢንዶኔዥያ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ዋንግ ዪን፤ በ25 ዓመታት ውስጥ ታይዋንን የጎበኙ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ፒሎሲ ወደ ደሴቲቱ ሊጓዙ እንደሚችሉ ነገሬው ነበር ያሉት ብሊንከን፤ የቻይና ድርጊት ከጠበቅነው ውጭ ባይሆንም የተጋነነ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

“እውነታው ግን የአፈ ጉባኤዋ ጉብኝት ሰላማዊ ነበር፤ እንደዚህ አይነት የተጋነነ እና ተመጣጣኝ ያልሆነ ወታደራዊ ምላሽ የሚያሰጥበት ምንም ምክንያት የለም” ሲሉም አክለዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ብሊንከን ይህን ይበሉ እንጂ፤ ናን ፔሎሲ ቻይና እንደ አንድ ግዛቷ አድርጋ በምትቆጥራት ታይዋን ላይ ያደረጉት ጉብኝት የቤጂንግ ሰዎች ኩፉኛ ማስቆጣቱ እየተገለጸ ነው።

በአሜሪካ ድርጊት እጅጉን የተበሳጨችው ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን ማቋረጧን ከሰዓታት በፊት አስታውቃለች።

ቻይና በውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ በኩል በሰጠቸው መግለጫ፤ ቤጂንግ እስካሁን ከከፍተኛ ወታደራዊ ትብብሮች ባለፈ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ከዚህ በፊት የነበራትን የከፍተኛ መሪዎች የጋራ ውይይት መድረኮችን ከአሜሪካ ጋር በትብብር ላለመስራት ወስናለች።

እንዲሁም ቻይና ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን ማጓጓዝ፣ አደገኛ እጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን አቋርጣለች።

ቻይና ሰሞኑን ታይዋንን በጎበኙት የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ላይ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።

News today, Politics

ኢትዮጵያ የ“አንድ ቻይና” ፖሊሲን እደግፋለሁ አለች

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህ የኢትዮጵያ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ብሏል

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም

የናንሲ ፔሎሲን ጉዞ ተከትሎ በቻይና-ታይዋን ጉዳይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱ ይታወቃል

ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የ”አንድ ቻይና” ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ከወቅታዊ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የሚከሰቱ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ያሳስቧታል ብለዋል።

ሰሞኑን በቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑንም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ የ“አንድ ቻይና” ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት አምባሳደር መለስ፥ “ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው” ብለዋል።

አሁንም ኢትዮጵያ ለ“አንድ ቻይና” ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉም ሲሆን፥ ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረትም እንደሚያራምዱት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን የሚያጠናክር ውጤታማ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው አምባሳደር መለስ ያነሱት።

የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የተመሰረተበትን 95ኛ ዓመት ክብረ በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የሀገሩን ሉዓላዊነት፣ ጸጥታና ጥቅም ከማስከበር አልፎ ለዓለማችን ሰላምና መረጋጋት እያደረገ ላለው በጎ ሚና ያላቸውን አድናቆት መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲን የቻይናን ዛቻ ወደ ጎን በመተው ወደ ታይዋን መጓዛቸውን ተከትሎ በቻይና-ታይዋን ጉዳይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱ ይታወቃል።

ቻይና አሜሪካ በዴሞክራሲ ሽፋን ሉአላዊነቴን ተዳፍራለች ያለች ሲሆን፤ ቻይናን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ ማለቷ አይዘነጋም።

የቻይና ጦር የፔሎሲን ጉብኝት ተከትሎ የአጸፋ እርጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ በትናንትናው እለትም 27 የቻይና የጦር ጄቶች የታይዋንን የአየር ክልል ጥሰው ገብተዋል።

ሩሲያ፣ ሰሜን ከሮያ እና ኤርትራ ቻይናን በመደገፍ አቋማቸውን ያንፀባረቁ ሲሆን፤ ኤርትራ የፔሎሲን ጉብኝት ህግን የጣሰ ነው ስትልም ተችታለች።

News today, Politics

ሙሴቪኒ ከአሜሪካዋ ዲፕሎማት ጉብኝት አስቀድመው ‘ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም’ አሉ

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ
የምስሉ መግለጫ,ዬዌሪ ሙሴቪኒ

ከ 6 ሰአት በፊት

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር የኡጋንዳ ጉብኝትን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም ሲሉ ለቢቢሲ ተናገሩ።

አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸው ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 28/2014 ዓ.ም. ከኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አምባሳደሯ ከዋሽንግተን ዲሲ መመሪያዎችን ይዘው ይመጡ እንደሆነ የተጠየቁት ሙሴቬኒ፤ “ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም” ሲሉ መልሰዋል።

ሙሴቬኒ አገራቸው ኡጋንዳ ከምዕራባውያን የሚላከውን እርዳታ በመልካም ጎኑ እንደምትመለከተው ጠቅሰው፤ አገራቸው ያለ እርዳታ መኖር እንደምትችልም ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ ኡጋንዳ በሩሲያ እና በዩክሬን ጦርነት ዙሪያ የያዘችውን አቋም ለማስቀየር የተደረገ ጥረት እንደሌለ ገልጸዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ወረራ እንድታቆም ያወጣውን ምክር ሃሳብ በድምጸ ታዕቅቦ ካለፉት 16 የአፍሪካ አገራት መካከል ኡጋንዳ አንዷ መሆኗ ይታወቃል።

አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪን ፊልድ ወደ ካምፓል የሚያመሩት የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኡጋንዳ ጉብኝት ካደረጉ ከቀናት በኋላ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ በቅርቡ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ በአራት የአፍሪካ አገራት ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።

ሙሴቬኒ፤ “ጥሩ ጓደኛ” ሲሉ የገለጿቸው አምባሳደር ቶማስ-ግሪንፊልድን ሁሌም ወደ ኡጋንዳ እንዲመጡ በራችን ከፍት ነው ካሉ በኋላ፤ አስተዳደራቸው ለምዕራባውያን ጫና እንደማይበረከክ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ በሩሲያ እና በዩክሬን ጦርነት ዙሪያ አቋማቸው ምን እንደሆነ ሲጠየቁ፤ ጦርነቱን ከ1962ቱ የኩባ ሚሳኤል ቀውስ ጋር አነጻጸረውታል።

ሙሴቪኒ ዛሬ ላይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) በሩሲያ ዙሪያ መገኘትን ሶቪየት ሕብረት አሜሪካ አፍንጫ ስር ኩባ ውስጥ ሚሳኤል ከመትከሏ ጋር አነጻጽረውታል።

የኩባ ሚሳኤል ቀውስ ተብሎ የሚታወቀው ክስተት የወቅቱ የዓለማችን ኃያላንን ወደ ኒውክሌር ጦርነት እንዲገቡ ከጫፍ አድርሶ ነበር።

በወቅቱ ሶቪየት ሕብርት የኩባን ደኅንነት ከአሜሪካ ጥቃት ለመጠበቅ በሚል፣ ኩባ ውስጥ የአሜሪካ ከተሞችን መምታት በሚያሰችሉ ስፍራዎች ላይ የኒውክሌር አረሮችን ማስወንጨፍ የሚችሉ ሚሳኤሎችን ተክላ ነበር።

ሙሴቬኒ ይህ ክስተት የአሜሪካንን የደኅንነት ስጋት ውስጥ ከትቶ እንደነበረ ተናግረው፤ በወቅቱ አገራቸው ለአሜሪካ ድጋፏን መሽጠቷን አስታውሰዋል።

ሙሴቬኒ ዛሬም ተመሳሳይ መርኅ ማረመድ አለብን ብለዋል።

ሙሴቬኒ ኔቶ በሩሲያ ዙሪያ መክተሙ፤ የሩሲያን እርምጃ እንዲገነዘቡ ያደርግዎታል ወይ ተብለው ሲጠይቁ፤ “በትክክል” ሲሉ መልሰዋል።

“ታሪክ የምትሉትን፤ እኔ ወቅታዊ ጉዳይ እለዋለሁ” ብለዋል ሙሴቬኒ።

News today, Politics

ሩሲያ ባለፉት ቀናት ውስጥ 500 የዩክሬን ወታደሮችን ገደልኩ አለች

ከምዕራባዊያን ለዩክሬን የተለገሱ በርካታ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟንም ሩሲያ አክላለች

ሩሲያ በሞስኮ የኖርቄይ ዲፕሎማትንም ማባረሯን አስታውቃለች

ሩሲያ ባለፉት ቀናት ውስጥ 500 የዩክሬን ወታደሮችን ገደልኩ አለች፡፡

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስድስት ወራት 162ኛ ቀኑ ላይ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን ጦርነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ዓለም አቀፋዊ ሆኗል።

የሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ባለፉት ቀናት በተካሄደው ጦርነት 500 የዩክሬን ወታደሮች መግደሉን አስታውቋል።ሚኒስቴሩ አክሎም ከአሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባውያን ሀገራት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን አውድሜያለሁም ብሏል።

የሩሲያ ጦር በዶንቴስክ እና ካርኪቭ አካባቢዎች ባካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ በርካታ የዩክሬን እና ቅጥረኛ ወታደሮች ይዞታዎችን እና የጦር ማዘዣዎችን ማውደሙንም አስታውቋል።

እንዲሁም ከረጅም እና አጭር ርቀት ሚሳኤል መሳሪያዎች፣ የጦር ተሽከርካሪዎች፣ መጋዝኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ ስፍራዎችን የሩሲያ አየር ሀይል መምታቱን አርቲ ዘግቧል።

የሩሲያ ጦር 390 የዩክሬን የጦር አውሮፕላኖች ፣ 1506 ድሮኖች፣ 354 ጸረ አውሮፕላን ሚሲኤሎች እና ከ 11 ሺህ በላይ የጦር ታንኮች፣ ልዩ የጦር ተሽከርካሪዎች፣ ጸረ ሮኬት መሳሪያዎች እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎች ማውደሙን ዘገባው አክሏል።

የዩክሬን መንግስት በሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር መግለጫ ዙሪያ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም።

በተያያዘ ዜና ሩሲያ ከሰሞኑ አንድ የኖርዌይ ዲፕሎማት በአንድ መዝናኛ ስፍራ ገብታ በተናገረችው ጸረ ሩሲያ ንግግር ምክንያት ሞስኮን ለቃ እንድትወጣ መወሰኗን አስታውቃለች።

News today, Politics

ኤርትራ፤ የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ዓለም አቀፍ ሕግ “የጣሰ ነው” አለች

ኤርትራ፤ የፔሎሲን ጉብኝት ያወገዘች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ናት

የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ (ፎቶ ከፋይል)

አስመራ፤ የአፈጉባኤዋ ጉዞ የአንድ ቻይና ፖሊሲን የሚቃነረን፤ የቻይናንም አንድነት የሚጻረረ ነው ብላች

ኤርትራ፤ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባዔ የታይዋን ጉብኝት ዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ገለጸች።

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፔሎሲን የታይዋን ጉብኝት አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። መስሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ፖሊሲ የማይረባና በግልጽ የወጣ መሆኑን ጠቅሷል።

ዋሸንግተን ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች መሆኑን የገለጸችው አስመራ ይህ ድርጊት አጸያፊ ነው ብላለች።

ኤርትራ የፔሎሲ ጉብኝት ወደ ግጭት የሚያመራና የሚያባብስ እንደሆነም ነው የገለጸችው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ግደለሽነትን የሚያመለክት እንደሆነ ነው የገለጸችው።

አሜሪካ ባለፉት ዓመታት በእስያ የማሳመን ስራ ስትሰራ የቆየችው ይህንን ታይዋንን ጉዳይ ለማሳካት እንደሆነም ነው ኤርትራ ያስታወቀችው።

የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነውም ብሏል የኤርትራ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት።

የአፈጉባኤዋ ጉዞ ድርጊቱ ፤የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም “የአንድ-ቻይና” ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነውም ብሏል የኤርትራ መንግስት።

ኤርትራ፤ የፔሎሲን የታይዋን ጉብኝት ያወገዘች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ናት።

ሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያ ጉብኝቱን ማውገዛቸው ይታወሳል።

News today, Politics

ሶማሊያ የአልሸባብ የቀድሞ ሁለተኛ ቁልፍ ሰውን በሚኒስትርነት ሾመች


የሶማሊያ መንግስት የአልሸባብ መስራች ሙክታር ሮቦ አሊን (አቡ መንሱር) ሚኒስትር አደርጎ ሾሟል
አቡ መንሱር የአልሸባብ የሽበር ቡድን መስራችና በምክትልነት የመራ ሰው ነበረ

አዲሱ የሶማሊያ መንግስት በርካቶችን ያስገረመ አዲስ ከቢኔ ከሰሞኑ ይፋ አድርጓል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ቤሪ የተመራው አዲሱ የሶማሊያ መንግሰት የአልሸባብ የሽብር ቡድን ሁለተኛ ቁልፍ ሰውን በሚኒስትርነት በመሾሙ ነው በርካቶችን ያስገረመው።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ “ከአልሻባብ ጋር እንደራደራለን” አሉ
በትናትናው እለት በሚቃዲሾ በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ልምድ እና ብቃት አላቸው ያላቸውን ሚኒስትሮቻቸውን አስተዋውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ፤ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ “ሶማሊያውያን ከአለም ጋር ስምምነት ላይ ናቸው” በሚለው መርህ ላይ ለመስራት ቃል ገብተዋል።

ከዚህ ሁሉ ግን በርከቶችን ያስገረመው ጉዳይ በቅጽል ስሙ “አቡ መንሱር” በመባል የሚጠራው የአልሸባብ የሽብር ቡድን መስራች እና የቡድኑ ሁለተኛ ቁልፍ ሰው ሙክታር ሮቦ አሊ ሹመት ነበር።

ሙክታር ሮቦ አሊ (አቡ መንሱር) በአዲሱ የሶማሊየ መንግስት ካቢኔ ውስጥ የኃይማኖት ጉዳዮች እና የኢንዶውምንት ሚኒስትር ተደርገው መሾማቸውም ተነግሯል።

ሙክታር ሮቦ አሊ አልሸባብን ለቆ እስከወጣበት የፈረንጆቹ 2011 ድረስ የሽበር ቡድኑ ምክትል መሪ የነበረ ሲሆን፤ የሽብር ቡድኑ ይፋዊ ቃል አቀባይም ነበር።

በፈነረንጆቹ 2017 ላይ እጁን ለሶማሊያ መንግስት የሰጠው አቡ መንሱር፤ በወቅቱ በሰጠው መግለጫ ከቡድኑ ጋር የተለያየው ከ5 ዓመት በፊት እንደነበረ ገልጾ ነበር።

ሶስት የአልሸባብ ቡድን አመራሮችን መግደሉን የኢትዮጵያ መከላከያ አስታወቀ
በፈረንጆቹ 2018 ላይ ደግሞ የደቡብ ምእራብ ሶማሊያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ተወዳድሮ እንደነበረም ይታወሳል።

