News today, Politics

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ

በጥቃቱ ከ265 የሚልቁ ሰዎችም ቆስለዋል ተብሏል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት

ከሟቾች መካከል ሁለት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን አመራሮች ይገኙበታል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ።

በየጊዜው ግጭት ውስጥ የሚገቡት እስራኤል እና ፍልስጥም አሁንም መልሰው ግጭት ውስጥ ገብተዋል።

የእስራኤል ጦር ባሳለፍነው ሰኞ የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን መሪ የሆኑት ባሳም አልሳዲን በዌስት ባንክ ማሰራቸውን ተከትሎ በጋዛ አውዳሚ ግጭት ተቀስቅሷል።

በጋዛ ሰርጥ ውስጥ እየተካሄደ ባለው በዚህ ጦርነት እስራኤል በተኮሰቻቸው የሮኬት ጥቃቶች የሞቱ ሰዎች ቁጥር 32 መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።

ከ265 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ዘገባው አክሏል።

ከሟቾች ውስጥ ስድስቱ ህጻናት ሲሆኑ አራቱ ደግሞ ሴቶች እንደሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የሟቾች እና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተጠቅሷል።

የእስራኤል ጦር የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን ምክትል መሪ ካሊድ ማንሱርን በጋዛ ሰርጥ በሮኬት ጥቃት መግደሏን አስታውቃለች።

የእስራኤል ጦር በፍልስጤም ጋዛ እንደሚንቀሳቀስ የተገለጸው የእስልሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን የሚለውን ለመስማት በሚል የተኩስ አቁም አውጇል።

የፍልስጤም ጤና ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ እስራኤል የምትተኩሳቸው የሮኬት ጥቃቶች ንጹሀንን እየገደለ መሆኑን ገልጿል።