News today, social life

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7 ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

በጃፖን በሬክተርስኬል መጠኑ 6 ነጥብ 8 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከስቶ በ146 ሰዎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

የታይዋን አየር ንብረት ቢሮ እንደገለጸው ህዝብ ተራርቆ በሚኖሮበት በደቡብ ምስራቅ ታይዋን የተከሰተው መሬት መንቀጥቀጥ ባቡሮች እንዲገለበጡ፣ የስቶር መደርደሪያዎች እንዲደረመሱና መንገዶች እንዲዘጉ ምክንያት ሆኗል።

ቢሮው የመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ ታይተን ግዛት ሲሆን በአካባቢው የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ግን ጉዳት አላደረሰም ብሏል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ በትናንትናው እለት የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል።

የታይዋን የእሳት ዲፖርትመንት በአደጋው የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን እና 146 ሰዎች መጎዳታቸውን አስታውቋል።

የታይዋን የሬይል ዋይ አስተዳደር ደግሞ ስድስት ባቡሮች መስመራቸውን ስተው መግልበጣቸውን እና በሰው ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልጿል።

በአደጋው በተዘጋው መንገድ ምክንያት በተራራማ አካባቢዎች መንገድ የተዘጋባቸውን 600 ሰዎች ለማውጣት ጥረት ላይ ናቸው።

የአሜሪካው የፖስፊክ የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ማእከል ከመንቀጥቀጡ አደጋው በኋላ ማስጠንቀቂያ አውጥቶ የነበረ ቢሆንም ቆይቶ አንስቶታል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል።

በፈረንጆቹ 2016 በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 100 ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።