አዲሱ ሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ቤሪ በቴሌቭዥን በሰጡት አስተያየት፤ አልሸባብን ከመልቀቁ በፊት ለጠቆመው ሰው 5 ሚሊየን ዶላር ሽልማት ተዘጋጅቶበት የነበረው ሰው አሁን ላይ የሶማሊያ ኃይማኖታዊ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኗል ብለዋል።

News today, Politics

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

ሩሲያ፤ ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍም ገልጻለች

ሩሲያ፤ ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍም ገልጻለች።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች።

የሩሲያ ቤተ መንግስት (ክሬምሊን) ቃል አቀባይ፤ ዲሚትሪ ፒስኮቭ ሀገራቸው ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ፒስኮቭ ከሰሞኑ በእስያ ፓስፊክ ባለው ውጥረት ዙሪያም አስተያየት መስጠታቸውን ሩሲያ ቱዴይ ዘጎቧል። ቃል አቀባዩ የእስያ ፓስፊክ ውጥረት ቀላል ግምት ሊሰጠው አይገባም ሲሉም ነው አስተያየት የሰጡት።

የአሜሪካ ምክርቤት አፈጉባዔ በታይዋን ያደረጉት ጉብኝት እንደቀላል መታየት እንደሌለበት ያነሱት ፒስኮቭ ጉዳዩ ከባድ እንደሆነ ገልጸዋል።

የፔሎሲን የቻይና ጉብኝት ተከትሎ የሶስተኛው የዓለም ጦርነት ይነሳል የሚል ፍርሃትን እንዳለ የገለጹት ቃል አቀባዩ፤ ይህ ግን እንደማይከሰት ተናግረዋል።

ፒስኮቭ፤ ሀገራቸው ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍ ተናግረዋል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለባትን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነችም ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

ሩሲያ እና ዩክሬን የጀመሩት ጦርነት አራት ወራት አልፈውታል።

ምዕራባውያን ሩሲያ፤ ዩክሬይንን፤ ቻይና ደግሞ ታይዋንን ትወራለች የሚል ፍርሃት አላቸው።

News today, Technology

አል ዛዋሂሪን የገደሉት እጅግ ዘመናዊና ሚስጥራዊ የአሜሪካ ሚሳኤሎች

እጅግ ዘመናዊ የተባሉት ሚሳኤሎቹ በፕሬዝዳንት ኦባማ ዘመን የተሰሩ ናቸው

 2022/8/2 17:14 GMT

ሚሳዔል አስወንጫፊ የአሜሪካ ድሮን

የአሜሪካ ሚሳኤሎች አልዘዋሪሂን ያለ አንዳች የጎላ የፍንዳታ ድምፅ የገደሉት

መነጋገሪያ ከሆኑ ሰሞነኛ ቀዳሚ የሚዲያ ጉዳዮች መካከል አንዱና ቀዳሚው የአልቃይዳው መሪ አል ዛዋሂሪ መገደል ነው።

የቀድሞው የሽብር ቡድኑ መሪ ኦሳማ ቢን ላደን የቅርብ ሰውና አማካሪ አልዛዋሂሪ በቢላደን እግር ተተክቶ ቡድኑን መምራት ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ሆኖም ላለፉት 20 ገደማ ዓመታት ልክ እን ቢላደን ሁሉ አልዛዋሪን ስታድን የነበረችው አሜሪካ መግደሏን ትናንት ሰኞ አስታውቃለች።

አልዛዋሂሪ በአፍጋኒስታን መገደሉን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ይፋ አድርገዋል።

ሆኖም የ71 ዓመቱ ግብጻዊ ቀዶ ጠጋኝ ሐኪም አገዳደል አሁንም ብዙዎችን እንዳስደመመ ነው። አልዛዋሂሪ ያለ አንዳች ከባድ ፍንዳታ እና የከፋ ጉዳት እንደተገደለ መነገሩም ብዙዎችን ለግርምት ዳርጓል።

ከሞቱ አሟሟቱ እንዲሉም በሁኔታው የተገረሙ ብዙዎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃኑን ጨምሮ ስለሁኔታው እየጠየቁ ነው።

ቁንጮው የሽብር ቡድን መሪ እንዴትና በምን ተገደለ የሚሉ መጣጥፎችን በማስነበብም ላይ ይገኛሉ።

ሰው አልባዎቹን (ድሮን) ጨምሮ ሌሎችም የጦር አውሮፕላኖች ዒላማቸውን የሚያደባዩት እንደ ነጎድጓድ በሚያስገመግም ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፅ ታጅበው ነው የሚለው ዘ ናሽናል አልዛዋሪን የተገደለበት ሚሳኤል ግን ድምፅ አልባ እና ዒላማውን ብቻ ነጥሎ የመታ ነው የሚል ሰፊ ሃተታን ይዞ ወጥቷል።

አልዛዋሪ በመኖሪያ ቤቱ በረንዳ ላይ ሳለ የተገደለበት ሚሳኤል ምንነቱ በውል ባይገለጽም አዲስና የተለየ ነው ሲል የሚያትተው ዘ ናሽናል የጦር ተንታኞች መሳሪያው ምናልባትም ‘በራሪው ጊንሱ’ ወይም

‘R9X Hellfire’ በሚል ከሚታወቁ እጅግ ዘመናዊ የአሜሪካ የሚሳኤል ጦር መሳሪያዎች መካከል አንዱ ሳይሆን እንዳልቀረ መናገራቸውን አስቀምጧል።

መሳሪያው ‘ኒንጃ ሄልፋየር’ የሚል ቅጽል መጠሪያ እንዳለውሞ ነው ሃተታው የሚጠቁመው።

የጦር መሳሪያው ምንነት

‘በራሪው ጊንሱ’ በሚል ይጠራሎል የተባለለት እጅግ ዘመናዊው የሚሳኤል ጦር መሳሪያ ግለሰቦችንና የተለዩ ዓላማዎችን ነጥሎ ለመምታት በማሰብ የተሰራ ነው።

ዒላማውን ነጥሎ ለመምታት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ይነገራል። በመኪና ውስጥ ከሚጓዙ ሰዎች እንኳን አንዱን ብቻ ነጥሎ ለመምታት ያስችላልም ነው የሚባለው።

ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ሌሎች የሚሳኤል ዝርያዎች ቢኖሩም ይኼንኛው ግን የተለየ ስለመሆኑ ይነገርለታል።

መሳሪያው ወደ መሬት ተምዘግዝጎ ዒላማውን የሚመታና 45 ኪሎ ግራም የሚመዝን አረርን እንደሚሸከምም ነው አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን ለዎል ስትሪት ጆርናል የተናገሩት።

ሆኖም አሜሪካ ስለ በራሪው ስለሚባለው ጦር መሳሪያ አንዳችንም ነገር አላለችም። ስለ አሰራሩና ስለ ስሪቱ የተባለ ነገርም የለም።

አልዛዋሪን በመግደሉ ውጥን ንጹሃንን ከጉዳት ለመታደግ የሚያስችል ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረጉን ግን አልሸሸገችም።

ባሳለፍነው ነሐሴ በፈጸመችው ተመሳሳይ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 10 ገደማ ንጹሐን መገደላቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችትንና ውግዘትን ማስተናገዷ ይታወሳል።

በመሆኑም ይህን ተከትሎ አልዛዋሪን ለመግደል ለግለሰባዊ ዒላማዎች በሚል በፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ዘመን እንደተሰራ የተነገረለትን ‘በራሪው ጊንሱ’ን መጠቀሟ ተነግሯል።

የቀድሞው የአል ቃይዳ መሪ ቢን ላደን በፕሬዝዳንት ኦባማ ትዕዛዝ በፈረንጆቹ 2011 በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉ ይታወሳል።

News today, Politics

አይመን አል ዘዋሂሪን ማን ሊተካ ይችላል?

