News today, Politics, social life

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጣለች

የሞስኮ ማዕቀብ ካናዳ ከዚህ በፊት በሩሲያዊያን ላይ ለጣለችው ማዕቀብ የአጸፋ እርምጃ ነው ተብሏል

ሩሲ እና ካናዳ

ሩሲያ ካናዳዊያን ዲፕሎማቶች፣ የሀይማኖት መሪዎች፣ ፖለቲከኞችና ምሁራን ላይ ነው ማዕቀብ ጣለችው

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታውቃለች።

ሩሲያ ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ወደ ይፋዊ ጦርነት የገባችው።

 ይሄንን ጦርነት ተከትሎም በሩሲያ ላይ ከ6 ሺህ በላይ ማዕቀቦች ሲጣልባት ከ400 በላይ ዲፕሎማቶቿ ደግሞ ከተለያዩ ሀገራት ተሰናብተዋል።

ካናዳም የሩሲያ ዲፕሎማቶችን ከማባረሯ ባለፈ በሩሲያ ጋዜጠኞች ፣ ባለሀብቶች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

የሩሲያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ካናዳ ለወሰደችው ማዕቀብ ምላሽ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

ይህ ማዕቀብ የተጣለባቸው ካናዳዊያን ወደ ሩሲያ እንዳይገቡ እና በሩሲያ ያላቸው ሀብት እንዳይንቀሳቀስ እንደሚደረግ ሮይተርስ ዘግቧል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በሀገሪቱ እንዲሁም በተቋማቶቿ እና ባለሃብቶቿ ላይ ማዕቀብን ጨምሮ የተለያዩ እገዳዎችን የጣሉ እርምጃዎቹን የደገፉ ሀገራትን “ወዳጅ አይደሉም” ማለቷ ይታወሳል።