Ke alemi zuriya-ከዓለም ዙሪያ

7 ነሐሴ 2022
እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን (ፒአይጄ) ሁለት አመራሮች አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ፍልስጤማውያን ተገደሉ።
አመራሮቹ ካሊድ መንሱር እና ጣይር ጃብሪ፣ በርካታ የቡድኑ ተዋጊዎችና ስድስት ህፃናትን ጨምሮ 32 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸው ተዘግቧል።
ከአርብ ጀምሮ ወደ 400 የሚጠጉ የፍልስጥኤም ሮኬቶች እና ሞርታሮች በእስራኤል ላይ መተኮሳቸውን የእስራኤል ባለስልጣን ተናግረዋል።
እስራኤል ወታደራዊ ዘመቻ ብላ የምትጠራውን ይህንን የአየር ጥቃት የጀመረችው የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን በደቀነው ከፍተኛ ስጋት ነው ብላለች።
ባለፈው አመት ግንቦት ወር ለ11 ቀናት በዘለቀው እና ከ200 በላይ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም በርካታ እስራኤላውያን ከተገደሉበት ግጭት ወዲህ ይህ በቅርቡ በእስራኤልና በጋዛ መካከል የተከሰተ አሳሳቢ ግጭት አድርጎታል።
‘ብሬኪንግ ዳውን’ ( መሰባበር) የሚል የኮድ ስም እስራኤል የሰጠችው ወታደራዊ ዘመቻ ለአንድ ሳምንት ሊቆይ እንደሚችል ባለስልጣናቷ አስጠንቅቀዋል።
በሁለተኛው ቀን ጥቃት ትናንት ቅዳሜ በደቡባዊ ጋዛ ራፋህ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ከፍተኛ የፒአይጄ መሪ ካሊድ መንሱርን መግደሏን አስታውቃለች።
ከጋዛ ውጭ ወታደራዊ ጥቃቶችን ፈጽሟል በማለት እስራኤል የምትከሰው ካሊድ መንሱር ከዚህ ቀደም በእስራኤል ጦር ከአምስት የግድያ ሙከራዎች ተርፎ ነበር።
ከሱ ሞት በፊት አርብ እለት ከፍተኛ የፒአይጄ አመራር የሆነው ታይሲር ጃባሪ በእስራኡል የአየር ጥቃት ተገድሏል።
እንዲሁም በጋዛ በተፈጸመው የአየር ጥቃት ድብደባ በርካታ የቡድኑ አባላት ከመገደላቸው በተጨማሪ እስራኤል ተቆጣጥራት ባለቸው የዌስት ባንክ በተደረገ ከበባ 19 የሚሆኑ የፒአይጄ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እስራኤል ገልጻለች።
የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለፍልስጥኤማውያን ሞት እንዲሁም ለቆሰሉት 203 ሰዎች “የእስራኤል ወራራን ተጠያቂ አድርጓል።