አሜሪካ የአልቃይዳ መሪ አይመን አል ዘዋሂሪ መግደሏን አስታውቃለች

 2022/8/2 7:43 GMT

አይመን አልዘዋሪን ሊተካ ይችላል የተባለው ግብጻዊ ሰይፍ አል ማስሪ

ትውልደ ግብፃዊው አይመን አል ዘዋሂሪ፤ ኦሳማ ቢላደንን በመተካት አል ቃይዳን ሲመራ ነበር

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአልቃይዳ መሪ አይማን አል ዘዋሂሪን እንደተገደለ መናገራቸው ይታወሳል።

 የሽብር ቡድኑ መሪ፤ የአሜሪካ የስለላ ተቋም (ሲአይ ኤ) በፈጸመው የድሮን ተልዕኮ መገደሉን ጆ ባይደን አረጋግጠዋል።

የቀድሞውን መሪ ኦሳማ ቢላደንን በመተካት አል ቃይዳን ሲመራ የነበረው ትውልደ ግብፃዊው አይመን ዘዋሂሪን የተገደለው በአፍጋኒስታን ካቡል መሆኑንም ጆ ባይደን ተናግረዋል።

አይማን አል ዘዋሂሪን የተገደለው የሽብር ቡድኑን ቁልፍ መሪዎችን ኢላማ በማድረግ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት እንደሆነም ተገልጿል።

የአል ዘዋሂሪን መገደልን ተከትሎ በቀጣይ የሽብር ቡድኑን ማን ይችላል በሚል የተለያዩ መላምቶች በመነሳት ላይ ናቸው።

አሁን ላይ እየወጡ ባሉ መረጃዎች ሌላኛው ግብጻዊ ሰይፍ አል ማስሪ ሊተካ እንደሚችል ግምቶች በመውጣት ላይ ናቸው።

ይህ ግብጻዊ በኢራን በረሀማ ስፍራዎች ውስጥ ተሸሽጎ እንዳለ የሚገመት ሲሆን ሟቹ የአልቃይዳ መሪ አይመን አልዘዋሪን ሊተካ ይችላል ተብሏል።

ሰይፍ አል ማስሪ ላለፉት 30 ዓመታት በአልቃይዳ የሽብር ቡድን ውስጥ የተለያዩ ተልዕኮዎችን ሲመራ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የሽብር ቡድኑን ከዚህ በፊት ኦሳማ ቦንላደን በነበሩበት ጊዜ ወደ ነበረበት ቁመና ሊመልሰው እንደሚችል ተሰግቷል።

አልማስሪ በፈረንጆቹ 1998 ናይሮቢ በሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ ላይ የተፈጸመውን እና ለ224 ሰዎች ህይወት ማለፍ ምክንያት የሆነውን የሽብር ድርጊት በመምራት ይፈለጋል።

አሜሪካ ይሄን የሽብር ቡድን መሪ ለያዘ ፣ለገደለ ወይም ለጠቆመ ግለሰብ 7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር እንደምትከፍል ይፋ አድርጋለች።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት፤ አል ቃይዳ መሪ መገደሉ፤ የቱንም ያህል ጊዜ ቢወስድም በመስከረም 11 ጥቃት የተጎዱት ዜጎች ፍትህ ማግኘታቸውን ያመለክታል ብለዋል።

ባይደን፤ የቡድኑ መሪ አይማን አል ዘዋሪ እንዲደመሰስ ላደረጉ የሀገራቸው የጸጥታ ኃይሎች ምስጋና አቅርበዋል።

ባይደን በካቡል በተደረገው ጥቃት ንጹኃን ኢላማ እንዳልተደረጉ ቢገልጹም ታሊባን ግን አጣጥሎታል።

በአፍጋኒስታን የተደረገውንና የአል ቃይዳ መሪ የተገደለበትን ጥቃት ታሊባን አውግዞታል።

የወቅቱ የአፍጋኒስታን ገዥ ታሊባን፤ አሜሪካ ጥቃት ያደረሰችው በመኖሪያ ቤት አካባቢ ነው ብሏል።

News today, Politics

አሜሪካ የአል ቃኢዳን መሪ ካቡል ውስጥ ገደለች

የኦሳማ ቢን ላደንን ሞት ተከትሎ አይማን አል-ዛዋሂሪን አል-ቃይዳን ሲመራ ቆይቷል

2 ነሐሴ 2022, 08:12 EAT

አሜሪካ የአል ቃኢዳውን መሪ አይማን አል-ዛዋሂሪን በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል ውስጥ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት መግደሏን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስታወቁ።

የአሜሪካ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሲአይኤ ባለፈው ዕሁድ ካቡል ውስጥ ባካሄደው የፀረ-ሽብር ዘመቻ ላይ ነው ዛዋሂሪን መግደል የቻለው ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ባይደን አይማን አል-ዛዋሂሪ “በአሜሪካ ዜጎች ላይ ግድያ እና ጥቃትን የቀረጸ ሰው ነው’’ ብለዋል።

አክለውም “አሁን ፍትህ ተሰጥቷል ፤ ይህ የአሸባሪ ቡድን መሪ ከዚህ በኋላ በሕይወት የለም” ሲሉም ግድያውን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል።

ዛዋሃሪ ከቀድሞው የአል-ቃኢዳ መሪ ቢን ላደን ጋር በመሆን ከ20 ዓመታት በፊት የተፈጸመውን የ9/11 ጥቃትን የመራ ሲሆን፣ አሜሪካ ለረጅም ዓመታት ስታፈላልገው የቆየችው የሽብር ቡድኑ መሪ ነው።

አይማን አል-ዛዋሂሪ የኦሳማ ቢን-ላደን ሕልፈትን ተከትሎም አል-ቃኢዳን ሲመራ ቆይቷል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት እንዳሉት ዛዋሂሪ በአንድ በጥብቅ በሚጠበቅ ቤት በረንዳ ላይ ተቀምጦ ባለበት ወቅት ነው የአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን ሁለት ሚሳኤሎችን ተኩሶ የገደለው።

እንዲሁም በቤቱ ውስጥ የነበሩ ሌሎች የቤተሰብ አባላት ምንም ጉዳት እንዳልደረሰባቸው እና በጥቃቱ ዛዋሂሪ ብቻ ተነጥሎ መገደሉንም አክለው ተናግረዋል።

ባይደን በ71 ዓመቱ የአል ቃኢዳ መሪ ላይ እርምጃውን ለመውሰድ ለወራት ዕቅድ ከወጣ በኋላ “የተመጠነ እና ትክክለኛውን ኢላማ የመታ ጥቃት” እንዲሰነዘር የመጨረሻውን የይለፍ ፍቃድ መስጠታቸውን ተናግረዋል።

የሽብር ቡድን መሪው ግድያም እ.ኤ.አ. በ2001 በተፈጸመው ጥቃት 3,000 የሚጠጉ ወዳጅ፣ ቤተሰቦቻቸውን ላጡ አሜሪካዊያን ለሐዘናቸው መልስ የሚሆን የመጨረሻውን መደምደሚያ የሚሰጥ እርምጃ ነውም ሲሉ አክለዋል።

“የቱንም ያህል ጊዜ ይፍጅ፣ የትም ይደበቁ፣ ለሕዝባችን ስጋት የሆነ አካል ካለ አሜሪካ ታገኛቸዋለች፣ ቀጥሎም ታስወግዳቸዋለች” ያሉት ባይደን አክለውም “አገራችንን እና ሕዝባችንን ከመከላከል ወደ ኋላ አንልም” ሲሉም አክለዋል።

ባይደን ዛዋሂሪ እ.ኤ.አ በጥቅምት 2000 በኤደን የአሜሪካ የባሕር ኃይል ግዙፍ የጦር መርከብ ላይ በተሰነዘረ የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃት 17 የአሜሪካ መርከበኞችን የገደለውን ጥቃት መርቷል ሲሉ ተናግረዋል።

እንዲሁም ለ223 ሰዎች ሕልፈት ምክንያት የሆኑት በ1998 በኬንያ እና በታንዛኒያ በአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ የተፈፀሙትን ጥቃቶችንም በማስተባበር ዛዋሂሪ ኃላፊነት እንዳለበትም አክለዋል።

ፕሬዝዳንት ባይደን አፍጋኒስታን ከእንግዲህ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ አትሆንም ሲሉም አጥብቀው ተናግረዋል።

የታሊባን ቃል አቀባይ የአሜሪካን ዘመቻ ዓለም አቀፍ መርሆችን የጣሰ ነው ሲሉ ገልፀውታል።

አክለውም “እንዲህ ያሉ ድርጊቶች ላለፉት 20 ዓመታት ያልተሳኩ ሙከራዎችን መደጋገም ናቸው። ድርጊቱም የአሜሪካን፣ የአፍጋኒስታንን ብሎም የቀጠናውን ጥቅም ጥቅም የሚፃረር ነው’’ ብለዋል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት በበኩላቸው በአል ዛዋሂሪ ላይ የተካሄደው ዘመቻ ሕጋዊ መሰረት ያለው ነው ብለዋል።

News today

በአሜሪካ የተገደለው ግብጻዊው ዶክተር እና የአል ቃኢዳ መሪ ማን ነበር?

አይማን አል-ዛዋህሪ

2 ነሐሴ 2022, 11:17 EAT

አፍጋኒስታን ውስጥ በአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት የተገደለው አይማን አል-ዛዋህሪ የአል ቃኢዳ ርዕዮተ ዓለም ዋና ጠንሳሽ ተብሎ ይጠራ ነበር።

ግብጻዊ ነው። የግብጽን እስላማዊ ጂሃድ ታጣቂ ቡድን ለመመስረትም ድጋፍ በማድረግ ይታወቃል።

አል-ዛዋህሪ የዓይን ቀዶ ሕክምና ባለሙያ ነው። እአአ ግንቦት 2011 የአሜሪካ ጦር ኦሳማ ቢን ላደን መገደሉን ተከትሎ የአል ቃኢዳ መሪ ሆነ።

ከዚያ በፊት አል-ዛዋህሪ የቢን ላደን ቀኝ እጅ እንደሆነ ይቆጠር ነበር። አንዳንድ ባለሙያዎች መስከረም 1/2001 በዩናይትድ ስቴትስ ከደረሰው ጥቃት ጀርባ የሚገኝ “ዋና ሰው” እንደሆነ ይታመናል።

የአሜሪካ መንግስት በአውሮፓውያኑ 2001 “በጣም የሚፈለጉ አሸባሪዎች” ብሎ ከዘረዘራቸው 22 ሰዎች አንዱ ነው።  በቢንላደን ብቻ ተቀድሞ አል-ዛዋህሪ ቁጥር ሁለት ላይ ተቀምጧል። አሜሪካ ያለበትን ለጠቆመ 25 ሚሊየን ዶላር እሸልማለሁ ብላ ነበር።

ከጥቃቶቹ በኋላ በነበሩት ዓመታት አል-ዛዋህሪ የአልቃኢዳ ዋነኛው ቃል አቀባይ ሆኖ ብቅ አለ። በ2007 ብቻ 16 ቪዲዮዎችን እና የድምጽ መልዕክቶችን አስተላልፏል። ይህ ከቢንላደን በአራት እጥፍ የሚበልጥ ቁጥር ነው።

ትኩረቱንም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሙስሊሞችን አክራሪ ለማድረግ እና ለመመልመል መሞከር ነበር።

ከቀናት በፊት በካቡል በተፈጸመ ጥቃት ነው አይማን አል-ዛዋህሪ የተገደለው። አሜሪካ ግለሰቡን ለማጥቃት ስትሞክር ግን የመጀመሪያዋ አልነበረም።

ጥር 2006 ፓኪስታን ከአፍጋኒስታን ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አካባቢ አሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት ዒላማዋ አድርጋው ነበር።

ጥቃቱ አራት የአልቃይዳ አባላትን ገድሏል። አል-ዛዋህሪ በሕይወት ተርፎ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ታየ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽም ሆኑ “በምድር ላይ ያሉ ኃያላን” ሞቱን “በአንድ ሰከንድ” ሊያቀርቡት እንደማይችሉ አስጠነቀቀ።

ከተከበረ ቤተሰብ የተገኘው ዶክተር

አይማን አል-ዛዋህሪ  በአውሮፓውያኑ ሰኔ 19 ቀን 1951 በግብጽ ርዕሰ መዲና ካይሮ ተወለደ። የተገኘው ከተከበሩ ሐኪሞች እና ምሁራን ቤተሰብ ነው።

አያቱ ራቢያ አል-ዛዋህሪ በመካከለኛው ምስራቅ የሱኒ እስላማዊ ትምህርት ማዕከል በሆነው የአል-አዝሃር ኢማም ነበሩ። አንዱ ከአጎቱ የአረብ ሊግ የመጀመሪያው ዋና ጸሐፊ ሆነው አገልግለዋል።

አይማን አል-ዛዋህሪ በትምህርት ቤት እያለ በፖለቲካዊ እስልምና ውስጥ ተሳትፏል። ህገ-ወጥ በሆነው የሙስሊም ወንድማማቾች አባል በመሆኑ በ15 ዓመቱ ለእስር በቅቶ ነበር። ይህ የግብጽ ትልቁ እስላማዊ ድርጅት ነው።

የፖለቲካ ዝንባሌው በካይሮ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምህርት ቤት ሕክምናን ከመማር አላገደውም። በ1974 ተመረቀ። ከአራት ዓመት በኋላ ደግሞ በቀዶ ሕክምና ሁለተኛ ዲግሪውን አግኝቷል።

በ1995 ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አባቱ መሐመድ በዚሁ ትምህርት ቤት የፋርማኮሎጂ መምህር ነበሩ።

አክራሪው ወጣት

አይማን አል-ዛዋህሪ መጀመሪያ የቤተሰቡን ዱካ ተከተለ። በካይሮ አካባቢ የህክምና ክሊኒክ ከፈተ። ብዙም አልገፋበትም። በኋላም የግብጽን መንግሥት ለመጣል በሚጥሩ አክራሪ እስላማዊ ቡድኖች ተማረከ።

በአውሮፓውያኑ 1973 የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ ተመሠረተ። አል-ዛዋህሪም ተቀላቀለ።

የቡድኑ የወታደር ልብስ ለብሰው ፕሬዝዳንት አንዋር ሳዳትን በካይሮ ወታደራዊ ትርኢት ላይ ገደሏቸው። ይህን ተከትሎም እአአ በ1981 ላይ ከበርካታ ተጠርጣሪ የቡድኑ አባላት ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ። ሳዳት ከእስራኤል ጋር የሠላም ስምምነት በመፈራረማቸው በቡድኑ ዘንድ ቁጣ ተቀሰቀሰ። ቀደም ሲልም የጸጥታ ሃይሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የፕሬዝዳንቱን ተቺዎች ማሰራቸው ቂም ፈጥሮ ነበር።

በጅምላ ችሎቱ ወቅት አል-ዛዋህሪ የተከሳሾቹ መሪ ሆኖ ቀርበ። “እኛ በዲናችን የምናምን ሙስሊሞች ነን። እስላማዊ መንግሥት እና እስላማዊ ማህበረሰብ ለመመስረት እየጣርን ነው” ሲል ለፍርድ ቤቱ ሲናገር ተቀርጿል።

