News today, Politics, social life, Technology

በ11 የአለም ዋንጫዎች ላይ የታደሙት ብራዚላዊ

የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን በአርጀንቲና በ1978 የተመለከቱት ዳኔል ስብሩዚ በኳታርም የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ተከታትለዋል

“የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው ፤ በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዝግጁ ነኝ” ብለዋል

11 የአለም ዋንጫዎችን የተመለከቱት ብራዚላዊ በድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ስማቸውን ማስፈር ችለዋል።

ዳኔል ስብሩዚ የተባሉት የ76 አመት አዛውንት የሳኦሎ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ስብሩዚ በ1978 ወደ አርጀንቲና በማቅናት የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ከተመለከቱ ወዲህ አለምን በኳስ ምክንያት ዞረዋል።

የዘንድሮውን የኳታር የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዶሃ ገብተው ሰንብተዋል።

የ76 አመቱ አዛውንት በዶሃ 11ኛ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ሲመለከቱም የአለም የድንቃድንቅ መዝገብ ክብረወሰን ይዘዋል በሚል የምስክር ወረቀት ሰጥቷቸዋል።

የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው የሚሉት ስብሩዚ ፤ የአለም ዋንጫ ከመልከ ብዙ ተሰጥኦ ባለቤቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑን አንስተዋል።

ከአርጀንቲና እስከ ኳታር አለም ዋንጫን ለመመልከት ሲጓዙም የብራዚልን ባህልና ወግ ሲያስተዋውቁ እንደነበር ተናግረዋል።

ባለፉት 44 አመታት በተለያዩ አልባሳት አጊጠው ብራዚልን እየደገፉ የሳኦ ፖሎን ባህል በስፋት ያስተዋወቁት ስፖርት አፍቃሪ፥ የአለም ዋንጫን በስታዲየም ከመመልከት የሚያስቆመኝ ሞት ብቻ ነው እያሉ ነው።

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ በሚያዘጋጁት የ2026 የአለም ዋንጫ ለምታደምም ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በራሳቸው የተያዘውን ክብረወሰን ለማሻሻል ተስፋ አድርገዋል።

News today, Politics, social life, Technology

አርጀንቲና የኳታሩን የአለም ዋንጫ ያነሳችበት ጨዋታ በምስል

አርጀንቲና ለ3ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን አንስታለች

የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን

አርጀንቲና በመለያ ምት 4 ለ 2 ፈረንሳይን አሸንፋለች

በሉሳይል ስታዲየም የተደረገው ልብ አንጠልጣይ ፍልሚያ በአርጀንቲና አሸናፊነት ተደምድሟል።

አርጀንቲና ሶስት ጊዜ መርታ አቻ በሆነችበት ምሽት ሌዮኔል ሜሲ ሁለት ጎሎችን አስቆጥሯል።

ውሃ ሰማያዊ እና ነጭ ለባሾቹ በመጀመሪያው አጋማሽ 2 ለ 0 እየመሩ ቢወጡም ፈረንሳይ በኪሊያን ምባፔ የ80 እና 81ኛ ደቂቃ ሁለት ጎሎች አቻ ሆናለች።

በተጨማሪ 30 ደቂቃውም ሜሲ ሶስተኛውን ጎል ለሀገሩ ቢያስቆጥርም የፈረንሳዩ የ23 አመት ኮከብ ኪሊያን ምባፔ ባስቆጠራት ሶስተኛ ጎል ጨዋታው በመለያ ምት ተጠናቋል። በዚህም አርጀንቲና 4 ለ 2 በሆነ የፍጹም ቅጣት ምት ጎል አሸናፊ ሆናለች።

ሊዮኔል ሜሲ ከ36 አመት በፊት ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ያሳካውን ክብር በደገመበት ምሽት የብራዚላዊውን ፔሌ የጎል አስቆጣሪነት ክብር ማሻሻል ችሏል።

የ35 አመቱ ሜሲ በ26 የአለም ዋንጫ ጨዋታዎች ተሰልፎ 13 ጎሎችን በማስቆጠሩም በብራዚላዊው ፔሌ ተይዞ የቆየውን ክብረወሰን ማሻሻል ችሏል።

አርጀንቲና በዛሬው የሉሳይል ስታዲየም ፍልሚያ ድል ማድረጓን ተከትሎ በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ተሸንፋ (በሳኡዲ አረቢያ) ዋንጫውን በመውሰድ ስፔን በ2010 የያዘችውን ሪከርድ ተጋርታለች።

የላቲን አሜሪካዋ ሀገር ፈረንሳይን በመርታት ሶስተኛ ዋንጫዋን አንስታለች።

አርጀንቲና በ1978 ፣ 1986 እና በኳታር የዓለም ዋንጫን ወስዳለች።

News today, Technology

የበርካቶችን ቀልብ የሳበው የቻይና “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

“J-20” ተዋጊ ጄት ዡሃይ የቻይና የአየር ትርኢት ላይ ለእይታ ቀርበዋል

“J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

የ2022 የቻይና የአየር ትርኢት በደቡባዊ የሀገሪቱ ከተማ ዡሃይ መካሄድ ላይ ሲሆን፤ “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት ለእይታ ቀርቧል።

የቻይና ሕዝብ ነፃ አውጪ ጦር ተብሎ የሚጠራው የቻይና ጦር የታጠቀው “J-20” ስውር ተዋጊ ጄቶች ዙሃይ ሰማይ ላይ መታየታቸው ለቻይና ኤር ሾው የበለጠ ድምቀትን ጨምሯል።

ለቻይና ኤር ሾው ላይ የቻይና አየር ሃይል ተዋጊዎች እና “የአየር ኤሮባቲክስ” ቡድን በዙሃይ ታላቅ የአየር ትርኢት ቢያቀርቡም አራት ጄ-20 ስውር ተዋጊዎች የተመልካችን አይን ስበዋ ነው የተባለው።

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

“J-20” ተዋጊ ጄቶች የመጀመሪያዎቹ ስሪቶች በሩሲያ የተመረቱ ሞተሮችን ይጠቀሙ የነበረ ሲሆን፤ በኋላ ላይ ግን ቻይና በራሷ ባመረተችው መንትያ ሞተር እንደተካች ይነገራል።

በችንግዱ ኤርክራፍት ግሩፕ የሚመረተው “J-20” ተዋጊ ጄት የመጀመሪያ በረራውን በፈረንጆቹ 2011 ያካሄደ ሲሆን፤ በ2017 በስራ ላይ እንደዋለም ተነግሯል።

በሰዓት እስከ 2 ሺህ 100 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር ይችላል የተባለለት “J-20” ተዋጊ ጄት፤ 19 ሺህ 390 ኪሎ ግራም ክብደት አለው ተብሏል።

 “J-20” ተዋጊ ጄት ቻይና የዓለማችን ቀዳሚ ስውር ተዋጊ ጄት ተብለው ለሚነገርላቸው የአሜሪካ ኤፍ-22 እና ኤፍ-35 ተዋጊ ጅቶች የሰጠችው ምለሽ መሆኑ ይነገራል።

በአሁኑ ወቅት 200 J-20 ተዋጊ ጄቶች የቻይና ህዝቦች ነጻነት ሰራዊት ተብሎ በሚጠራው የቻይና ጦር አየር ኃይል አገልግሎት እየሰጡ ነው።

የቻይና አየር ክልሏ ለሚጥሱ የማንኛውም ሀገር ተዋጊ ጄቶች ምለሽ የምትሰጠው በእነዚሁ “J-20” ተዋጊ ጄቶች መሆኑ ተገልጿል።

News today, Politics, Technology

ኢራን የጸጥታው ም/ቤት ውሳኔን በመጣስ ለኢትዮጵያ ድሮን መሸጣን አሜሪካ አስታወቀች

ኢራን ሰው አልባ የጦር አውሮፕላን (ድሮን) ለኢትዮጵያ የሸጠችው ከአንድ ዓመት በፊት ነው ተብሏል

ኢራን “ሞሃጀር” የተሰኘውን ድሮን ለኢትዮጵያ መስጠቷን አሜሪካ ገልጻለች

ኢራን የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔን በመጣስ ለኢትዮጵያ ድሮን መሸጧን አሜሪካ አስታወቀች።

የአሜሪካ መንግስት እንዳሳወቀው ኢራን ከአንድ ዓመት በፊት ክረምት ላይ ለኢትዮጵያ ሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን ማስተላለፏን ገልጿል።

ኢራን በፈረንጆቹ 2015 ላይ የጦር መሳሪያ ግብይት እንዳትፈጽም የሚከለክል ማዕቀብ በመንግስታቱ ድርጅት የተወሰነባት ሲሆን፤ ይሄንን ማዕቀብ በመጣስ ለኢትዮጵያ አስተላልፋለች ተብሏል።

2231 የተሰኘው ይህ የተመድ ውሳኔ በኢራን መጣሱን የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቪዳንት ፓቴል መናገራቸውን ዋቢ አድርጎ ሮይተርስ ዘግቧል።

ይህ የተባበሩት መንግስታት ውሳኔ በ2020 ላይ የሚያበቃ ቢሆንም በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ ማዕቀቡ እንዲራዘም ጠይቀው ነበር።

ይሁንና ይህ ማዕቀብ እንዲነሳ ያልተወሰነ በመሆኑ ኢራን ውሳኔውን በመጣስ ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጥታለች ተብሏል፡።

