News today, Politics

የዩክሬኗ ዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ


የዛፖሮዝሂ ክልል በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን ትገኛለች
እስካሁን በዛፖሮዝሂ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ የዘገቡት የሩሲያ ሚዲያዎች ናቸው

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን የምትገኘው የዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ሕዘበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ግዛቲቱ ወደ ሩሲያ ለመጠቃለል ሕዝበ ውሳኔ እንደምታደርግ አስተዳዳሪው መግለጻቸውን የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

የሩሲያ ጦር የተቆጣጠራቸው የዩክሬን ግዛቶች ወደ ሩሲያ ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ሊያካሂዱ ነው
የግዛቲቷ አስተዳዳሪ ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል የሚስችል ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ ያስታወቁት ዛሬ ነው፡፡

የግዛቲቱ ደቡባዊ ክፍል አሁን ላይ በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን ሙሉ ግዛቱ ግዛቱ ሕዝበ ውሳኔ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሕዝበ ውሳኔው ከዩክሬን ጋር መቀጠል ወይስ ወደ ሩሲያ ግዛት መጠቃለል የሚሉ ምርጫዎች እንዳሉትም ነው የተገለጸው፡፡

የግዛቲቱ አስተዳዳሪ ኢቭጌኒ ባሊትስኪ ጉባዔ በተደረገበት ወቅት ሕዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ተብሏል፡፡

የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን የሆኑት ሩሲያ ቱዴይ እና ታስ እንደዘገቡት ከሆነ ከ700 በላይ የሚሆኑ ተወካዮች ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አጽድቀዋል ብለዋል፡፡

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በምትገኘው ዛፖሮዚ ግዛት ይደረጋል የተባለው ሕዝበ ውሳኔ በመስከርም ወር ሊካሄድ እንደሚችል ፍንጭ ተሰጥቷል፡፡

በዛፖሮዚ ግዛት ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ውሳኔ መተላለፉን በተመለከተ የዘገቡት የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ብቻ ናቸው፡፡

ሩሲያ በምስራቅ ዩክሬን ውስጥ ላሉ ተገጣይ ግዛቶች እውቅና ሰጠች
አሁን ላይ ሕዝበ ውሳኔ ይደረግባታል ተብላ የምትጠበቅ ግዛት ግማሽ ክፍል በሩሲያ ወታደሮች የተያዘው ገና ሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በጀመሩ ሰሞን ነበር፡፡

የተወሰነው የግዛቲቲ ክፍል ብቻ በዩክሬን ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት አራት ወራትን የተሻገረ ሲሆን አሁንም አልተቋጨም፡፡