በሳዳት ግድያ ውስጥ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንደሌለው ተገለጸ። ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በመያዝ ተከሶ ግን ሦስት ዓመት እስራት ተላለፈበት።

ቢን ላደን እና አይማን አል-ዛዋህሪ

እንደ እስላማዊ እስረኞች ገለጻ ከሆነ አል-ዛዋህሪ በግብጽ እስር ቤት በባለስልጣናት አዘውትሮ ይሰቃይና ይደበደብ ነበር። ይህም አክራሪ እንዲሆን አድርጎታል ተብሏል። 

በ1985 ከእስር የተፈታው አይማን አል-ዛዋህሪወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀና።

ሳዑዲ ብዙም አልቆየም። ወደ ፓኪስታኗ ፔሻዋር አመራ። ቀጥሎ ወደ ጎረቤት አፍጋኒስታን አቀና። በሶቪየት ወረራ ወቅት በሐኪምነት ከመስራት ጎን ለጎን የግብጽ እስላማዊ ጂሃዳዊ አንጃን አቋቋመ።

የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ በ1993 እንደገና ሲያንሰራራ አል-ዛዋህሪ መሪነቱን ተረከበ። ቡድኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አጢፍ ሲድቂን ጨምሮ በግብጽ ሚኒስትሮች ላይ ተከታታይ ጥቃት ሰነዘረ። እሱም የጥቃቶቹ ቁልፍ ሰው ነበር።

በ1990ዎቹ አጋማሽ ቡድኑ መንግሥትን ለመጣል እና እስላማዊ መንግሥት ለመመስረት ዘመቻ አካሄደ። ይህም ከ1 ሺህ 200 በላይ ግብጻውያንን ለህልፈት ዳርጓል።

እአአ በ1997 የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዲፓርትመንት የቫንጋርድስ ኦፍ ኮንክሰስ ቡድን መሪ ነው ሲል ሰይሞታል። ይህ የእስልምና ጂሃድ ቡድን በዛው ዓመት በሉክሶር ከተካሄደው የውጭ ቱሪስቶች እልቂት ጀርባ ነበር።

ከሁለት ዓመት በኋላ በሌለበት በግብጽ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የሞት ፍርድ ተላልፎበታል። በቡድኑ ጦሩ ላይ ባደረሰው በርካታ ጥቃቶች ሚና ነው ውሳኔው የተላለፈበት።

ምዕራባውያን ዒላማዎች

አይማን አል-ዛዋህሪ እአአ በ1990ዎቹ ለሐይማኖታዊ እና የገንዘብ ድጋፍ ፍለጋ በዓለም ዙሪያ ተዘዋውሯል ተብሎ ይታሰባል።

ሶቪዬት አፍጋኒስታንን ለቃ ከወጣች በኋላ በነበሩት ዓመታት በቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ስዊዘርላንድ ይኖር ነበር። አንዳንዴ ሐሰተኛ ፓስፖርት በመጠቀም ጭምር ወደ ባልካን፣ ኦስትሪያ፣ የመን፣ ኢራቅ፣ ኢራን እና ፊሊፒንስ  ተጉዞ እንደነበር ይገመታል።

በታህሳስ 1996 ደግሞ ቺቺኒያ ውስጥ ህጋዊ ቪዛ ሳይኖረው ተይዞ ለስድስት ወራት ያህል በሩሲያ እስር ቤት እንደቆየ ይነገራል።

በአይማን አል-ዛዋህሪ  ተጽፏል በተባለው ጽሑፍ መሠረት የሩሲያ ባለስልጣናት በኮምፒዩተሩ ላይ የነበሩ አረብኛ ፅሁፎችን መተርጎም ባለመቻላቸው ማንነቱን በሚስጥር መያዝ ችሏል።

አይማን አል-ዛዋህሪ

እአአ በ 1997 አል-ዛዋህሪ ኦሳማ ቢን ላደን ወደከተመባት አፍጋኒስታኗ ጃላላባድ ከተማ እንዳቀና ይታመናል።

ከአንድ ዓመት በኋላ የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ የቢን ላደኑን አልቃይዳን ጨምሮ ሌሎች አምስት አክራሪ እስላማዊ ታጣቂ ቡድኖችን በመቀላቀል በአይሁዶች እና በመስቀል ጦረኞች ላይ የዓለም እስላማዊ ጂሃድን መሠረተ።

የቡድኑ የመጀመሪያ አዋጅ የአሜሪካ ዜጎችን መገደል የሚፈቅደውን ፈትዋ ወይም ሃይማኖታዊ ድንጋጌን ያካትታል። ከስድስት ወራት በኋላ በኬንያ እና በታንዛንያ የሚገኙት የአሜሪካ ኤምባሲዎች በተመሳሳይ ወቅት ጥቃት ተፈጽሞባቸው 223 ሰዎች ሞቱ።

ከሴራው ጀርባ ቢንላደን እና አልቃኢዳ መኖራቸውን ለማረጋገጥ ከተወሰዱት ነገሮች አንዱ የአል-ዛዋህሪ የሳተላይት የስልክ ንግግር  ነበር።

ጥቃቱ ከተፈጸመ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ በአፍጋኒስታን የሚገኘውን የቡድኑን ማሰልጠኛ ካምፖች በቦምብ ደበደበች። በማግስቱ አይማን አል-ዛዋህሪ ለአንድ የፓኪስታን ጋዜጠኛ ደውሎ “የቦምብ ፍንዳታው፣ ዛቻው እና ጥቃቱ አያስፈራንም። ጦርነቱ ገና አሁን መጀመሩን ለአሜሪካ ንገራት” ብሎ ነግሮታል።

ከቢንላደን ሞት በኋላ በነበሩት ዓመታት የአሜሪካ የአየር ጥቃት የአል-ዛዋህሪ ምክትሎች ለመግደል አስችሏታል። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበረ አቅሙን አዳክሞታል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ አል-ዛዋህሪ ሩቅ እና የተገነጠለ ሰው ሆነ ነበር። መልዕክቶችንም አልፎ አልፎ ብቻ ነበር የሚሰጠው።

አሜሪካ ባለፈው ዓመት ከአፍጋኒስታን የወጣችበት መንገድ በግርግር እና በጥድፊያ የተሞላ ነበር። እስላማዊ መንግሥት ያሉ አዳዲስ ቡድኖች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጽዕኖ እያሳደሩ በመሆናቸው አል-ዛዋህሪ ብዙም ስልጣን አሜሪካ መሞቱን እንደ ድል ታበስራለች።

አልቃኢዳ አዲስ መሪ ይፋ እንደሚደረግ ምንም ጥርጥር የለውም። አዲሱ መሪ ግን አይማን አል-ዛዋህሪ ያነሰ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል።

News today, Politics

የቻይና ጦር የአፀፋ እርምጃ ለመውሰድ በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆኑን ገለፀ

P.R.C


የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት የቻይናን ዛቻ ወደጎን ትተው የታይዋን ጉብኝታቸውን ጀምረዋል

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር የአፀፋ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆኑን አስታወቀ።

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ወ ዩ ኪያን፤ የቻይና ጦር የሀገሪቱን ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ ነው ብለዋል።

“የአሜሪካ ፖለቲከኞች የ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሕዝብ ጠላት መሆን አምሯቸዋል”- ቻይና
ቃል አቀባዩ የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የቻይና አካል በሆነችው ታይዋን ክልል ለጉብኝት መግባታቸውን ተከትሎ የቻይና ጦር በተመረጡ ኢላማዎች ላይ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።