እንደዘገባው ከሆነ ኢትዮጵያ ከኢራን የተረከበችውን ሞሃጀር የተሰኘውን ይሄንን ድሮን ከህወሃት ጋር በሚደረገው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ላይ እንዳዋለችውም ተገልጿል።

ኢራን ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የጦር መሳሪያ ማዕቀቡን በመተላለፍ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ለጀመረችው ጦርነት ድሮን ለሞስኮ ማስተላለፏንም አሜሪካ አስታውቃለች።

ኢራን በምዕራባዊያን የሚቀርቡባትን ክሶች ውድቅ ያደረገች ቢሆንም ከሩሲያ ጋር የሰው አልባ አውሮፕላን እና ሚሳኤል ግዢ ስምምነት መፈጸሟን አምናለች።

ዩክሬን በበኩሏ ኢራን ሻሂድ፣ጄራን እና ሌሎች ስያሜ ያላቸውን ድሮኖች ለሩሲያ በመሸጥ የዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች እንዲደበደቡ አድርገዋል በሚል ከቴህራን ጋር ያላትን ግንኙነት እንደምታቋርጥ ዝታለች።

News today, Technology

ዩክሬን ከ230 በላይ የኢራን ሰራሽ ድሮኖችን መትታ መጣሏን አስታወቀች

ሩሲያ ድሮኖቹን በመጠቀም የዩክሬን መሰረተ ልማቶች እያወደመች እንደሆነ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ተናግረዋል

ዩክሬን ከኢራን ጋር ያላትን ግንኙነት ለማቋረጥ እያሰበችበት እንደሆነም ተገልጿል

ዩክሬን ከ230 በላይ የኢራን ሰራሽ ድሮኖችን መትታ መጣሏን አስታወቀች።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስምንት ወራት የሞላው ሲሆን የጦርነቱ ሁኔታ በየጊዜው እየተቀያየረ አዳዲስ ክስተቶችን እያስተናገደ ቀጥሏል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ኢራን ሰራሽ የሆኑ ከ233 በላይ ለሩሲያ የተሰጡ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወይም ድሮኖች ተመተው መውደቃቸውን ተናግረዋል፡፡

ሩሲያ እነዚህን ኢራን ሰራሽድሮኖቹን በመጠቀም የዩክሬን መሰረተ ልማቶች እያወደመችበት እንደሆነ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በዛሬው ዕለት ብቻ 10 ድሮኖችን መትተው መጣላቸውን አክለዋል፡፡

ሩሲያ በተለይም የዩክሬን ዋና ዋና መሰረተ ልማቶችን እያወደመች እንደሆነ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ በተለይም ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከጥቅም ውጪ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት የዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች ከሀይል አቅርቦት ውጪ ሆነዋል የተባለ ሲሆን ከተሞቹን መልሶ የሀይል አቅርቦት እንዲያገኙ ከፍተኛ ወጪ እየጠየቁ እንደሆነም ፕሬዝዳንቱ አክለዋል፡፡

ክሪሚያን ከተቀረው የሩሲያ ክፍል ጋር ለማስተሳሰር የሚውለው ድልድይ በዩክሬን ተመቶብኛል ያለችው ሞስኮ በ10 ቀናት ውስጥ ከ190 በላይ የአየር ላይ ጥቃቶችን በዩክሬን ላይ አድርሳለች ተብሏል፡፡

ሩሲያ በአጠቃላይ በ16 የዩክሬን ግዛቶች ላይ የሚሳኤል፣ የድሮን እና ሌሎች ጥቃቶችን ሰንዝራለች የተባለ ሲሆን ኢራን ሰራሽ ድሮኖች ዋነኛ የጥቃቱ መፈጸሚያ እንደሆኑ ዩክሬን አስታውቃለች፡፡

ዩክሬን ከመሰረተ ልማት ውድመት በተጨማሪ 70 ንጹሃን ዜጎቿ እንደተገደሉባት ያስታወቀች ሲሆን ኢራን ለሩሲያ የጦር መሳሪያ ድጋፍ አድርጋለች ስትልም ክስ አቅርባለች፡፡

ኢራን በበኩሏ ለሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላን እንዳልሰጠች ብትገልጽም በትናንትናው ዕለት ሚሳኤል ለመስጠት ከሩሲያ ጋር ስምምነት መፈጸሟን ዓለም አቀፍ ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡ 

News today, Technology

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ከአሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ጋር ሲነጻፀሩ

የአሜሪካን ጨምሮ የ70 ሀገራት ወታደራዊ ተቋማት ለዩክሬን ድጋፍ እያደረጉ ነው

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ከአሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

የሩሲያው “ታይገር” ብረተ እና አሜሪካው “ሀምቪ” ብረተ ለበስ ተሸከርካሪዎች በዩክሬን ጦርነት ላይ እየተፋለሙ ነው

በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ጦርነተ ከተጀም ሰባት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በርካታ ምእራባውያን ሀገራትም ለዩክሬን የመሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው።

የሩሲያ መከላካያ ሚኒሰቴር በቅርቡ፤ የ70 ሀገራት ወታደራዊ ተቋማት ለዩክሬን ድጋፍ እያደረጉ እንደሆ እና ሩሲያ በዩክሬን ምድር ምዕራባውያን ጋር እየተዋጋች እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል።

አሜሪካ ለሩሲያ በተለያየ ጊዜ የተለያየ መጠን ያለው የጦር መሳሪ ለዩክሬን የሰጠች ሲሆን፤ ከእነዚህም ውወስጥ “ሀምቪ” የተባለው ብረት ለበስ የጦር ተሽከርካሪ አንዱ ነው።

ሩሲያም በዩክሬን ካሰለፈቻቸው የጦር ተሸከርካሪዎች ውስጥ “ታይገር” ብረተ ለበስ ተሸከርካሪ ይገኛል የተባለ ሲሆን፤ በጦርነቱ ላይም የሩሲያው “ታይገር” የአሜሪካውን ሀመቪ ሲያሳድድ እንደታየ ዩሩሲያ መገናኛ ብዙሃ ምንጮች ገልጸዋል።

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ እና አሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪዎች አቅም እና ጥንካሬ ምን ይመስላል?

የሩሲያ የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

“ታይገር ኤም “ አርዛማስክ በተባለ የጦር ተሸከርካሪ አምራች ኩብንያ ነው የተመረተው

በውጊያ ወቅት ወታደሮችን ለማጓጓዘ እንዲሁም መሳሪያዎችን ለማቀበል ይውላል

ፍጥነት፤ በሰዓት ከ125 እስከ 140 ኪሎ ሜትር ድረስ ይጓዛል

በጨለማ ውስጥ ያለምንም ችግር እንዲጓዝ የሚያችል የእይታ መሳሪያ ተገጥሞለታል

ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ አካል እና መስታወት ተገጥሞለታል

የሚታጠቃቸው መሳሪያዎችም

“2A72” አውቶማቲክ ጠመንጃ ከ30 ሚሊ ሜትር ካሊበር ጋር

“AGS-30” አውቶማቲክ የእጅ ቦምብ እና የጭስ ቦምብ ማስወንጨፊያ

ኮርኔት-ዲ ፀረ-ታንክ ሚሳይል ስርዓት እና ተንቀሳቃሽ የአየር ክልል መከላከያዎችን ይገኙበታል

አሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

“ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ በውጊያ ወቅት ወታደሮችን ለማጓጓዘ እንዲሁም መሳሪያዎችን ለማቀበል ይውላል

ፍጥነት፤ በሰዓት ከ105 እስከ 113 ኪሎ ሜትር ድረስ ይጓዛል

ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ አካል እና መስታወት ተገጥሞለታል

በተጨማሪም ከጎን እና ከኋላ ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ ተለጥፎለታል

የሚታጠቃቸው መሳሪያዎችም

• M2፣ M240፣ እና M249 ካሊበር መሳሪያ

• 25 ሚሊ ሜትር ፀረ አውሮፕላን መሳሪያ

• Mk-19 ቦምብ እና የጭስ ቦምብ ማስወንጨፊያ ከ40 ሚሊ ሜትር ካበር ጋር

• ፀረ ታንክ እና AIM-120 ሚሳዔል ማስወንጨፊያዎች እንዲሁም 105 ሚሜ መድፍ ይገኙበታል

News today, Technology

“አውዳሚው” የሚባለው ዘመናዊ የአሜሪካ የጦር መርከብ

የዘርፉ ባለሙያዎች “አጓጊ ግን የከሸፈ የመርከብ ጽንሰ-ሀሳብ” ይሉታል

አሜሪካ ካላት ግዙፍ የጦር መሳሪያዎች ውስጥ “ዩ.ኤስ.ኤስ ዙምዋልት” የጦር መርከብ አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

4 ነጥብ 4 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደወጣበት የሚነገረው የጦር መርከቡ በርካታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎቸን የጣጠቀ እንደሆነ ይነገርለታል።

በፈረንጆቹ 2008 ግንባታው የተጀመረው የጦር መርከቡ በ2013 ላይ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ በፈረንጆቹ 2016 ላይ በአሜሪካ ባህር ኃይል ስራ ላይ እንደዋለም መረጃዎች ያመለክታሉ።

