News today, social life

የሴኔጋል ፓርላማ አባላት እርስበርሳቸው ተደባደቡ

ሴኔጋል ከአንድ ወር በፊት ነበር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደችው።

ገዥው ፓርቲ አብዛኛውን መቀመጫ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በተነጠቀበት በዚህ ምርጫ ተመራጭ የሆኑ የምክር ቤት አባላት ዛሬ ስራቸው ጀምረዋል።

አባላቱ በዛሬው ስብሰባቸው የምክር ቤቱን ተጠሪ ፕሬዝዳንት መምረጥ የነበረባቸው ቢሆንም ወደ ስምምነት መምጣት አልቻሉም።

የምክር ቤቱ አባላት አለመስማማታቸው ተከትሎ በተፈጠረ አለመግባባት በወንበር እና ውሀ መያዣ ፕላስቲኮችን እርስ በርስ በመወራወር እንደተደባደቡ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል።

በምክር ቤቱ አባላት የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎም የሀገሪቱ ፖሊስ ገብቶ ተደባዳቢዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ክስተቱን ተቆጣጥሯል ተብሏል።

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya