News today, Politics

ሰሜን ኮሪያ ጥላትን ለማሳሳት በማለት 8 አንድ አይነት ቤተመንግሥት ሰራች


2022/8/29 11:38 GMT

ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን

ቤተ መንግስቶቹ ተመሳስለው የተገነቡት ፕሬዝዳንቱ ያሉበት እንዳይታወቅ እንደሆነ ተገልጿል

ከምዕራባዊያን ጋር እሰጣ አገባ ውስጥ ያለችው ሰሜን ኮሪያ ጠላትን ለማሳሳት በሚል ስምንት ተመሳሳይ ቤተ መንግስቶችን መገንባቷ ተገልጿል።

እንደ ዴይሊ ሜይል ዘገባ ከሆነ ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን ደህንነትን ለመጠበቅ ሲባል በሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ ተመሳሳይ ቅርጽ ያላቸው ቤተመግስቶችን ገንብታለች።

ሰሜን ኮሪያ በጎረቤቷ ደቡብ ኮሪያ አማካኝነት እና በምዕራባዊያን የተቀናጀ ጥረት በፕሬዝዳንቱ ላይ ግድያ ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት አላት።

ይሄንን ስጋቷን ለማስወገድ እና ፕሬዝዳንቷን ለመጠበቅ ተመሳሳይ ቅርጽ፣ የቀለም ቅብ፣ መሰረተ ልማት እና ሌሎች ሚስጢራዊ ግንባታዎችን የያዘ ቤተ መንግስት መገንባቷን ዴይሊ ሜጠይል የሳተላይት ምስሎችን ዋቢ አድርጓል።

እነዚህ ቅንጡ ስምንት ቤተ መንግስቶች በመሃል ፒዮንግያንግ ቻንግ ክዋንግሳን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሀገሪቱ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት መገንባቱ ተገልጿል።

ቤተ መንግስቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች ለሌሎች የሀገሪቱ ዜጎች ዝግ መሆኑን ተከትሎ አካባቢው “የተከለከለ ከተማ” ወይም ፎርቢድን ሲሰቲ የሚል ስምም ተሰጥቶታል ተብሏል።

የሰሜን ኮሪያ ሀገራዊ ሚስጢራት እና ወታደራዊ እቅዶች በነዚህ ቤተመንግስቶች ውስጥ እንደሚረቀቁም ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ኪም እና አስተዳድራቸው በሰሜን ኮሪያ ዋነኛ ስጋቷ ከሀገሬው ህዝብ ወይም ፖለቲከኞች ሳይሆን ከውጭ ሀገራት የሚሰነዘር እንደሚሆን እርግጠኛ ናቸው።

ይሄንንም ስጋት ለመቀልበስ ጥቃቱ በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እና ወታደራዊ ተቋማቸው ላይ ስለሚሆን ጠላቶችን ለማሳሳት አጠቃላይ እንቅስቃሴያቸውን ገድበው በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ኪም ራሳቸውን እና ሀገራቸውን ከአደጋ ለመጠበቅ በጠዋት እና በምድር ውስጥ የተዘጋጁ መጓጓዣዎችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ኪም ከሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ በተጨማሪ በመላው የሀገሪቱ ክፍል 13 ቤተ መንግስቶች አሏቸው የተባለ ሲሆን እነዚህ ቤተመንግስቶች በወዳጆቻቸው እና ዘመዶቻቸው ይጠበቃሉም ተብሏል።