አሁን ላይ አሜሪካ ሁለት ዙምዋልት አውዳሚ የጦር መርከቦችን ያላት ሲሆን፤ እነዚህ “ዩ.ኤስ.ኤስ ሞንሶር” እና “ዩ.ኤስ.ኤስ ላይደን ቢ ጆንሰን” የሚል መጠሪያ ያላቸው ናቸው።

አውዳሚ ነው የተባለው የጦር መርከቡ አሜሪካ ካላት ጦር መርከቦች የወጣበት ዋጋ በእጥፍ የሚበልጥ ነው ብለዋል።

የቢላዋ ቅርጽ ያለው የመርከቡ የፊት ክፍል በከባድ የባህር ክፍል ላይ በቀላሉ እንዲጓዝ የሚያስችለው መሆኑንም ድፌንስ ኒውስ በመረጃው አስታውቋል።

መርከቡ 158 የባህር ኃይል አባላትን አሳፍሮ የሚጓዝ ሲሆን፤ 16 ሺ ቶን ገደማ ክብደት በመያዝ በሰዓት እስከ 56 ኪሎ ሜትር መብረር ይችላል ተብሏል።

መርከቡ ባለብዙ ተግባር ራዳሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ከውኃ አካል ላይ ወደ ላይ ሚሳዔል ለማስወንጨፍ የሚያስችሉ 80 ሴሎች እንዳሉትም ተነግሯል።

ሆኖም ግን መርከቡ የፀረ መርከብ፣ የፀረ ባሀር ስርጓጅ ፣ የአየር መከላከያ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፊያ የሌለው መሆኑ እንደክፍተት ይነሳበታል።

የወታደራዊ ጉዳዮች ባለሙያ የሆኑት ሴባስቲያን ሮብሊን፣ የመርከቡ ጽንሰ ሀሳብ እጅግ አጓጊ ነገር ግን የከሸፈ ነው ሲሉ ይገልጹታል።

News today, Technology

“አይበገሬው” የሚል መጠሪያ የተሰጠው “CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር

“CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር ለመንቀሳቀስ ሁለት አብራሪዎች ያስፈልጉታል

የተለያዩ የጦር መሳሪያ የሚተኩሰው ሄሊኮፕተሩ በሰዓት 445 ኪ.ሜ ይበራል

አሜሪካ ካሏት የጦር ሄሊኮፕተሮች ውስጥ “አይበገሬው” የሚል መጠሪያ የተሰጠው “CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር አንዱ ነው።

ቦይንግ እና ሄል ሄሊኮፕተር ቴክስትሮን ኩባንያዎች በጥምረት ያመረቱት ሄሊኮፕተሩ በፈረንጆቹ በ2006 ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰማራ ሲሆን፤ የተለያዩ ተልእኮዎችንም መፈጸም እንደቻለ ይነገርለታል።

ሄሊኮፕተሩ ከተሳተፈባቸው ዉጊያዎች ውስጥም ቀዳሚ እና ግዙፉ አሜሪካ በኢራቅ ያካሄደችው ዘመቻ እንደሆነም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት።

በውጊያ ወቅት የጦር መሳሪያዎችን ለመተኮስ እና ወታደሮችን ለማጓጓዝ የሚውለው ሄሊኮፕተሩ፤ በአንድ ጊዜ ተቀምጠው ከሆነ 24 ወታደሮችን ቆመው ከሆነ ደግሞ 32 ወታደሮችን ጭኖ መጓዝ ይችላል ተብሏል።

CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር ምን የተለየ ያደርገዋል?

ሮልስ ሮይስ አሊሰን AE1107C ሞተር የተገጠመለት ሄሊኮፕተሩ ለመነሳትም ይሁን ለማረፍ መደርደሪያ አያስፈልገውም የተባለ ሲሆን፤ ቀጥ ብሎ ወደላይ የሚነሳ እና ባለበት ተወዳች እየተምዘገዘገ ማረፍ ይችላል።

የረቀቁ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር ዲጂታል ካርታ፣ ዲጂታል ሙሉ በሙሉ ዲጂታል የሆነ የአብራሪዎች ክፍል (ኮክፒት) እንዲሁም ራስን የመከላከል ስርዓቶች ተገጥመውለታል።

ሄሊኮፕተሩ ከባባድ ሮኬቶችን ጨምሮ ኒውክሌርን መቋቋም ይችላል የተባለ ሲሆን፤ “አይበገሬው” የተባለውም ከዚሁ በመነሳት ነው።

ሄሊኮፕተሩን ለማብረር ሁለት አብራሪዎች እና ሁለት የበረራ ኢንጂነሮች (መሃንዲሶች) የግድ ያስፈልጉታል ነው የተባለው።

CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር በሰዓት 445 ኪሎ ሜትር የሚበር ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ ነዳጅ ብቻ ከ925 ኪሎ ሜትሮች በላይ መብረር የሚችል ይችላል።

አየር ላይ ነዳጅ ከተሞላለት ደግሞ በየትኛውም የአየር ሁኔታ ውስጥ ከ3300 በላይ ኪሎ ሜትር ያለማቋረጥ መጓዝ እንደሚችል ተነግሯል።

ሄሊኮፕተሩ ላይ ወደላይ መተኮስን የሚያስችላቸው 7.62 ሚሊ ሜትር ሚኒገን ተገጠመለት ሲሆን፤ በመወጣጫው ላይ ደግሞ ካሊበር ማችን ገን ተገጥሞለተል።

News today, Technology

የአሜሪካው ናሳ ወደ ጨረቃ ሊያመጠቅ የነበረው ሮኬት ለሁለተኛ ጊዜ ከሸፈ

ሮኬቱ ላይ ነዳጅ መፍሰስ በማጋጠሙ ማስወንጨፉ ለሁለተኛ ጊዜ ተቋርጧል

የአሜሪካው ናሳ “አርቴሚስ 1” ሮኬት

አሜሪካ ከ50 ዓመታት በኋላ ተመራማሪዎችንና መሳሪያዎቻቸውን ወደ ጨረቃ ለመላክ እየሰራች ነው

የአሜሪካው ናሳ “አርቴሚስ 1” የተባለ ሮኬትን ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ ያደረገው ሙከራ ለሁለተኛ ጊዜ መክሸፉ ተሰምቷል።

የናሳ ተመራማሪዎች በትናትናው እለት ሮኬቱን ለማስወንጨፍ የሚረዳውን የጠፈር ማስወንጨፊያ ስርዓት ለማስጀምር በተደጋጋሚ ቢሞክሩም ለሁለተኛ ጊዜ ሳይሳካቸው ቀርቷል።

የሮኬቱ ማስወንጨፍ ለሁለተኛ ጊዜ ሳይሳካ የቀረው በማስወንጨፊያው ላይ ባጋጠመው የነዳጅ መፍሰስ እንደሆነም ታውቋል።

ይህንን ተከትሎም የዘርፉ ባለሙያ ኢንጂነሮች በሮኬቱ ላይ ድጋሚ ፍተሻ ያደርጋሉ የተባለ ሲሆን፤ ይህም ጊዜ ሉወስድ ይችላል ተብሏል።

ፍተሸው ከማስወንጨፊያ ስፍራ ይልቅ በመስሪያ ቦታው ላይ ተወስዶ ሊካሄድ እንደሚችል እና ይህም የሮኬቱን የማስወንጨፊያ ጊዜ እስከ ጥቅምት ወር ሊያዘገየው ይችላል ነው የተባለው።

ናሳ ሮኬቱን ባሳለፍነው ሰኞ ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ ሞክሮ የነበረ ሲሆን፤ ሆኖም ግን አራቱ ትላልቅ ሞተሮች በትክክለኛ የሥራ ሙቀት ላይ መሆናቸውን ተቆጣጣሪዎች ማረጋገጥ ባለማቻላቸው ተቋርጦ ነበር።

ሮኬቱን የማስወንጨፍ ሙከራ ከትናትናው ጋር ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፤ መሳካት ግን አልቻለም።

አሜሪካ ከ50 ዓመታት በኋላ ተመራማሪዎችንና መሳሪያዎቻቸውን ወደ ጨረቃ ለመላክ እየሰራች ሲሆን፤ ይህም የአፖሎ ፕሮጀክት እአአ በ1972 ካበቃ በኋላ የተሰራ ነው።

6100 ሜትር የሚረዝመው ሮኬት አላማው ኦሪዮን የተባለውን ካፕሱል ወደ ጨረቃ ለማድረስ አላማ ኖሮት የተሰራ መሆኑንም ከናሳ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

News today, Technology

አፕል በአደጋ ወቅት ኔትዎርክ ከሌለበት ስፍራ በሳተላይት መልእት የሚልክ አይፎን 14 ይፋ አደረገ


አፕል ለስፖርተኞች የሚሆን “አልትራ” ስማርት ሰዓትም አስተዋውቋል

አፕል የመኪና አደጋ ቀደሞ መለየት የሚያችል ቴክኖሊጂ የተገጠመለት ስማርት ስልክም አስተዋውቋል

የአሜሪካው የቴክኖሎጂ ኩባያ አፕል በትናትናው ምሽት በበርካቶች ዘንድ ሲጠበቅ የነበረውን አይፎን 14 ስማርት ስልክን ጨምሮ ሌሎችም አዳዲስ የቴክኖለጂ ምርቶችን አስተዋውቋል።

አፕል ኩባያ በትናትናው እለት ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ በቴክኖሎጂ የረቀቁ የአይፎን 14 ስማርት ስልኮች፣ ስማርት ሰዓት እንዲሁም የማዳመጫ ምርቶቹን ይፋ አድርጓል።

ክባያው ሁለት የአይፎን 14 ስማርክ ስልክ አይነቶችን ያስተዋወቀ ሲሆን፤ እነዚህም አይፎን 14 እና አይፎን 14 ፕላስ ናቸው።

ስማርት ስልኮቹ በቴክኖሎጂ የረቀቁ ናቸው የተባለ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ በአደጋ ጊዜ ኔትዎርክ በሌለበት አካባቢ ላይ ስንሆን ከሳተላይት ጋር በመገናኘት መልእክት ለመላክ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተገጥሞለታል።

ስማርት ስልኩ ያለ ሞባይል ኔዎርክ ከሳተላይት ጋር ተገናኝቶ መልእክት ለመላክ ዝቅተኛው 15 ሰከንድ ከፍ ካለ ደግሞ ጥቂት ደቂቃዎችን ሊፈጅበት ይችላል።

አዲሱ አይፎን 14 ከጀርባው ላይ ሶስት 12 ሜጋ ፒክስል ጥራት ያላቸው ካራዎች የተገጠሙ ሲሆን፤ የፊትለፊት (ሰልፊ) ካሜራውም 12 ሜጋ ፒከስል መሆኑ እና ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን የማስካከል ቴክኖሎጂም ተገጥሞለታል።

የአይፎን 14 ካሜራዎች ፈጣን እንቅስቃሴ ያላቸውን ቁሶች ፎቶ ማንሳት ጨምሮ በዝቅተኛ ብርሃን ፎቶ በማንሳት ረገድ 49 በመቶ ማሻሻያ እንደተረገም ኩባያው አስታውቋል።

ለስማርት ስልቹ የመሸጫ ዋጋ የተቆረጠላቸው ሲሆን፤ በዚህ የአይፎን 14 ዋጋ 799 የአሜሪካ ዶላር፣ የአይፎን 14 ፕላስ ደግሞ 999 ዶላር መሆኑም ታውቋል።

አፕል ኩባንያ ትናንት ካስተዋወቃቸው የቴክኖሎጂ ምርቶች ውስጥ ሲሪየስ 8 የተሰኘው ስማርት ሰዓትም ይገኝበታል።

ሲሪየስ 8 የተሰኘው ስማርት ሰዓት የመኪና አደጋ ቀደሞ መለየት የሚያስችል ቴክኖሊጂ የተገጠመለት ሲሆን፤ አደጋ ከደረሰ በኋላም የአደጋው የደረሰበትን አካባቢ የሚጠቁም መልእክት መላክ ይችላል ተብሏል።

ስማርት ሰዓቱ በተጨማሪም ለሴቶች የወር አበባን መከታተል እንዲሁም የሰውነትን ሙቀት በመለካት ክትትል ማድረግን ጨምሮ በርካታ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በውስጡ ይዟል።

አልትራ የተባለው ስማርት ሰዓትም አፕል ትናንት ካስተዋወቃቸው ውስጥ ሲሆን፤ በተለይም ለስፖርተኞች የሚያለግል ነው ተብሏል።

አልትራ ስማርት ሰዓት ውሃ የማያስገባ በመሆኑ ለዋነተኞች እንዲሁም በቀላሉ የማይሰበር እና አቧሯ የማያስገባ መሆኑ ደግሞ ለአትሌቶች እና ለሌሎችም ስፖርተኞች ያገለግላል።

News today, Technology

ቻይና በ2025 ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ማጓጓዝ ልትጀምር ነው

ቻይና ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የጉዞ አይነቶችን አዘጋጅታለች
የቻይና የጠፈር ጉዞ
የአንድ ሰው የጠፈር የጉዞ ትኬት ዋጋም ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይሆናል ተብሏል

ቻይና በፈረንጆቹ 2025 የግል ተጓዦችን በክፍያ ወደ ጠፈር ለማጓጓዘ እየሰራች መሆኑ ተገለፀ።

አንድ የቻይና የሮኬት ተመራማሪ እንዳስታወቁት ከሆነ የአንድ ሰው የጉዞ ዋጋ 2 እና 3 ሚሊየን የቻይና ዩዋን (ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር) ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል።

ለጥቂት ደቂቃዎች ወደ ጠፈር ለመጓዝ የአንድ ወንበር የጨረታ ዋጋ ከ2 ነጥበ 4 ሚሊዮን ዶላር አለፈ
በፈረንጆቹ በ2018 የተመሰረተው የሎንግ ማርች ሮክት ዋና ዳይሬክተር እና መቀመጫውን ቤጂንግ ያደረገው ሲ.ኤ.ኤስ ስፔስ ኤጀንሲ መስራች የሆኑት የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ፤ ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የመጓጓዣ ዘዴዎች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

የመጀመሪያው ወደ ዓለም አቀፍ የጠፈር ማዕከል መግባት የሚያስችል ሲሆን፤ ይህም ለቱሪስቶች ጥብቅ የሆነ የአካላዊ እና የስነ ልቦናዊ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሰቀምጥ ነው ተብሏል።

ጃፓናዊው ቢሊየነር የ12 ቀናት የጠፈር ቆይታውን አጠናቆ ተመለሰ
ሁለተኛው የጉዞ አይነት ቱሪስቶች መንኮራኩር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ በሌላ በካርጎ መንኮራኩር ወደ ጠፈር እንዲሄዱ ማድረግ የሚያስችል ሲሆን፤ ይህኛው ጉዞ በአንድ መቀመጫ 450 ሺህ ዶላር እንደሚያስከፍል ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

ሶስተኛው የጉዞ አይነት ሰብ ኦርቢታል የሚባል ሲሆን፤ ይህኛው የጉዞ አይነት ለአብዛኞቹ ጎብኚዎች የተመቸ እንደመሆን የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ ገልፀዋል

News today, Technology

ባህር ስር የሚጓዘው “ፖሲዶን” ኒውክሌር ታጣቂው የሩሲያ ድሮን

ሰርጓጅ ድሮኑ ሱናሚዎችን በማስነሳት የጠላት ኢላማን የማጥፋት አቅም አለው

ከባህር ስር 1 ሺህ ሜትር ጥልቀት ላይ የሚጓዘው ድሮኑ፤ እስከ 10 ሺህ ኪ.ሜ ድረስ መሸፈን ይችላል

ሩሲያ በያዝነው የፈረንጆቹ 2022 ይፋ ካደረገቻቸው አውዳሚ የጦር መሳሪያዎች ውስጥ “ፖሲዶን” የባህር ሰርጓጅ ድሮን አንዱ ነው።

“ፖሲዶን” ሰርጓጅ ድሮን የምጽአት ቀን የሚል መጠሪያ በተሰጠው የሩሲያው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ላይ የሚገጠሙ ሲሆን፤ ከሰርጓጅ መርከቡ ላይ የሚወነጨፉ መሆኑም ታውቋል።

“ፖሲዶን” የሩሲያ ኒውክሌር ድሮን ምን የተለየ ያደርገዋል?

“ፖሲዶን” በባህር ስር የሚጓዝ ድሮን ሲሆን፤ የኒውክሌር አረር የሚሸከም ግዙፍ የሆነ የባህር ሰርጓጅ ድሮን ነው።

የውሃ ስር ድሮን ፕሮጀክቱ መሰራት እንደተጀመረ የሚያሳየው መረጃ በ2015 ላይ እንደወጣ የዘገበው ኢውሮ ኒውስ፤ የድሮኑ ዋነኛ ዓላማም የባህር ዳርቻ ላይ የሚገኙ የጠላትን ወታራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ስፍራዎችን ለማውደም ነው።

“ፖሲዶን” የኒውክሌር የባህር ሰርጓጅ ድሮን 20 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ከባህር ስር እስከ 1000 ሜትር ጠልቆ መጓዝ እንደሚችልም ተመላክቷል።

የባህር ስር ድሮኑ እስከ 10 ሺህ ኪሎ ሜትር ድረስ የማካለል እና የጠላትን ኢላማ የመምታት አቅም ያለመው መሆኑም ተመላክቷል።

አብዛኛው የባህር ስር ድሮኑ ዝርዝር መረጃዎች እስካሁን በሚስጥር የተያዙ ሲሆን፤ ካለው ፍጥነት የተነሳ መከላከልም ሆነ ለማስቆም አዳጋች እንደሆነ ግን ተነግሯል።

የባህር ስር ድሮኑ ሰው ሰራሽ ሱናሚ ማእበሎችን ማስነሳት ይችላል የተባለ ሲሆን፤ እስከ 500 ሜትር ርዝመት ያለው ሱናሚ በማስነሳትም የባህር ዳርቻ ከተሞችን እንዳልነበሩ አድርጎ ሙሉ በሙሉ ማውደም ይችላል ተብሏል።

የብሪታኒያው ዴይሊ ሜይል ጋዜጣ እንዳስነበበው እነዚህን ድሮኖች የተሸከመው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ በነጭ ባህር ላይ መታየቱን እና በወቅቱም ዲሚትሪ ዶንስኮይ የተባለ ሌላ የጦር መርከብ አብሮት እንደበረ ይታወሳል።