የአሜሪካ አፈ ጉባኤ ናንሲ ሌሎሲ ታይዋንን ጨምሮ አምስት የእስያ ሀገራትን ጉብኝት መጀመራቸውን ተከትሎ ዓለም አይኑ ታይዋን ላይ አርፏል።

የአሜሪካዋ አፈጉባዔ የጉብኝታቸው አካል ወደሆነችው ታይዋን በዛሬው እለት ገብተዋል።

ቻይና በአሜሪካ ፖለቲካ ሶስተኛው የስልጣን ባለቤት እየሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷን ተከትሎ በሩቅ ምስራቅ ውጥረት ነግሷል።

ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ አወጀች
አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን መድረሳቸውን ተከትሎም የቻይና ሱ35 ጄቶች የታይዋንን የአየር ክልል ጥሰው መግባታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

ቻይና፤የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ”ቻይና ማስጠንቀቂያ አስተላልፋ እንደነበረ ይታወሳል።

News today, Politics

ፑቲን የኒዩክለር ጦርነት በየትኛውም መንገድ ቢሆን መቅረት እንዳለበት

ፑቲን የኒዩክለር ጦርነት በየትኛውም መንገድ ቢሆን መቅረት እንዳለበት አሳሰቡ
ፑቲን ሁሉም ሀገራት ኒውክለርን ለሰላማዊ ዓላማ እንዲጠቀሙ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባም ጥያቄ አቅርበዋል

የኒውዩክለር ጦርነትን በማንኛውም ዋጋ ቢሆን ማስወገድ እንደሚገባ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሳሰቡ።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከል ላይ ባተኮረው ጉባዔ ላይንግግር ማድረጋቸውን የሀገራቸው መገናኛ ብዙኃን አርቲ ዘግቧል።

ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ የሩሲያ “ዋነኛ ስጋት” ነች ሲሉ ፈረጁ
በቀጣይ ኒውክለርን በመጠቀም የሚረግን ጦርነት በየትኛውም መልኩ ማስቀረት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኒውክለር ጦርነት አሸናፊ የሌለውና ዓለም በፍጹም ሊሄድበት የማይገባ እንደሆነም ነው ቭላድሚር ፑቲን ያሳሰቡት።

ፑቲን ሀገራቸው ከአሜሪካ ለገባችውን ኒውክለርን ያለመታጠቅ ስምምነት እንደምትታመንም የገለጹት።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከልን የሚተገብሩ ሁሉም ሀገራት ኒውክለርን ለሰላማዊ ዓላማ እንዲጠቀሙ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባም ጥያቄ አቅርበዋል።

የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እንዴት ሊጠናቀቅ ይችላል?
የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከል ውል ዓላማዎች ስርጭቱን መግታት፣ አለመታጠቅና ለሰላማዊ ኃይል መጠቀም የሚሉትን ያጠቃልላል።

ይህንን ስምምነት 192 ሀገራት የተቀላቀሉት ሲሆን ኒውክለር የታጠቁትም በዚህ ስምምነት ውስጥ ተሳታፊ ናቸው።

ፕሬዝደንት ቫላድሚር ፑቲን አሜሪካን ዋነኛ የሩሲያ ጠላት እንደሆነች ትናንት የሀገራቸው የባሕር ኃይል ቀን ሲከበር ይፋ አድርገዋል።

News today, Politics

የቻይና ጦር ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ


ፕሬዝዳንት ባይደንና የቻይና ሺ ጂንፒንግ በታይዋን እና በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ጉዳይ ይወያያሉ

በታይዋን ጉዳይ አለመግባባት ውስጥ ያሉት የአሜሪካ እና ቻይና ፕሬዝዳንቶች ውይይት ሊያደርጉ መሆኑ ተገለጸ።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በታይዋን እና በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ላይ ትኩረት ያደረገ ንግግር እንደሚያደርጉም ነው የተገለጸው፡፡

የአሜሪካዋ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ቻይና አስጠነቀቀች
ሁለቱ መሪዎች ነገ ከአራት ወራት በኋላ በስልክ ንግግር እንደሚደርጉ አንድ ከፍተኛ የዋሸንግተን ባለስልጣን መናገራቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

የአሜሪካዋ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ከሰሞኑ ታይዋንን እንደሚጎበኙ መግለጻቸውን ተከትሎ ቤጅንግ ቁጣዋን ገልጻለች፡፡

ከዚህ ባለፈም ቻይና አፈጉባዔዋ ወደ ታይዋን የሚሄዱ ካልሆነ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር፡፡

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የስልክ ውይይት ያደርጋሉ የተባለው በዚህ ውጥረት ውስጥም ሆነው እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የመሪዎቹን የስልክ ንግግር አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበለት የቻይና ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በታይዋን ጉዳይ ላይ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚወያዩ ቢጠበቅም በአውሮፓ ያለው ወታደራዊ ሁኔታም የውይይታቸው አካል እንደሚሆን ተገምቷል፡፡

ቻይና በታይዋን ጉዳይ ለአሜሪካ ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጠች
መሪዎቹ በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ላይ ትኩረት ያደረገ ንግግር ይኖራቸዋል ተብሎ የተጠበቀ ሲሆን በእስካሁኑ ሂደት ዋሸንግተን ከዩክሬን፤ ቤጅንግ ደግሞ ከሩሲያ ጎን መሆናቸው ይታወሳል፡፡

የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ፤ ሁለቱ መሪዎች በኢኮኖሚ ውድድር ላይም ይነጋገራሉ ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ባይደን ከቻይናው አቻቸው ጋር ነገ ውይይት የሚያደርጉት ከኮሮና ቫይረስ ካገገሙ በኋላ ነው፡፡

News today, Politics

ኢራን የእስራኤልን የስለላ ኔትወርክ መያዟን አስታወቀች


ኢራን የስለላ ቡድኑ አባላት መረጃ ሲሰበሰቡ እና ጸረ -ኢራን የሆነ ፕሮፖጋንዳ ሲጽፉ ነበር ብላለች

የኢራን የደህንነት ድርጅት እንዳስታወቀው ኢራን ወሳኝ በሆኑ ዘርፎች ላይ መረጃ ለመሰብሰብ ሲንቀሳቀስ የነበረ የእስራኤል የስለላ ኔትዎርክ ይዛለች።

በቴህራን ያለው የአል ዓይን ኒውስ ጋዜጠኛ ያየው የኢራን የደህንነት ድርጅት መግለጫ፣ የእስራኤሉ ሞሳድ አካል የሆነው መረብ ተበጥሷል፤ኪሳራም ደርሶበታል ብሏል።

መግለጫው የስለላ ቡድኑ አባላት ከእስራኤል ጋር የመስራት ታሪክ ካለው የተገንጣይ ቡድን አመራር ከሆኑት መካከል በአንዱ አማካኝነት ከሞሳድ ኃላፊ ጋር መገናኘታቸውን ጠቅሷል።

ከዚህ በተጨማሪም የስለላ ቡድኑ አባት መረጃ ሲሰበስቡ፣ የጦር መሳሪያ ስልጠና ሲወስዱ እንዲሁም ጸረ ኢራን የሆነ የፕሮፖጋንዳ መፈክር ሲጽፉ ነበር ብሏል መግለጫው።

የኢራን የደህንነት ሚኒስቴር የታሰሩት እነማን እንደሆኑ፣የየት ሀገር ዜጎች እንደሆኑ እና የት እንደታሰሩ ግልጽ አላደረገም።

ደህንነቱ ባለፈው ሳምንት ወሳኝ የሆነ ተቋም ላይ ጉዳት ሊያደርሱ የነበሩ የእስራኤል የስለላ መረብ መያዙን ባለፈዉ ቅዳሜ ገልጾ ነበር።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ “ይህ የስለላ ኔትወረክ በሰሜን ኢራን በሚገኘው የኩርዲስታን ግዛት በኩል ወደ ኢራን ገብቷል፤ ፍንዳታ ለማድረስ የሚያስችል ዘመናዊ መሳሪያ ታጥቀው የነበሩት የኔትውኩ አባላት በክትትል ተይዘዋል።”

ነገርግን የኩርዱ ኮምላ የተባለው ፖርቲ አባላቱ ከእስራኤሉ ሞሳድ ጋር ግንኙነት አላቸው የሚለውን ክስ አስተባብለዋል

News today, Politics

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው ከአሜሪካ ጋር ለሚደረግ ማንኛውም ወታደራዊ ግጭት ዝግጁ መሆኗን በልበሙሉነት ተናገሩ፡፡

ሮይተርስ ዮንሃፕ የዜና አገልግሎትን ጠቅሶ እንደዘገበው ፤ ኪም የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ዮን ሶክዬኦል እና ሰራዊታቸው “አደገኛ” ሙከራዎችን ካደረጉ የመጥፋት አደጋ ሊደርስባቸው እንደሚችልም አስጠንቅቋል።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል።

ሰሜን ኮሪያ ሩሲያ ቀደም ሲል በተባበሩት መንግስታት ያቀረበቸውንና መጋቢት በነበረው የተመድ  ጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ውድቅ የተደረገውን የ“አሜሪካ በዩክሬን ውስጥ ባዮሎጂካል የጦር መሳሪያ ትሰራለች” ክስም አቅርባለች፡፡

የሞስኮ አጋር የሆነችው ፒዮንግያንግ፤ ዋሽንግተንን “የሰው ልጅን ለጥፋት የሚወረውር የባዮ ሽብርተኝነት መጥፎ ስፖንሰር” እና በ1950ዎቹ በኮሪያ ጦርነት ወቅት “የባክቴሪያ ጦርነት” ያደረገች ሀገር ናት ስትልም ወቅሳለች፡፡

ይህንን መሰል ወቀሳዎች ከሰሜን ኮሪያ በተጨማሪ ቻይና እና ሩሲያ ደጋግመው ሲሉት የሚደመጡ ቢሆንም በዋሽንግተን ግን ይህንን ስታስተባብል ትስተዋላለች።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፤ ከሁለት ወራት በፊት የሰሜን ኮሪያ ጦር ሃይሎች ምስረታ ቀንን ምክንያት በማድረግ ባደረጉት ንግግር ከእኛ ጋር ግጭት ውስጥ ለመግባት የሚፈልግን ማንኛውንም ሀገር “እናጠፋለን” ሲሉ መዛታቸው የሚታወስ ነው፡፡

ማንኛውም ሀገር ሰሜን ኮሪያ ከነካ አጸፋው የከፋ እንደሚሆን ያስጠነቀቁት ኪም ጆንግ ኡን፤ ፒዮንግያንግ አሁንም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እድገትን ለማፋጠን ጠንክራ ትሰራለች ሲሉም ተደመጠዋል፡፡

ኪም “በማንኛውም ጊዜ ሪፐብሊኩ የጣለባችሁን ኃላፊነት የተሞላበት ተልእኮ እና ልዩ መከላከልን ለመፈጸም ዝግጁ መሆን አለባችሁ” የሚል መልእክት ለኒውክሌር ኃይል ማስተላለፈቻውም ነበር የሰሜን ኮሪያ የዜና አገልግሎት ኤጀንሲ በወቅቱ የዘገበው።

እናም አሁን አሜሪካ በዩክሬን ምድር ባዮሎጂካል መሳሪያዎችን እያመረተች ትገኛለች የሚሉት ኪም፤ ከአሜሪካ ጋር ግጭት እንዳይገቡ እጅጉን ተሰግቷል፡፡

ሩሲያ በየካቲት ወር መጨረሻ በዩክሬን ላይ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ማካሄድ የጀመረችው፤ ዋሽንግተን በዩክሬን ውስጥ ባዮሎጂካል መሳሪያዎችን ለማምረት ለምርምር የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች የሚል ክስ ማቅረብ ከጀመረች በኋላና ወደፊት በሩሲያ ላይ ሊጋረጡ የሚችሉ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል በሚል እንደነበር አይዘነጋም፡፡

News today, social life

ሩሲያ ለኢትዮጵያ 162 ሚሊዮን ዶላር ብድር መሰረዝዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሩሲያ ለኢትዮጵያ 162 ሚሊዮን ዶላር ብድር መሰረዝዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ያጎለብተዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ከሶቭየት ህብረት የተበደረቻቸውን ብድሮች መሰረዟን በይፋ አሳውቃለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ከሶቭየት ህብረት ወይም አሁን ላይ ሩሲያ ተብላ ከምትጠራው ሀገር 162 ሚሊዮን ዶላር የተበደረችውን ገንዘብ ሰርዛለች ያሉት አምባሳደር መለስ በብድር መልክ ሊከፈል የነበረው ገንዘብ ለምን አገልግሎት መዋል እንዳለበትም ሁለቱ ሀገራት ተስማምተዋልም ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለሩሲያ በብድር መልክ ልትከፍለው የነበረው 162 ሚሊዮን ዶላር ባልቻ ሆስፒታልን እና መልካ ዋከና የሀይል ማመንጫ ጣቢያ ለማዘመን እንዲውል መስማማታቸውም ተገልጿል።

ቃል አቀባዩ አቶምባሳደር መለስ በመግለጫቸው አክለውም፣ በኢትዮጵያ በህገወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች ምዝገባ መጀመሩን እና እስካሁን 60 ሺህ ሰዎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በእስካሁኑ ምዝገባ የካናዳ፣ አሜሪካ፣ኮንጎ፣ ናይጀሪያ ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ኤርትራ ፣ሱዳን፣ቻይና፣ ቡሩንዲ ጋና፣ ህንድ፣ ባንግላዲሽ፣ ላይቤሪያ፣ ጣልያን እና የካሜሩን ዜግነት ያላቸው ህገወጥ ሰዎች መገኘታቸው ተገልጿል።

በዚህ ምዝገባ የተካተቱት በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቪዛ ጊዜያቸው የለፈበት፣ በህጋዊ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ፣ የስደተኝነት ፈቃድ የሌላቸው እና ፈቃድ ለማግኝት በሂደት ላይ ያሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች ናቸው ተብሏል።

ዲፕሎማቶች፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና ህጋዊ ቪዛ ያላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች በምዝገባው እንደማይካተቱም ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

ህገወጥ የውጭ ሀገራትን የመመዝገብ ስራው በአዲስ አበባ 21 ቦታዎች፣ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፎች ሰበታ፣ ቡራዩ፣ ሆለታ፣ሱሉልታ፣ ለገጣፎ፣ ገላን እና ዱከም ከተሞች እየተመዘገቡ እንደሆነ ተገልጿል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ግብጽን ከጎበኙ በኋላ በካይሮ ስለ ህዳሴው ግድብ ተናገሩት ተብሎ የወጣውን መረጃ የሶማሊያ መንግሥት አቋም እንዳልሆነ ኢትዮጵያ ትረዳለችም ሲሉ አምባሳደር መለስ በመግለጫቸው ተናግረዋል።

በግብፅ ብዙሃን መገናኛዎች የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ከግብጽ አቻቸው ጋር በጋራ ሆነው ተናገሩት ተብሎ የወጣው ዘገባ የአንድ ወገን አስተያየት ነው፣ በመሆኑም የሶማሊያ መንግስት በይፋ ስለ ህዳሴው ግድብ ያወጣው መግለጫ እንደሌለም ተገልጿል።