News today, Politics

ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ ነው

ጀርመን ወደ ሞስኮው ልኡክ የምትልከው ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከሩሲያ ጋር ለመምከር ነው
ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ መሆኑ ተሰምቷል።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦርን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲጠያ ጋር በተቀሰቀሰው ጦርነት የዓለም ነዳጅ ዋጋ አሻቅቧል።
40 በመቶ የነዳጅ ፍጆታቸውን ከሩሲያ የሚሸምቱት አውሮፓዊያን በዩክሬን ጉዳይ አጣብቂኝ ውስጥ ወድቀዋል።

ከአውሮፓ ሀገራት መካከል ጀርመን ደግሞ የሩሲያ ነዳጅ ጥገኛ ከሆኑ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነዳጅ እንደበፊቱ ማግኘት አልቻለችም።

በዚህም ምክንያት የፕሬዝዳንት ፑቲን ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የቀድሞቀው የጀርመን ፕሬዝዳንት በጌራልድ ሽሮደር የሚመራ ልኡክ ወደ ሞስኮ ልትልክ መሆኑን አስታውቃለች።

የወቅቱ የጀርመን ፕሬዝዳንት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ወደ ጀርመን የምትልከውን ነዳጅ መጠን እንዳትቀንስ የሚያግባባ ልኡክ ወደ ሞስኮ እንደሚልኩ ሮይተርስ ዘግቧል።

ይህን በነዳጅ ግብይት ዙሪያ ለመምከር ወደ ሞስኮ የሚያቀናውን ልኡክ የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሾልደር ሊመሩት እንደሚችሉ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

ወደ ሞስኮ የሚያቀናው የጀርመን ልኡክም በዋናነት ተልዕኮው ሩሲያ በኖርድ ስትሪም አንድ ተብሎ በሚጠራው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ነዳጅ በበቂ መጠን እንድትልክ ማግባባት እንደሚሆን ተገልጿል።

የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሽሮደር ወደ ሞስኮ አቅንተው ፕሬዝዳንት ፑቲንን ያገኙ ሲሆን የጀርመን መንግስት ከዚህ በፊት ነዳጅ ከሩሲያ የሚያገኝበት ኖርድ ስትሪም አንድን ትቶ ወደ ሁለት እንዲያተኩር አሳስበው ነበር።

ጌራልድ ሽሩደር ጀርመንን ከፈረንጆቹ 1998 ጀምሮ እስከ 2005 ድረስ በፕሬዝዳንትነት ማገልገላቸው አይዘነጋም።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 170ኛ ቀኑ ላይ ሲሆን እስካሁን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ሀገራቸውን ጥለው ወደ ጎረቡት ሀገራት መሰደዳቸውን ተመድ ከሰሞኑ ገልጿል።