News today, Technology

የጃፓን ተመራማሪዎች የሰዎች ቀለድ የሚያስቀው ሮቦት ሰርተዋል

ሮቦቱን ሳቅ ያስተማሩት የጃፓን ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ናቸው

የሚስቀው ሮቦት ፕሮጀክት ሮቦቶችን ከሰው ልጅ ጋር የማመሳሰል እቅድ አንዱ ካል ነው

የጃፓን ተመራማሪዎች ከዚህ በፊት ያልተመለደ “በሰዎች ቀልድ የሚስቅ ሮቦት” መስራታቸውን ከሰሞኑ አስታውቀዋል።

ሮቦቱን ሳቅ ያስተማሩት የጃፓን ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ሲሆኑ፤ ዋና አላማዉም ሮቦቶች የበለጠ ከሰው ልጆች ጋር ለማመሳሰል እንደሆነም ተነግሯል።

ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ሮቦቱ ትክክለኛ የሰው ልጆችን ሳቅ እንዲስቅ ለማለማመድም ሰው ሰራሽ ክህሎት (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ) መጠቀማቸውን አስታውቀዋል።

ተመራማሪዎቹ ኤሪካ የሚል ስያሜ ባለው ሮቦት ላይ ሳቅን የማስተማር ስራውን እየሰሩ ሲሆን፤ ይህ ስራም በሰዎች እና በሮቦቶች መካከል ያለው ንግግሮች የበለጠ ተፈጥሯዊ እንዲመስሉ እንደሚያደርግ ተስፋ ሰንቀዋል።

ርዝመታቸው ከሁለት እስከ ሶሰስተ ደቂቃ የሚቆዩ ንግግሮች በሰዎች እና በኤሪካ ሮቦት መካከል የተደረገ ሲሆን፤ ይህም አዲሱን ሲሰተም ለመመኮር እንደተካሄደ እና ስራውም በጎ ውጤት እንደተገኘበት አስታውቀዋል።

ሮቦቶቹ የበለጠ ከሰዎች ጋር እንዲግባቡ እና በቀልዶች የምር እንዲስቁ ለማስቻል አሁንም ቀሪ ስራች እንደሚቀሩ አስታውቀዋል።

በሰዎች እና በሮቦቶች መካከል ልክ ንደጓደኛ መደበኛ ንግግሮች እንዲኖሩ ለማስቻል እየሰሩ መሆኑን ያስታወቁት ተመራማሪዎቹ፤ ይህንን እውን ለማድረግ እን ከ10 እስከ 20 ዓመት ሊያስፈልገን ይችላል ብላዋል።

News today, Technology

በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ላይ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር ገለፀ

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚጣለው የጉምሩክ ታሪፍ ዝቅተኛ እንደሚሆንም ሚኒስቴሩ አስታውቋል

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ ነፃ እንደሚደረጉ ተገለፀ

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኢንቨስትመንትንና አስመጪዎችን የሚያበረታታ እንዲሁም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም የታክስ ማሻሻያ ከውጭ የሚገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎች እና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው መሆኑን ከሚኒስቴሩ ማህበራዊ ገጽ ያኘነው መረጃ ያመለክታል።

እንዲሁም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ ነፃ እንደሚደረጉም ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በታክስ ማሻሻያው መሰረት የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን በተመለከተም ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ መደረጉን ሚኒስቴሩ ገልጿል

በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን በተመለከተም 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ ደግሞ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን፤ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ መወሰኑንም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ መኪናዎችን በኢትዮጵያ ጎዳናዎች ላይ መታየት ከጀመሩ ዋል አደር ያሉ ሲሆን፤ ግሪን ቴክ አፍሪካ የተባለ ኩባያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን በኢትዮጵያ መገጣጠም ሊጀምር መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚይ ኢንጅነር ቅደም ተስፋዬ ከወራ በፊት ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አሁን ለይ ከ320 በላይ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት መቻሉን አስታውቀው ነበር።

የተሸከርካሪዎቹ ዋጋ በነዳጅ ከሚሰሩት መኪኖች ጋር ተቀራራቢና እኩል እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የጉምሩክ፣ ሱርታክስታና ተጨማሪ እሴት ታክስ ባይኖር ግን ዋጋቸው ከዚህ ይቀንስ እንደነበር መግለጻቸው ይታወሳል።

News today, Technology

በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር የሚጓዘው በራሪ ሞተር ሳይክል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ አዲስ በራሪ ሞተር ሳይክል ይፋ አድርጓል

በራሪው ሞተር ሳይክል በቀጣዩ 2023 ለገበያ ይቀርባል ተብሏል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የዓለማችን የመጀመሪያው በራሪ ሞተር ሳይክል ከሰሞበኑ ይፋ አድርጓል።

በአሜሪካ ዴትሮይት እየተካሄደ ያለው አውቶሞቲቭ ሾው ላይ የቀረበው በራሪው ሞተር ሳይክል የበርካቶችን ቀልብ ይዟል።

በራሪ ሞተር ሳይክሉን የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የሰራው ሲሆን፤ ሞተር ሳይክሉ ለ40 ደቂቃ ያክል አየር ላይ መብረር ይችላል።

ዚቱሪስሞ በራሪ ሞተር ሳይክሉ በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መብረር የሚችል መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል።

የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ ኩባንያው ከበራሪ ሞተር ሳይክል በተጨማሪ ድሮኖች እና በራሪ መኪናዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ በጃፓን መሸጥ ጀምሯል ያሉት ስራ አስፈጻሚው፤ በአሜሪካ እና በሌሎች የዓለም ሀገራት ከ2023 ጀምሮ ለገበያ ይቀርባል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ የተገመተለት ዋጋም 777 ሸህ ዶላር ነው።

8የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ እስከ ፈረንጆቹ 2025 ባለው ጊዜ በኤሌክትሪ የሚሰራውን በራሪ ሞተር ሳይክል ዋጋ ወደ 55 ሺህ ዶላር የመቀነስ ተስፋ እንዳለ አስታውቀዋል።

News today, Technology

ሚሳዔልና ተተኳሽ ቦምቦችን ጭኖ በሰዓት ከ2 ሺህ ኪ.ሜ በላይ የሚበረው “ሚኮያን ሚግ-35” ጄት

ሚኮያን MIG-35 ሩሲያ ካሏት አደገኛ የጦር ጄቶች ውስጥ አንዱ ነው

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት

እስከ ከ300 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ የሚገኙ የባሀር ላይና የአየር ላይ ጠላት ኢላማዎችን መለየት ይችላል

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት ሩሲያ ካሏት ጦር የውጊያ ጄቶች ውስጥ በአደገኛነቱ እና በፈጣንነቱ ብዙ ይነገርለታል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት በፈረንጆቹ 2007 የተመረተ ሲሆን፤ ሩሲያ አሁን ላይ ከዩክሬን ጋር ከገጠመችው ጦርነትን ጨምሮ በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ እንተጠቀመችበት ኤር ፎርስ ቴክኖሎጂ ድረ ገጽ አስነብቧል።

ተዋጊ ጄቱ ክሊሞቭ አር ዲ 33 MK የሚል መጠሪያ ያለው ሁለት ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ከመሬት ለመነሳት 122 ሜትር የመንደርደሪያ፤ ለማረፍ ደግሞ 137 ሜትር ርዝመት ቦታ ያስፈልገዋል።

በሰዓት ከ2 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ አየር ላይ የሚከንፈው ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት፤ በአንድ ጊዜ በተሞላለት ነዳጅ ከ3 ሸህ ኪሎ ሜትሮች ባለይ፤ እዛው አየር ላይ ነዳጅ ተከሞላለት ደግሞ ከ5 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ መጓዝ እንደሚችል ታውቋል።

ተዋጊ ጄቱ ፀረ መርከብ እና ፀረ አውሮፕላን ሚሳዔሎችን ጨምሮ የተለያዩ ተተኳሽ ቦምቦችን የመታጠቅ አቅም ያለው እንደሆነ ይነገራል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት ከሚታጠቃቸው እና ከሚያስወነጭፋቸው መሳሪያዎች መካከልም ሚግ-35 Kh-29TE ሚሳኤል እና KAB-500Kr TV ቦምቦች ተጠቃሽ ናቸው።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት አየር ክልልን ጦሶ የገባን የጠላት አውሮፕላን ከ160 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መለየት እንደሚችልም ኤር ፎርስ ቴክኖሎጂ ድረ ገጽ መረጃ ያመለክታል።

ታዲያ ይህ የጦር ጄት የአየር ክልል ጥሶ የገባን የጠላት አውሮፕላን ሚግ-35 Kh-31P ፀረ-ራዳር ሚሳኤል በመጠቀም የሚያወድም መሆኑ ተነግሯል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት በተጨማሪም የሀገርን የውሃ ክልል ጥሶ የገባን መርከብ ከ300 ኪሎ ሜትር ላይ የመለየት ብቃት ያለው ሲሆን፤ አስፈላጊ ሆኖ ከገተኘ Kh-31A ፀረ-መርከብ ሚሳኤል በማስወንጨፍ መምታት ይችላል ተብሏል።

News today, Technology

አሜሪካ ቲክቶክን ጨምሮ በሌሎች የቻይና ኩባንያዎች ላይ እገዳ ልትጥል እንደምትችል ተገለጸ

እገዳዎቹ የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በአሜሪካ እንዳይሰሩ ማድረግንም ይጨምራል

አሜሪካ ቲክቶክን ጨምሮ በሌሎች የቻይና ኩባንያዎች ላይ እገዳ ልትጥል እንደምትችል ተገለጸ።

ሁለቱ የዓለማችን ባለ ብዙ ሀገራት አሜሪካ እና ቻይና የማይግባቡባቸው አጀንዳዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል።

ሁለቱ ሀገራት በተለይም በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአስተዳድር ጊዜ ከቻይና ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ ገብተው የነበረ ሲሆን ሁለቱም ወገኖች ወደ ሀገራቸው በሚገቡ ምርቶች ላይ እገዳዎችን ሲጥሉ ነበር።

በታይዋን ጉዳይ እንደ አዲስ መካረር ውስጥ የገቡት ቻይና እና አሜሪካ አሁን ደግሞ ከምርት እገዳ ወደ ተቋማት እገዳ እየገቡ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።

አሜሪካ በተለይም በፍጥነት እያደጉ የመጡ የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ስጋት ላይ የጣሏት ሲሆን ቲክቶክ ደግሞ ዋነኛው ነው።አሜሪካ አጫጭር ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በመልቀቅ ተወዳጅ የሆነው የቻይናው ቲክቶክ በአሜሪካ እገዳ ሊጣልበት እንደሚችል ዘገባው ጠቅሷል።

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና ቲክቶክን ለአሜሪካ ኩባንያዎች ካልሸጠች እገዳ እንጥላለን ማለታቸው ይታወሳል።የአሁኑ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳድርም ቲክቶክ ኩባንያን ጨምሮ ሎሎች የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በአሜሪካ እንዳይሰሩ እገዳ እንደሚጥል ተገልጿል።

እገዳው የሚጣልባቸው የቻይና ኩባንያዎች ማንነት፣ የእገዳው መጠን እና አይነትን በሚመለከት ኋይት ኃውስ መንግስት እና የአሜሪካ ኮንግረስ በውይይት ላይ እንደሆኑ ተገልጿል።

አሜሪካ ከአንድ ሳምንት በፊት መነሻቸውን ከቻይና ያደረጉ 44 በረራዎች ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ እገዳ መጣሏ ይታወሳል።

News today, Technology

ቻይና “አሜሪካ 10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ፈጽማብኛለች” አለች

ቻይና የተፈፀመባት የመረጃ ጠለፋ በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም የተመራ ነው ብላለች

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ተቋም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃቶቸን እንደፈጸመባት ቻይና ገለጸች።

በአሜሪካ የሳይበር ጥቃቶችም 140 ጊጋ ባይት ጠቃሚ መረጃዎች መሰረቃቸው እንዳልቀረ የቻይና ብሄራዊ የኮምፒውተር ቫይረስ ግብረ መልስ ኃይል እና ኪሆ የተባለው የኢንተርኔት ደህንነት ተቋም ባጋራ ባካሄዱት ምርመራ አስታውቀዋል።

ተቋማቱ ምርመራውን ማካሄድ የጀመሩት የቻይና ሰሜናዊ የፖሊ ቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር ላይ የሳይበር ጥቃት እንደተፈፀመበት ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

ተቋማቱ ጥቃቱን የፈፀመውን ኔትዎርክት ዱካ ተከትለው ባደረጉት ምርመራም ጠላፊው በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም አካል በሆነው ትሮይድ አክሰስ ኦፕሬሽን ቢሮ እንደተፈጸመ ደርሰንበታል ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲ ላይ በተፈፀመው የሳይበር ጥቃት በቀጥታ 13 ሰዎች መሳተፋቸው እና የመረጃ ጠላፊዎ የዩኒቨርሲቲዉን የመረጃ ደህንነት መጠበቂያ (ፋየርዎል) ለማለፍ ከ41 በላይ መሳሪያዎችን መጠቀማቸው ተነግሯል።

ጠላፊዎቹ ማንነታቸውን ለመሸፈን ኢራን፣ ደቡብ ኮሪ እና ጃፓንን ጨምሮ በ17 ሀገራት አይ.ፒ እቀያየሩ ሲጠቀሙ ነበርም ብሏል ተቋማቱ ባወጡት መረጃ።

ምርመራውያን ያካሄዱት ተቋማት ወደፊት የአሜሪካ የመረጃ ጠለፋ እና የስለላ ዘዴቆች እና መሰሳሪያዎችን ዝርዝር ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርመራ ውጤቱን ተከትሎ ምለሽ ሰጠ ሲሆን፤ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ፤ ቻይና ኢንዲህ አይነት ተጋባራትን በጽኑ ታወግዛለች ብለዋል።

አሜሪካ ከሳይበር ጥቃት ተግበሯ ልትታቀብ ይገባል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ቻይና የኔትዎርክ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከዓለም አቀፉ ማህበረስበ ጋር ትሰራለች ሲሉም ተናግረዋል።

News today, Technology

ሁዋዌይ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሳተላይት የሚሰራ ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ አደረገ

ሁዋዌይ ሜት 40 ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ይፋ የተደረገው

የቻይናው የቴክኖሎጂ ቁሶች አምራች ሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልኩን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉ ተነግሯል።

አዲሱ የህዋዌይ ስማርት ስልክ ከዚህ በፊት በስማርት ስልኮች ላይ ያልተለመደ የሳተላይት ኮሙዩኒኬሽን የተገጠመለት መሆኑን ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

በዚህም ስማርት ስልኩ ከጂ.ፒ.ኤስ ተመሳሳይነት ባለው በቻይናው ቤይ-ዶው ናቪጌሽን ሳተላይት ሲስትም (BDS) ኔትዎርክ አማኝነት በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚባይል ኔትዎርክ ባይኖርም መስራት ይችላል።

 በተጨማሪም አዲሱ ሜት 50 ስማርት ስልክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአሜሪካው የጎግል አንድሮይድ ስማርት ስልክ በመላቀቅ ቻይና በራሷ ባመረተችው አዲስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ለገበያ የሚቀርብ ይሆናል ነው የተባለው።

ይህም ባትሪው ሊዘጋ 1 ፐርሰት እየቀረው 3 ሰዓት እንደቆይ ማድረግ እንደሚያስችልም ኩባያው አስታውቋል።

አዲሱ የሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልክ የባትሪ አቅም 4460 mAh መሆኑን ኩባያው አስታውቋል።

ስማርት ስልኩ ከጀርባው 4 የካሜራ ሌንሶች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሌንሶቹም 50 ሜጋ ፒክስል፣ 13 ሜጋ ፒክሰል እና 12 ሚክስል ናቸው።

ከፊትለፊት አሊያም ሰለፊ ካሜራው ደግሞ 1 ሲሆን፤ የሌንሱ ምስል የማንሳት ጥራትም 13 ሜጋ ፒከስል ነው ተብሏል።

ሁዋዌይ ሜት 40 የተባለ ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ የተደረገው።

በርካቶቸ ሁዋዌይ ስማርት ስልኩን ይፋ ሳያደርግ ይህን ያክል የቆየው አሜሪካ በኩንያው ላይ በጣለችው ማእቀብ ሳቢያ ሳይሆን እንዳልቀረ ያምናሉ።

News today, Technology

የባህር ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪው አዲሱ የቻይና ድሮን


ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ድሮኑ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል
ድሮኑ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘር ይችላል

ቻይና በአይነቱ ለየት ያለ ባህር ስር እንደ ሰርጓጀ አየር ላይ ደግሞ ድሮን የሚሆን መሳሪያ እየሰራች መሆኑ ተሰምቷል።

የቻይና ተመራማሪዎች እየሰሩት ነው የተባለው አዲሱ ስተሊዝ ድሮን ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ሲሆን፤ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል።

ሚሳዔል አስወንጫፊው የቻይና CH-7 የውጊያ ድሮን
በዓለም ላይ ካሉ “በጣም አደገኛ” የጦር መርከቦች አንዱ የሆነው የቻይናው “ለሃሳ” መርከብ
የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አሁን ላይ ለናሙና የሚሆን አዲሱን ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪ ድሮን በመስራት ሙከራ እያደረጉበት መሆኑም ታውቋል።

ሳውዝ ቻይና ሞኒተሪንግ ፖስት ጋዜጣ ባወጣው መረጃ፤ ድሮኑ አራት ተሸከርካሪ ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሁለቱ ከፊት ሁለቱ ደግሞ ከኋላ የተገጠሙ ናቸው።

ደሮኑ በባህር ስር በሚሆንበት ጊዜ ሁለቱ ክንፎቹን በማጠፍ የሚቀዝፍ ሲሆን፤ ይህም በጣም ዘመናዊ የሆነ የሰርጓጅ መርከብ ቅርጽ እንዲላበስ የሚያደርገው ነው።
ከባህር በመውጣት አየር ላይ በሚንሳፈፍበት ወቅት ደግሞ ክንፎቹን የሚዘረጋ ሲሆን፤ በሰዓት እስከ 120 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር የሚችል መሆኑንም የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታውቀዋል።

ድሮኑ በባህር ስር እንዲሁም በአየር ላይ ፈጣን እና የረጅም ርቀት ተልእኮዎችን በቀላሉ መከወን የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር አንግ ሂሶንግ ገልፀዋል።

“J-20” ዘመናዊዎቹ የቻይና ተዋጊ ጄቶች
አዲሱ ድሮን ከራዳር እይታ ውጪ እንዲሆን ታስቦ መሰራቱን የሚያነሱት የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ትክክለኛ ጥቅሙ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር መቻሉ እንደሆነም ተናግረዋል።

ድሮኑ መቼ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የቻይና ጦር ይታጠቀዋል በሚል ላይ እንዲሁም ድሮኑ ምን አይነት መሳሪያዎችን መታጠቅ ይችላል በሚለው ላይ የወጣ መረጃ የለም።

News today, Technology

በስህተት የጣለውን ቢትኮይን በ13 ሚሊዮን ዶላር እያፈላለገ ያለው ግለሰብ


ከ10 ዓመታት በፊት ነው። ጄምስ ሃዌልስ ያስቀመጠውን ቢትኮይን ረስቶ የኮምፒውተሩን የመረጃ ቋት (ሃርድ ድራይቭ) አውጥቶ ጣለው።

ጄምስ ተዝናግቶ የወረወረው ቢትኮይን ዘንድሮ ባለው ገበያ 184 ሚሊዮን ዶላር ሊያወጣ ይችላል።

ይህ የከነከነው ጄምስ ከዓመታት በፊት የጣለውን ቢትኮይን ሚሊዮን ዶላር ከፍሎ ሊያስቆፍረው አስቧል።

የሰውዬው ‘ሃርድ ድራይቭ’ ኒውፖርት በተሰኘችው የዩናይትድ ኪንግደም ከተማ ቆሻሻ መጣያ ሥፍራ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል።

ጄምስ ይህ ውድ ቁስ ከተገኘለት ከቢትኮይኑ 10 በመቶውን ቆንጥሮ ከተማዋን የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቃል ገብቷል።

ነገር ግን የከተማዋ ምክር ቤት የቆሻሻ መጣያውን መቆፈር ሥነ-ምኅዳራዊ (ኢኮሎጂካል) ቀውስ ያስከትላል እያለ ነው።

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (አይቲ) ባለሙያው ጄምስ ከዘጠኝ ዓመት በፊት በፈረንጆቹ 2013 ነበር፤ 8 ሺህ ቢትኮይን ያቀፈውን ሃርድ ድራይቭ ጠርጎ የጣለው።

ወቅቱም ቢትኮይን የተሰኘው ዲጂታል የመገበያያ ገንዘብ ብቅ ብቅ ማለት የጀመረበት ነበር።

ቢትኮይን ገበያው ላይ የሚታወቀው በሚዋዥው ዋጋው ነው።

ለምሳሌ የጄምስ ቢትኮይን ዋጋ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት [2021] 256 ሚሊዮን ዶላር ደርሶለት ነበር።

ነገር ግን ከዘንድሮው ዓመት መባቻ ጀምሮ ዋጋው አሽቆልቁሏል።

ጄምስ በተደጋጋሚ ለኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ቆሻሻ ማከማቻው ይቆፈርልኝ ብሎ ቢያመልክትም ጥያቄው ሰሚ አጥቷል።

ይህ ያታከተው ግለሰብ አሁን ሃርድ ድራይቩ ከተገኘ 10 በመቶ ገቢውን ለከተማዋ የክሪፕቶከረንሲ ማስፋፊያ ለመስጠት ወስኗል።

ነገር ግን የጄምስን መዳፍ የምታክል ቁስ ለማግኘት ሲል ከተማ አስተዳደሩ በርካታ ወጪ አውጥቶ ለዓመታት የተከማቸውን ቆሻሻ ይቆፍር እንደሁ አልታወቀም።

ከተማ አስተዳደሩ የቆሻሻ ማከማቻውን ማመስ አካባቢውን ሊበክለው ይችላል የሚል ስጋት አለው።
ጄምስ ደግሞ “እኔ ማከማቻውን የማስቆፈር አቅም እንዲሁም አደጋ ሳያደርስ የሚያስስ ባለሙያ አለኝ” ይላል።

“እርግጥ ነው ቆሻሻ ማከማቻ መቆፈር ራሱን የቻለ ትልቅ ሥራ ነው” ይላል ጄምስ።

“ነገር ግን ማስቆፈሪያ ወጪውን እችላለሁ። የሰው-ሠራሽ ልኅቀት [አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ] ባለሙያ አስመጥተናል። ሃርድ ድራይቩን ነቅሎ የሚያወጣ ቴክኖሎጂ አለ።”

ግለሰቡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከበቢያዊ አደጋን የሚመረምር ቡድን ማዘጋጀቱን ይገልጣል።

“በሁሉም ዘርፍ የተካኑ ልምድ ያላቸው ሙያተኞች ይዣለሁ። ከተፈቀደላቸው ይህንን ሥራ በብቃት መከውን የሚችሉ ናቸው።”

ነገር ግን ሃርድ ድራቩን ማግኘት ብቸኛው ሥራ አይደለም። ይህ የመረጃ ማከማቻ ቁስ ቢገኝ እንኳ ለመሥራቱ ማስተማመኛ የለም።

ይህ በርካታ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን ያቀፈው ቁስ ቢገኝ ጄምስ ሚሊየነር ይሆናል። ነገር ግን የቢትኮይንን የገበያ ዋጋ መገመት ከባድ ነው።

ቢሆንም የ37 ዓመቱ ግለሰብ የበርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ባለቤት ሊሆን ይችላል።

ጄምስ ገንዘቡ ተቆፍሮ ይውጣለት እንጂ፣ ያደገባትን ከተማ የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቆርጦ ተነስቷል።

“ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ሥራ ለመሥራት የሚያስችል ዕቅድ አስቀምጫለሁ” ይላል።

“አንደኛው ሥራ የቆሻሻ ማከማቻውን ማዘመን ነው። ከተቻለ በአካባቢው በነፋስ ኃይል የሚሠራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ እንገነባለን።”

የኒውፖርት ማኅበረሰብ የሚጠቀምበት የክሪፕቶከረንሲ ገበያ ለመዘርጋት ነው የጄምስ ዓላማ።

ለእያንዳንዱ የኒውፖርት ነዋሪ 61 ዶላር ዋጋ ያለው ቢትኮይን ለመስጠትም ቃል ገብቷል። በተከማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ደግሞ ክሪፕቶ ላይ የተመሠረቱ ፌርማታዎች ለመግንባትም አስቧል።

የኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ግን በተደጋጋሚ የሰውዬውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።

የከተማዋ ቃል አቀባይ “ቆሻሻ ማከማቻን በተለመከተ የተቀመጠ ሕግ አለን። ይህን ሕግ መከተል አለብን” ብለዋል።

“አንደኛው ጉዳይ ይህ የቆሻሻ ማከማቻ ከተቆፈረ በአካባቢው ማኅበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ሥነ ምኅዳራዊ አደጋ ነው። የጄምስ ዕቅድ ደግሞ ይህን አደጋ የሚያስከትል ነው። ይህን ልንቀበለው አንችልም። በሕጉ መሠረት እንዲያውም ከግምት ውስጥ ልናስገባው የምንችለው ሐሳብ አይደለም።”

News today, Technology

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን መገጣጠም ሊጀምር መሆኑን ግሪን ቴክ አፍሪካ ገለፀ


እስካሁን 320 በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ሀገር ቤት ገብተዋል
ግሪን ቴክ አፍሪካ በወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን መገጣጠም እጀምራለሁ ብሏል

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ በሁለት ወይም ሶስት ወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም እንደሚጀምር አስታወቀ።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚይ ኢንጅነር ቅደም ተስፋዬ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኩባንያው የአሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈም በሀገር ቤት ለማምረት ማቀዱን አስታቀዋል።

በዚህም መሰረት ድርጅቱ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች የመኪና መገጣጠም ስራን ይጀምራል ነው ያሉት።
አሁን ለይ ከ320 በላይ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት መቻሉን የገለጹት ኢ/ር ቅደም፤ ተሸከርካሪዎቹ 100 በ 100 በባትሪ የሚሰሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።

የተሸከርካሪዎቹ ዋጋ በነዳጅ ከሚሰሩት መኪኖች ጋር ተቀራራቢና እኩል እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የጉምሩክ፣ ሱርታክስታና ተጨማሪ እሴት ታክስ ባይኖር ግን ዋጋቸው ከዚህ ይቀንስ እንደነበር ገልጸዋል።

ተሸከርካሪዎቹን ከውጭ ሀገራት እያሰገቡ ከመሸጥ ባለፈም በሀገር ውስጥ ለመገጣጠም መታቀዱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።ይህም በሶስት ወይም በሁለት ወራት ውስጥ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

የመገጣጠሙ ሂደት በዚህ ሲቀጥል፤ በአምስት አሊያም በስድስት ዓመታት ውስጥ 60 በመቶ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት እንደሚቻል ነው የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው።

መኪኖቹን በሀገር ቤት ከመገጣጠም የሚያስችል የሰለጠነ የሰው ኃይል በቻይና እየሰለጠ እንደሆነ የገለጹት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፤ ተጠቃሚዎች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ብለዋል።
መኪኖቹን በቤት ውስጥ ቻርጅ ማድረግ እደሚቻልና ከ 4 እስከ 6 ሰዓታት ውስጥ ተሽከርካሪዎቹ 80 በመቶ ቻርጅ እንደሚያደርጉም ነው የተገለጸው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በፍጥነት ቻርጅ እንዲያደርጉ ለማድረግ 40 ቦታዎች ተዘጋጅተዋል ተብሏል፡፡

አንዱ ፈጣን ቻርጀር ማድረጊያ በአንድ ጊዜ ሁለት መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ የሚችል ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ 80 መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ ይቻላል ተብሏል።

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ የአህጉሩ ሕዝብ የኢነርጂ ሃይል ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በምስራቅ፣ በምእራብ እና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት ውስጥ እየሰራ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለአል ዐይን አማርኛ አስታውቀዋል።

ኩባንያው፤ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ አፍሪካ ሀገራት በማስገባት ስራውን መጀመሩን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው፤ ከዚህ ባለፈም ድርጅታቸው፤ በታዳሽ ሃይል እና በአዳዲስ የኢነርጂ ምንጮች ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

News today, Technology

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን
በሱፐርሶኒክ ፍጥነት የሚበረው አውሮፕላኑ በሰዓት ከ1 ሺህ 200 ኪ.ሜ በላይ ይጓዛል
እስከ 16 ሺህ ኪ.ግ ቦምቦችንና ክሩዝ ሚሳዔሎችን ታጥቆ ያለምንም ችግር መብረር ይችላል

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በገጠመችው ጦርነት ከተጠቀመችባቸው የጦር አውሮፕላኖች ውስጥ “Tu-160” አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

በጣም ግዙፍ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጦር አውሮፕላን በሶቪየት ህብረት ወቅት ማለትም በፈረንጆቹ 1981 ወደ አገልግሎት የገባ ሲሆን፤ በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት እስካሁን እያገለገል ይገኛል።

በሰዓት ከ6 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚምዘገዘገው ሃይፐርሶኒክ ሚሳዔል
ሩሲያ አውሮፕላኑ ላይ በፈረንጆቹ 2008 አዳዲስ ማሻሻዎንብመ በማድረግ ይፋ ያደረገች ሲሆን፤ Tu-160R በሚል ስያሜ የአየር ኃይሏን ዳግም አስታጥቃለች።
ለመሆኑ ግዙፉ Tu-160 የጦር አውሮፕላንን ምን የተለየ ያደርገዋል?

የአወሮፕላ ቁመት 54.1 ሜትር ሲሆን፤ ክንፉ ርዝማኔም 35.6 ሜትር ይረዝማል፤ ክንፎቹ ላይ አራት ኩዜንትዞቭ NK-321 ቱርቦፋን ሞተሮች ተገጥመውለታል።

አውሮፕላኑ ከመሬት እስከ 52ሺ ገጫማ ወደላይበመነሳት መብረር ይችላል ተብሏል።

ሱፐርሶኒክ ፍጥነት እንዳለው የተነገረው Tu-160 የጦር አውሮፕላን በሰዓት 1,236 ኪሎ ሜትሮች መብረር የሚችል መሆኑም ይነገርለተል።

“አደገኛው” የሩሲያ “ዛላ ኬ.ዋይ.ቢ” ድሮን
Tu-160 የጦር አውሮፕላን 16,330 ኪ.ግ የሚመዝኑ ቦምቦችን ተሸክሞ በሱፐርሶኒክ ፍጥነት መብረር የሚችል ነው ተብሏል።

አውሮፕላኑ ከቦምቦች በተጨማሪም Kh-101 እና Kh-102 የሚባሉ ክሩዝ ሚሳኤሎችን መታጠቅ የሚችል እና ኢላማውን በአግባ የሚመታ መሆኑም ተነግሯል።

News today, Technology

አል ዛዋሂሪን የገደሉት እጅግ ዘመናዊና ሚስጥራዊ የአሜሪካ ሚሳኤሎች

እጅግ ዘመናዊ የተባሉት ሚሳኤሎቹ በፕሬዝዳንት ኦባማ ዘመን የተሰሩ ናቸው

 2022/8/2 17:14 GMT

ሚሳዔል አስወንጫፊ የአሜሪካ ድሮን

የአሜሪካ ሚሳኤሎች አልዘዋሪሂን ያለ አንዳች የጎላ የፍንዳታ ድምፅ የገደሉት

መነጋገሪያ ከሆኑ ሰሞነኛ ቀዳሚ የሚዲያ ጉዳዮች መካከል አንዱና ቀዳሚው የአልቃይዳው መሪ አል ዛዋሂሪ መገደል ነው።

የቀድሞው የሽብር ቡድኑ መሪ ኦሳማ ቢን ላደን የቅርብ ሰውና አማካሪ አልዛዋሂሪ በቢላደን እግር ተተክቶ ቡድኑን መምራት ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ሆኖም ላለፉት 20 ገደማ ዓመታት ልክ እን ቢላደን ሁሉ አልዛዋሪን ስታድን የነበረችው አሜሪካ መግደሏን ትናንት ሰኞ አስታውቃለች።

አልዛዋሂሪ በአፍጋኒስታን መገደሉን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ይፋ አድርገዋል።

ሆኖም የ71 ዓመቱ ግብጻዊ ቀዶ ጠጋኝ ሐኪም አገዳደል አሁንም ብዙዎችን እንዳስደመመ ነው። አልዛዋሂሪ ያለ አንዳች ከባድ ፍንዳታ እና የከፋ ጉዳት እንደተገደለ መነገሩም ብዙዎችን ለግርምት ዳርጓል።

ከሞቱ አሟሟቱ እንዲሉም በሁኔታው የተገረሙ ብዙዎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃኑን ጨምሮ ስለሁኔታው እየጠየቁ ነው።

ቁንጮው የሽብር ቡድን መሪ እንዴትና በምን ተገደለ የሚሉ መጣጥፎችን በማስነበብም ላይ ይገኛሉ።

ሰው አልባዎቹን (ድሮን) ጨምሮ ሌሎችም የጦር አውሮፕላኖች ዒላማቸውን የሚያደባዩት እንደ ነጎድጓድ በሚያስገመግም ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፅ ታጅበው ነው የሚለው ዘ ናሽናል አልዛዋሪን የተገደለበት ሚሳኤል ግን ድምፅ አልባ እና ዒላማውን ብቻ ነጥሎ የመታ ነው የሚል ሰፊ ሃተታን ይዞ ወጥቷል።

አልዛዋሪ በመኖሪያ ቤቱ በረንዳ ላይ ሳለ የተገደለበት ሚሳኤል ምንነቱ በውል ባይገለጽም አዲስና የተለየ ነው ሲል የሚያትተው ዘ ናሽናል የጦር ተንታኞች መሳሪያው ምናልባትም ‘በራሪው ጊንሱ’ ወይም

‘R9X Hellfire’ በሚል ከሚታወቁ እጅግ ዘመናዊ የአሜሪካ የሚሳኤል ጦር መሳሪያዎች መካከል አንዱ ሳይሆን እንዳልቀረ መናገራቸውን አስቀምጧል።

መሳሪያው ‘ኒንጃ ሄልፋየር’ የሚል ቅጽል መጠሪያ እንዳለውሞ ነው ሃተታው የሚጠቁመው።

የጦር መሳሪያው ምንነት

‘በራሪው ጊንሱ’ በሚል ይጠራሎል የተባለለት እጅግ ዘመናዊው የሚሳኤል ጦር መሳሪያ ግለሰቦችንና የተለዩ ዓላማዎችን ነጥሎ ለመምታት በማሰብ የተሰራ ነው።

ዒላማውን ነጥሎ ለመምታት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ይነገራል። በመኪና ውስጥ ከሚጓዙ ሰዎች እንኳን አንዱን ብቻ ነጥሎ ለመምታት ያስችላልም ነው የሚባለው።

ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ሌሎች የሚሳኤል ዝርያዎች ቢኖሩም ይኼንኛው ግን የተለየ ስለመሆኑ ይነገርለታል።

መሳሪያው ወደ መሬት ተምዘግዝጎ ዒላማውን የሚመታና 45 ኪሎ ግራም የሚመዝን አረርን እንደሚሸከምም ነው አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን ለዎል ስትሪት ጆርናል የተናገሩት።

ሆኖም አሜሪካ ስለ በራሪው ስለሚባለው ጦር መሳሪያ አንዳችንም ነገር አላለችም። ስለ አሰራሩና ስለ ስሪቱ የተባለ ነገርም የለም።

አልዛዋሪን በመግደሉ ውጥን ንጹሃንን ከጉዳት ለመታደግ የሚያስችል ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረጉን ግን አልሸሸገችም።

ባሳለፍነው ነሐሴ በፈጸመችው ተመሳሳይ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 10 ገደማ ንጹሐን መገደላቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችትንና ውግዘትን ማስተናገዷ ይታወሳል።

በመሆኑም ይህን ተከትሎ አልዛዋሪን ለመግደል ለግለሰባዊ ዒላማዎች በሚል በፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ዘመን እንደተሰራ የተነገረለትን ‘በራሪው ጊንሱ’ን መጠቀሟ ተነግሯል።

የቀድሞው የአል ቃይዳ መሪ ቢን ላደን በፕሬዝዳንት ኦባማ ትዕዛዝ በፈረንጆቹ 2011 በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉ ይታወሳል።