News today, Politics, social life, Technology

በ11 የአለም ዋንጫዎች ላይ የታደሙት ብራዚላዊ

የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን በአርጀንቲና በ1978 የተመለከቱት ዳኔል ስብሩዚ በኳታርም የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ተከታትለዋል

“የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው ፤ በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዝግጁ ነኝ” ብለዋል

11 የአለም ዋንጫዎችን የተመለከቱት ብራዚላዊ በድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ስማቸውን ማስፈር ችለዋል።

ዳኔል ስብሩዚ የተባሉት የ76 አመት አዛውንት የሳኦሎ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ስብሩዚ በ1978 ወደ አርጀንቲና በማቅናት የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ከተመለከቱ ወዲህ አለምን በኳስ ምክንያት ዞረዋል።

የዘንድሮውን የኳታር የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዶሃ ገብተው ሰንብተዋል።

የ76 አመቱ አዛውንት በዶሃ 11ኛ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ሲመለከቱም የአለም የድንቃድንቅ መዝገብ ክብረወሰን ይዘዋል በሚል የምስክር ወረቀት ሰጥቷቸዋል።

የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው የሚሉት ስብሩዚ ፤ የአለም ዋንጫ ከመልከ ብዙ ተሰጥኦ ባለቤቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑን አንስተዋል።

ከአርጀንቲና እስከ ኳታር አለም ዋንጫን ለመመልከት ሲጓዙም የብራዚልን ባህልና ወግ ሲያስተዋውቁ እንደነበር ተናግረዋል።

ባለፉት 44 አመታት በተለያዩ አልባሳት አጊጠው ብራዚልን እየደገፉ የሳኦ ፖሎን ባህል በስፋት ያስተዋወቁት ስፖርት አፍቃሪ፥ የአለም ዋንጫን በስታዲየም ከመመልከት የሚያስቆመኝ ሞት ብቻ ነው እያሉ ነው።

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ በሚያዘጋጁት የ2026 የአለም ዋንጫ ለምታደምም ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በራሳቸው የተያዘውን ክብረወሰን ለማሻሻል ተስፋ አድርገዋል።

News today, Technology

የበርካቶችን ቀልብ የሳበው የቻይና “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

“J-20” ተዋጊ ጄት ዡሃይ የቻይና የአየር ትርኢት ላይ ለእይታ ቀርበዋል

“J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

የ2022 የቻይና የአየር ትርኢት በደቡባዊ የሀገሪቱ ከተማ ዡሃይ መካሄድ ላይ ሲሆን፤ “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት ለእይታ ቀርቧል።

የቻይና ሕዝብ ነፃ አውጪ ጦር ተብሎ የሚጠራው የቻይና ጦር የታጠቀው “J-20” ስውር ተዋጊ ጄቶች ዙሃይ ሰማይ ላይ መታየታቸው ለቻይና ኤር ሾው የበለጠ ድምቀትን ጨምሯል።

ለቻይና ኤር ሾው ላይ የቻይና አየር ሃይል ተዋጊዎች እና “የአየር ኤሮባቲክስ” ቡድን በዙሃይ ታላቅ የአየር ትርኢት ቢያቀርቡም አራት ጄ-20 ስውር ተዋጊዎች የተመልካችን አይን ስበዋ ነው የተባለው።

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

“J-20” ተዋጊ ጄቶች የመጀመሪያዎቹ ስሪቶች በሩሲያ የተመረቱ ሞተሮችን ይጠቀሙ የነበረ ሲሆን፤ በኋላ ላይ ግን ቻይና በራሷ ባመረተችው መንትያ ሞተር እንደተካች ይነገራል።

በችንግዱ ኤርክራፍት ግሩፕ የሚመረተው “J-20” ተዋጊ ጄት የመጀመሪያ በረራውን በፈረንጆቹ 2011 ያካሄደ ሲሆን፤ በ2017 በስራ ላይ እንደዋለም ተነግሯል።

በሰዓት እስከ 2 ሺህ 100 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር ይችላል የተባለለት “J-20” ተዋጊ ጄት፤ 19 ሺህ 390 ኪሎ ግራም ክብደት አለው ተብሏል።

 “J-20” ተዋጊ ጄት ቻይና የዓለማችን ቀዳሚ ስውር ተዋጊ ጄት ተብለው ለሚነገርላቸው የአሜሪካ ኤፍ-22 እና ኤፍ-35 ተዋጊ ጅቶች የሰጠችው ምለሽ መሆኑ ይነገራል።

በአሁኑ ወቅት 200 J-20 ተዋጊ ጄቶች የቻይና ህዝቦች ነጻነት ሰራዊት ተብሎ በሚጠራው የቻይና ጦር አየር ኃይል አገልግሎት እየሰጡ ነው።

የቻይና አየር ክልሏ ለሚጥሱ የማንኛውም ሀገር ተዋጊ ጄቶች ምለሽ የምትሰጠው በእነዚሁ “J-20” ተዋጊ ጄቶች መሆኑ ተገልጿል።

News today, Politics

ኢትዮጵያ ተመድ ሩስያ ለዩክሬን ካሳ እንድትከፍል ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በመቃወም ድምጽ ሰጠች

የውሳኔ ሃሳቡን ኢትዮጵያን ጨምሮ 14 ሀገራት የተቃወሙት ሲሆን 73 ሀገራት ደግሞ ድምፅ ከመስጠት ታቅበዋል

ይህም ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ሀገራት ያልደገፉት የውሳኔ ሀሳብ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጎታል

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ትናንት ማምሻውን በሩስያ ላይ ያቀረበው አዲስ የውሳኔ ሃሳብ ተቃውሞ ገጥሞታል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ 14 ሀገራት ሩስያ በዩክሬኑ ጦርነት ላደረሰችው ጉዳት ካሳ እንድትከፍል የሚያስገድደውን የውሳኔ ሀሳብ ተቃውመውታል።

አረብ ኤሚሬትስን ጨምሮ 73 ሀገራት በድምፀ ተአቅቦ ማለፋቸውን ተከትሎም የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የመንግስታቱ ድርጅት ካወጣቸው አምስት የውሳኔ ሀሳቦች ሁሉ ይሁንታ የተነፈገው ሆኖ ተመዝግቧል።

የውሳኔ ሀሳቡ በጦርነቱ ለተገደሉና ለቆሰሉ ዩክሬናውያን ሞስኮ ካሳ እንድትከፍል የሚጠይቅ ነው።

በጦርነቱ የጠፋውን የሰው ህይወትና የደረሰውን የንብረት ውድመት የሚያጣራ አለም አቀፍ ቡድን እንዲዋቀርም ተመላክቷል በዚሁ የውሳኔ ሀሳብ።

ዩክሬን – “የውሳኔ ሃሳቡ ፍትህ ለማስፈን ትልቅ ተስፋ ነው”

በመንግስታቱ ድርጅት የዩክሬን አምባሳደር ሰርጌ ኪይልይስታይ፥ ሩስያ ዩክሬንን ለማፈራረስ የመጨረሻ አቅሟን ተጠቅማለች ብለዋል።

“ከመኖሪያ ህንፃዎች እስከ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች ያላፈራረሰችው የህዝብ ተቋም የለም፤ ባለፈው ወር ብቻ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ጥቃት አድርሳ ግማሽ ዩክሬን በጨለማ ተውጧል” ነው ያሉት አምባሳደሩ።

የሩስያ ወታደሮች ይዘዋተው በቆዩ የዩክሬን ከተሞች የፈፀሟቸውን ወንጀሎችም በማንሳት ሞስኮ ተጠያቂ እንድትሆን የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ አድንቀዋል።

ዩክሬንን መልሶ የመገንባቱ ስራ ሲካሄድ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን የመካስ እና ፍትህን የማስፈኑ ጉዳይም እኩል ሊካሄድ እንደሚገባም አብራርተዋል።

ኬቭ በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት ሳትጨምር ሳትቀንስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ ለማድረግ መዘጋጀቷንም በመጥቀስ የውሳኔ ሃሳቡን ፍትህን ለማስፈን የተስፋ ብርሃን ነው ብለውታል።

ሩስያ – “የውሳኔ ሀሳቡ ህጋዊ ያልሆነና ተፈፃሚነት የሌለው ነው”

በመንግስታቱ ድርጅት ሩስያን የወከሉት ቫስሊ ንቤንዚያ በበኩላቸው፥ የውሳኔ ሀሳቡ በአለም አቀፉ ህግ ተቀባይነት የሌለውን ነገር ህጋዊ ለማስመሰል የሞከረና ተፈፃሚነት የሌለው ነገር ነው በሚል ተቃውመውታል።

ምዕራባውያን እንዳይንቀሳቀስ ያገዱትን በቢሊየን ዶላር የሚቆጠር የሩስያ ሃብት ለመዝረፍ የተቀነባበረ ነው፤ የመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤም ይህን ዘረፋ እንዲሸፍንላቸው የውሳኔ ሃሳቡን አቀርበዋል ሲሉም ሀገራት እንዲቃወሙት ጠይቀዋል።

የውሳኔ ሀሳቡን ማፅደቅ የምዕራባውያን የጦር መሳሪያ አምራቾችን ከመጥቀምና አለምን የባሰ ውጥረት ውስጥ ከመክተት ውጭ ፋይዳ እንደሌለውም አስገንዝበዋል።

ቻይና፣ ኢራን፣ አንጎላ፣ ቬንዙዌላን ጨምሮ 16 ሀገራት ለሩስያ ድጋፋቸውን በፊርማ ገልፀው፥ ፍትህ በተገቢው የህግ ስርአት እንጂ ምንም አይነት የህግ መሰረት በሌለው የውሳኔ ሃሳብ አይደለም ብለዋል።

በፀጥታው ምክር ቤት ድምፅን በድምፅ የመሻር ስልጣን ያላት ሩስያ የሚቀርቡባትን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አድርጋለች።

በጠቅላላ ጉባኤው ግን ይሄው ድምፅን በድምፅ የመሻር ስልጣን የላትም፤ ይሁን እንጂ የጠቅላላ ጉባኤው የውሳኔ ሃሳብ እንደ ፀጥታው ምክርቤት ህጋዊ አስገዳጅነት የለውም።

በካናዳ፣ ጓቲማሚላ፣ ኔዘርላንድና ዩክሬን አነሳሽነት የቀረበው የትናንቱ ሩስያ የጦር ካሳ ትክፈል የውሳኔ ሀሳብ በ94 ሀገራት ድጋፍ ቢፀድቅም በሞስኮ ላይ ህጋዊ ጫና አያመጣም።

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮልድሚር ዜለንስኪ ባስተላለፉት የቪዲዬ መልዕክት ግን ሩስያ ላደረሰችው ኪሳራ ሁሉ ካሳ መክፈሏ ከይቀሬ ነው ብለዋል።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በበኩላቸው፥ እንዳይንቀሳቀስ ያገዱትን የሩስያ ሃብት በካሳ ስም ለዩክሬን ለመስጠት ላሰቡት ምዕራባውያን የትኛውንም ምላሽ እንሰጣለን ሲሉ ዝተዋል።

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ቻይና ለጋራ ጥቅም ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ፈቃደኛ ነች አሉ

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ የሁለቱም ኃያላን ሀገራት ግንኙነት ጥሩ የሚባል እንዳልሆነ ይታወቃል

የጆ ባይደን አስተዳደር ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ያሏት የግንኙነት መስመሮችን ክፍት እንደሚያደረግ አስታውቋል

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ቻይና ለጋራ ጥቅም ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ፍቃደኛ ናት ማለታቸው የቻይና መንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በትናንትናው እለት በተዘጋጀውና በአሜሪካ – ቻይና ግንኙነት ዙሪያ ትኩረት የሚያደረገው የጋራ ብሔራዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት ከሆነ ሁለቱም ኃያላን ሀገራት ግንኙነታቸውንና ትብብር በማጠናከር ለዓለምና መረጋጋት ትልቅ ሚና መጫወት አለባቸው ብለዋል፡፡

ዢ ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በቅርቡ በኢንዶኔዥያ በሚካሄደው ቡድን-20 ስብሰባ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሊያደርጉት ከሚችሉት ውይይት በፊት መሆኑ ነው፡፡

ጆ ባይደን በበኩላቸው “አሜሪካ ከቻይና ጋር ግጭ አትፈልግም” ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዝዳንት ዢ ለሶስተኛ ጊዜ የቻይና መሪ ሆነው መመረጣቸውን ተከትሎ ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ያሏት የግንኙነት መስመሮችን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተውም ተናግራል ፕሬዝዳንቱ።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ የሁለቱም ሀገራት ግንኙነት ጥሩ የሚባል እንዳልሆነና በበርካታ ዛቻዎች የታጀበ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በተለይም በፔሎሲ ጉብኝት ምክንያት የተበሳጨችው ቻይና እና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብርን ጨምሮ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያም ንግግርና ውይይት የነበራት ቢሆንም ሁሉንም ማቋረጧ የሚታወስ ነው፡፡ 

ከዚህ ባለፈም የፕሬዝዳንት ዢ ሺን ፒንግ አስተዳደር፤ ሀገሪቱ ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን የማጓጓዝ፣ አደገኛ ዕጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን ማቋረጡን ገልጾ ነበር፡፡

አሜሪካ በበኩሏ የቻይና ድርጊት ተገቢ እንዳለሆነ ስትሞግት ቆይታለች፡፡

ያም ሆኖ የሁለቱም ኃያላን ሀገራት መሪዎች አሁን ላይ አዲስ ተረክ ይዘው መምጣታቸው የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሷል ተብሏል፡፡

በተለይም ሀገራቱም ሀገራት ከተባበሩ ለዓለም ሰላም የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ዋና ኃላፊ ከአሜሪካ-ቻይና ትብብር ውጭ የዓለም አቀፍ ቁልፍ ጉዳዮችን ለመፍታት የሚደረግ ‘ምንም መንገድ የለም’ ብለው እንደሚያምኑ በቅርቡ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

News today, Politics, social life

የሩሲያን ጦር ምልክት በተሸከርካሪው ላይ የቀረጸው ጀርመናዊ በ4 ሺህ ዩሮ ተቀጣ

የሀምቡርግ ከተማ ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ የሩሲያን ጦር ደግፏል በሚል የገንዘብ ቅጣት ተጥሎበታል

የሩሲያ ጦር በዩክሬን ለልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ከገባ ስምንት ወር ሆኖታል

የሩሲያን ጦር ምልክት በተሸከርካሪው ላይ የቀረጸው ጀርመናዊ በ4 ሺህ ዩሮ ተቀጣ።

የጀርመኗ ሀምቡርግ ከተማ ነዋሪ የሆነ አንድ ግለሰብ የግሉ ተሸከርካሪ ላይ በነጭ ቀለም የሩሲያ ጦር ምልክት የሆነውን የዜድ (“Z”) አርማ ቀርጿል ተብሏል።

ግለሰቡ ከስምንት ወራት በፊት ለልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ግዛት የገባውን የሩሲያ ጦር ደግፏል በሚል በሀምቡርግ ከተማ ፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶበታል።

ይህ ግለሰቡ ባሳለፍነው መጋቢት ወር ላይ በነጭ ወረቀት ላይ የዜድ ምልክትን በደማቁ በመጻፍ በአደባባዮች ሲያሽከረክር እንደነበርም ተገልጿል።

የግለሰቡ ተደጋጋሚ ድርጊት ሩሲያ በዩክሬን እየፈጸመች ያለውን ጦርነት ለመደገፍ ያደረገው ጥረት ነው ያለው የሀምቡርግ አቃቢ ህግ ለማስተማሪያነት በሚል ግለሰቡ 4 ሺህ ዮሮ እንዲከፍል ቅጣት እንደተጣለበት የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።

ሩሲያ በዩክሬን እያደረገች ላለው ጦርነት የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት ወይም ድጋፍ ለማግኘት በሚል የጦር ተሸከርካሪዎቿ የዜድ ምስልን ተጠቅመው እንዲንቀሳቀሱ አድርጋለች።

በሞስኮ እና በተወሰኑ ሀገራት የዜድ ምስል የተጻፈባቸው ምልክቶች በአደባባዮች ላይ መታየት ጀምረውም የነበረ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይም ለተወሰኑ ቀናት በስፋት ተሰራጭተዋል።

ጀርመን የትኛውም ዜጋዋ የሩሲያ ጦር ምልክት የሆነው ይህ የዜድ ምስልን በአደባባይ ይዞ መገኘት አልያም ማሰራጨት ዓለም አቀፍ ወረራን መደገፍ ስለሚሆን ድርጊቱን ከልክላለች።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ስምነተኛ ወሩ ላይ የሚገኝ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ሲሰደዱ በቢሊዮን የሚቆጠር መሰረተ ልማት ደግሞ መውደሙን የተመድ ሪፖርት ያስረዳል።

News today, Politics

ፑቲን ለ3ኛ ጊዜ መሪ ሆነው ለተመረጡት ፕሬዝዳንት ዢ የእንኳን ደስ አልዎት መልእክት አስተላለፉ

ፑቲን፤ በቀጣይ የዢ የስልጣን ዘመን ሞስኮ-ቤጂንግ ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋ አለኝ ብለዋል

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ፑቲን እና የቻይናው አቻቸው ዢ መልካም የሚባል ግንኙነት ያላቸው መሪዎች ናቸው

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላደሚር ፑቲን ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን መሪ ሆነው ለተመረጡት የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ የእንኳን ደስ አልዎት መልእክት አስተላለፉ፡፡

ፑቲን በቀጣይ የዢ ጂንፒንግ የስልጣን ዘመን ሞስኮ-ቤጂንግ ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸው ተስፋም ገልጸዋል፡፡

 “በሀገራቱ መካከል ያለውን… ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ ገንቢ ውይይታችንን እና የቅርብ የጋራ ስራችንን ለመቀጠል ደስተኛ ነኝ” ማለታቸውንም ነው በክሬምሊን በኩል የወጣው መግለጫ የሚያመለክተው፡፡

የሩሲያው ፕሬዝዳንት አክለው፤ ለ ዢ “ብልጽግና እና አዲስ ስኬቶች” እንደሚመኙ ተናግረዋል::

ሞስኮ እና ቤጂንግ በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ባለቸው ግንኙነት የቅርብ አጋሮች ሆነው ብቅ ያሉበት አጋጣሚ ተፈጥረዋል።

በሀገራቱ መሪዎች መካከል ያለው ግንኙነትም እንዲሁ መልካም የሚባል እንደሆነ ይነገራል፡፡

መሪዎቹ በቅርቡ በኡዝቤኪስታን መዲና ሳማርካንድ ተገናኝተው በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጎልበት እንደሚሰሩ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

ቭላድሚር ፑቲን እና ዢ ጂንፒንግ “ዓለምን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረገው ሙከራ” አንቀበልም የሚል የጋራ አቋም ያላቸው መሪዎች መሆናቸው ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል ቻይና ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የመነጠል አደጋ ለተጋረጠባት ሩሲያ ያላትን ድጋፍ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ስታንጸባርቅ ይስተዋልል፡፡

 ቻይና በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ አብዛኛው ጊዜ የመሃል አቋም ስታራምድና በሞስኮ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ስትቃወም ነው የምትታየው፡፡

ይህም አሜሪካን ጨምሮ በምዕራባውያን ዘንዳ ባይወደድም፤ ፑቲን የቻይናው መሪ ዢ በዩክሬን ጉዳይ የሚያንጸባርቁት “ሚዛናዊ አቋም” እንደሚያደንቁ በቅርቡ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም ሀገራቱ ለዓለም ተምሳሌት የሆነ ገደብ የለሽ ትብብር ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም፡፡

እናም የአሁኑ የፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ለሶስተኛ የስልጣን ዘመን መሪ ሆኖ መመረጥ በሞስኮ-ቤጂንግ መካካል ያለውን ጥሩ የሚባል ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሷል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

News today, Politics

ታይዋን፤ ቻይና “አሮጌ አስተሳሰብን ማስወገድ አለባ” አለች

ታይዋን ልዩነቶችን በሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና በተጨባጭ መንገድ እንዲፈቱ ጠይቃለች

ቻይና “የታይዋን ነጻነትን” ለመቃወም የሚያሽችል ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አድርጋለች

ታይዋን፤ ቻይና “አሮጌ አስተሳሰብን ማስወገድ አለባ” አለች፡፡

ታይፔ ይህን ያለችው ጉበኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የታይዋን ነጻነትን በተመለከተ ያለውን ተቃውሞ በህገ መንግስቱ ላይ ካረጋገጠ በኋላ ነው፡፡

የታይዋን የድንበር ተሸጋሪ ፖሊሲዎች አስፈጻሚ አካል የሆነው የመይንላንድ ጉዳዮች ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ “የቻይና ኮሚኒስት መንግስት አዲሱ አመራር የወረራ እና የመጋጨት አስተሳሰቡን አስወግዶ ልዩነቶችን በሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና በተጨባጭ መንገድ እንዲፈቱ እንጠይቃለን” ብሏል፡፡

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ በህገ-መንግስቱ ላይ “የታይዋን ነጻነትን” ለመቃወም የሚያሽችለው ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አድርጓል፡፡

ማሻሻያው ቅዳሜ ዕለት በፓርቲው ብሔራዊ ኮንግረስ ላይ ከ 2ሺህ በላይ ተወካዮች ያሳለፉት ውሳኔ አካል ነው መባሉን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

ለአንድ ሳምንት የቆየው ይህ የኮሙኒስት ፓርቲ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግን ፓርቲውን በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በሊቀመንበርነት እንዲመሩ በመምረጥ በትናንትናው እለት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ከዚህ በተጨማሪም ቻይናን ከፈረንጆቹ 2012 ዓመት ጀምሮ በሬዝዳንትነት እየመሩ ላሉት ዢ ጂንፒንግን ተጨማሪ ስልጣንም እንደሰጠም ሽንዋ ዘግቧል።

ፕሬዝዳንቱ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ቻይናን ሲመሩ ከኮሙንስት ፓርቲ ጽንሰ ሀሳብ ባለፈ ለቻይናዊያን ይበጃል የሚሉትን ሀሳብ ወደ ተግባር መቀየር እንዲችሉ ፈቃድም ሰጥቷል።

ፓርቲው 25 አባላት ያሉት የፖሊት ቢሮ እና አዲስ ሰባት የማዕከላዊ አባላት የተመረጡ ሰዎችን ያሳወቁ ሲሆን በፖሊት ቢሮ አንድም ሴት አለማካተታቸው አነጋገሪ ሆነዋል፡፡

ቻይና ሴት የፖሊት ቢሮ አባል የሌለው ካቢኔ ስታዋቅር በ25 ዓመታት መጀመሪያው ነው ተብሎለታል፡፡

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግን በፓርቲው ጉባኤ መዝጊያ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር ለቻይና ድል እንደሚዋጉ እና እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በኮሮና ቫይረስ ፣ በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እየተፈተነ ያለውን ኢኮኖሚ ማስታግስ እንዲሁም የታይዋን ጉዳይ ለፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ ዋነኛ ትኩረት የሚሰጡባቸው ጉዳዮች ናቸው።

News today, Politics

ሩሲያ የዩክሬኑን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠየቁ

ሩሲያ የዩክሬኑን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠየቁ

ሩሲያ ከሁለት ሺህ በላይ መካናይዝድ ጦሯን ግድቡ ወደሚገኝበት አካባቢ አሰማርታለች

ሩሲያ የዩክሬኑን ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘውን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠይቀዋል፡፡

ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘው ግድብ ከተመታ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጨማሪ ዜጎች በውሀ ሊጥለቀለቁ እንደሚችሉ ተሰግቷል።

ስምንት ወራት የሞላው የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በየጊዜው አዳዲስ ክስተቶችን ማስተናገዱን ቀጥሏል።

ሩሲያ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ በዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን ጥቃት በማድረስ ላይ እንደሆነች ተገልጿል።

በዚህ የሩሲያ ጥቃትም ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን የሀይል መሰረተ ልማቶች መውደማቸውን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ተናግረዋል።

የሩሲያ ጥቃት መቀጠሉ ያሳሰባቸው የዩክሬን ፕሬዝዳንት ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘው ግዙፉ የዩክሬን ግድብ እንዳይመታባቸው ሞስኮን ተማጽነዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ለደቡብ ዩክሬን ግዛቶች ዋነኛ የሀይል ምንጭ የሆነው ይህ ግዙፍ ግድብ ከተመታ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመቋረጡ ባለፈ በርካታ ዜጎች ሊጥለቀለቁ እንደሚችሉ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።

ሩሲያ በዚህ የዩክሬን ግድብ አካባቢ ከሁለት ሺህ በላይ መካናይዝድ ጦሯን ማስጠጋቷ ግድቡን ልታወድም እንደምትችል ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ምዕራባውያን እና ተመድ ሩሲያ የዩክሬንን ግድብ እንዳትመታ ጫና እንዲያደርጉ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠይቀዋል።ሩሲያ ከአንድ ወር በፊት የዩክሬን ግዛት የሆኑ አራት ግዛቶችን በህዝበ ውሳኔ ወደ ሞስኮ መጠቅለሏ ይታወሳል።

የመንግስታቱ ድርጅት ባሳለፍነው ሳምንት የሩሲያን ህዝበ ውሳኔ የሚቃወም ውሳኔ በአብላጫ መወሰኑም አይዘነጋም።

News today, Politics

ቻይና ጥቃት ከፈጸመች አሜሪካ ታይዋንን እንደምትከላከል ባይደን ተናገሩ

ቻይና “ጥቃት ከፈጸመች” አሜሪካ ታይዋንን እንደምትከላከል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በድጋሚ አስጠነቀቁ።

ፕሬዝዳንቱ ከሲቢኤስ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ የአሜሪካ ኃይሎች ታይዋንን ይከላከላሉ ወይ ተብለው ሲጠየቁ “አዎ” ብለው መልሰዋል።

እሑድ በተሰራጨው ቃለ መጠይቅ የአሜሪካ ፖሊሲ እንዳልተለወጠ ዋይት ሐውስ በድጋሚ እንዲናገር አስገድዶታል።

የዋሽንግተን ፖሊሲ ሁሌም “ስትራቴጂካዊ አሻሚነት” ያለው ሲሆን ታይዋንን ለመከላከል ቃል ባይገባም አማራጩን ደግሞ ሙሉ ለሙሉ አያስቀርም።

ታይዋን በምሥራቅ ቻይና የባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኝ ራስ ገዝ ደሴት ስትሆን ቤይጂንግ የግዛቴ አካል ናት ስትል ትገልጻለች።

በጉዳዩ ላይ ዋሽንግተን ቁርጥ ያለ አቋም ሳትይዝ ለረዥም ጊዜ በዲፕሎማሲያዊ ዥዋዥዌ ተጉዛለች። በአንድ በኩል ከቤይጂንግ ጋር ላላት ግንኙነት መሠረት የሆነውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ ታከብራለች።

በዚህ ፖሊሲ ታይዋን የቻይና አካል ስትሆን አቋሙም መገዳደሪያ የለውም። ስለዚህ አሜሪካ ታይዋንን እንደ የተለየ አገር ዕውቅና የማትሰጥ ሲሆን ከደሴቱ ጋር ምንም አይነት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትም የላትም። ነገር ግን የጠበቀ ግንኙነት ፈጥራለች።

አሜሪካ ከግዛቲቱ ጋር ባላት ውል መሰረት ለታይዋን የጦር መሳሪያ ትሸጣለች። ውሉ ደሴቲቱ ራሷን የምትከላከልበትን መንገድ ማቅረብ ያስፈልጋል ይላል።

ባይደን ከሲቢኤስ ቴሌቪዥን 60 ደቂቃ ከተሰኘው ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ይህንን በድጋሚ አስረግጠዋል።

“የአንድ-ቻይና ፖሊሲ አለ። ታይዋንም ነጻነቷ ላይ ራሷ ትወስናለች። እኛ አንንቀሳቀስም፣ ነፃነታቸውን አናበረታታም። ይህ የራሳቸው ውሳኔ ነው” ብለዋል።

ባይደን ታይዋን ጥቃት ከደረሰባት ለመከላከል ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚኖር በግንቦት ወር ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተዋል። ዋይት ሐውስም በፍጥነት አሜሪካ ከረዥም ጊዜ ፖሊሲዋ አትወጣም በማለት በፍጥነት ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

አሁንም ዋይት ሐውስ ባይደንን የሚቃረን መግለጫ አውጥቷል። “ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በቶኪዮ ይህንኑ ተናግረዋል። የታይዋን ፖሊሲ እንዳልተለወጠም ግልፅ አድርገዋል። ይህ እውነት ነው” ብሏል።

ይህ ግን በአንድ ዓመት ውስጥ ፕሬዝደንቱ ከይፋዊ የአገሪቱ አቋም ርቀው ለወታደራዊ እርምጃ ቃል ሲገቡ ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ነው። በጥቅምት እና በግንቦት ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተዋል።

በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ለታይዋን 1.1 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያዎች እና ፀረ ሚሳኤሎች ለመሸጥ ተስማምታለች። ይህም የቻይናን ክፉኛ አስቆጥቷል።

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በነሐሴ ወር በደሴቲቱ ያደረጉት አወዛጋቢ ጉብኝት በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለውን ውጥረት አባብሶታል። ባይደን ጉብኝቱን ቀደም ብለው “ጥሩ ሃሳብ አይደለም” ብለው ነበር።

በምላሹ ቤይጂንግ በታይዋን ዙሪያ ለአምስት ቀናት የቆየ ወታደራዊ ከበባ በማድረግ ልምምድ አካሂዳለች።

ዩናይትድ ስቴትስ ወደ ደሴቲቱ ሚሳኤል መተኮሱን ብትናገርም ቤይጂንግ ግን ይህንን አላረጋገጠችም። ቻይና የተኮሰችው ሚሳኤሎች ምንም አይነት ስጋት እንዳልፈጠሩ ታይዋን ተናግራለች።

ቀደም ብሎ ተቀርጾ እሑድ በተላለፈው ቃለ መጠይቅ ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት የኬሚካል ወይም የታክቲካል የጦር መሳሪያ እንዳትጠቀም ባይደን አስጠንቅቀዋል።

News today, Politics

አሜሪካ እና ታሊባን የእስረኛ ልውውጥ አደረጉ

በልውውጡ ፤ ታሊባን ለ17 ዓመታት ያክል በአሜሪካ እጅ የቆየው የጦር አዛዥ ባሻር ኑርዛይን ተቀብሏል

የጦር አዛዡ ባሻር ኑርዛይን ታሊባን ወደ ትጥቅ ትግል ሲገባ ለቡድኑ “የጦር መሳሪያ ድጋፍ” ሲያደረግ የነበረ ነው ተብሏል

ታሊባን በአሜሪካ እጅ የነበረውን የጦር አዛዥ ለማስፈታት ከሁለት አመት በላይ ታስሮ የነበረውን አሜሪካዊ የባህር ኃይል አርበኛ ለዋሽንግተን አሳልፎ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

የአፍጋኒስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካን ሙታቂ በካቡል ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ዛሬ ማርክ ፍሬሪችስ ለአሜሪካ ተላልፎ ተሰጥቷል ፤ እኛም የጦር መሪው ሃጂ ባሻር ኑርዛይ በካቡል አየር ማረፊያ ተሰጥቶናል” ብለዋል።

ልውውጡ የተከናወነው “ከረጅም ድርድር በኋላ” መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በካቡል ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አንድ የሀገራችን ልጅ ወደ ሀገሩ ሲመለስ የነበረውን አስደናቂ ስነ ስርዓት በማየታችን ደስተኛ ነን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኑርዛይ በአውሮፕላን ማረፊያው ሲደርስ በአዲሱ የአፍጋኒስታን እስላማዊ ኢሚሬትስ (አይኢኤኤ) መንግስት የጀግና አቀባበል እንደተደረገለትም ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

በማህበራዊ የትስስር ገጾች በመዘዋወር ላይ ያሉ ፎቶዎች የሚያሳትም፤ኑርዛይን የአበባ ጉንጉን በያዙና ጭንብል በለበሱ የታሊባን ባለስልጣናት አቀባበል ሲደረግለት ነው፡፡

ለበርካታ አመታት በአሜሪካ እጅ የቆየው የጦር አዛዡ ባሻር ኑርዛይ ወደ ሀገሩ ከተመለሰ በኋላ በሰጠው መግለጫ የታሊባን አመራሮች እሱን ለመስፈታት የተጓዙት የድርድር ርቀት አድንቋል፡፡

“ታሊባን ጠንካራ ቁርጠኝነቱን ባያሳይ ኖሮ ዛሬ እዚህ ባልነበርኩ ነበር” ብሏል ኑርዛይ።

ባሻር ኑርዛይ – ከሄሮይን ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ለ17 ዓመታት በአሜሪካ ታስሮ የቆየ የጦር አዛዥ ሲሆን ማርክ ፍሬሪችስ ደግሞ እንደፈረንጆቹ በ2020 ታፍኖ ተወስዶ በታሊባን ቁጥጥር ስር የቆየ የአሜሪካ የባህር ኃይል አርበኛ ነው፡፡

የአሜሪካ የባህር ኃይል አርበኛው ማርክ ፍሬሪችስ በአፍጋኒስታን ውስጥ በግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ በሲቪል መሃንዲስነት ሲሰራ የነበረ እንደሆነም ነው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገለጸው፡፡

ኑርዛይ በታሊባን ውስጥ ምንም አይነት ኦፊሴላዊ ቦታ አልነበረውም ነገር ግን በ 1990 ዎቹ ውስጥ ጠንካራው እንቅስቃሴ ብቅ ባለበት ወቅት “ጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ ለታሊባን ጠንካራ ድጋፍ ያደረግ ነበር” ያሉት ደግሞ የአፍጋኒስታን መንግስት ቃል አቀባይ ዛቢሁላህ ሙጃሂድ ናቸው፡፡

ከአንድ አመት በፊት የአሜሪካና አጋሮቿ ጦር ከ20 ዓመታት ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በኋላ አፍጋኒስታንን ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ፤ ታሊባን አፍጋኒስታንን እያስተዳደረ እንደሚገኝ የሚታወቅ ነው፡፡ 

News today, Politics

ሞስኮ፤ የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን የጦር ወንጀል ፈጽመዋል የሚለውን ውንጀላ “ውሸት” ነው አለች

ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ፤ የሩሲያ ኃይሎች በኢዚዮም የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ሲሉ ከሰዋል

ኢዚዮም በተባለ ስፍራ 450 የሚጠጉ በጅምላ ተቀብረው የነበሩ አስክሬኖች እንደተገኙ መረጃዎች እየወጡ ነው

ሞስኮ፤ የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት የጦር ወንጀል ፈጽመዋል የሚለውን ውንጀላ “ውሸት” ነው አለች፡፡

የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ኃይሎች የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የዩክሬኗ ካርኪቭ ግዛት መልቀቃቸውን ተከትሎ ኢዚዮም በተባለ ስፍራ 450 የሚጠጉ በጅምላ ተቀብረው የነበሩ አስክሬኖች እንደተገኙ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡

በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጡት የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ክሱ መሰረተ ቢስ ነው ሲሉ ውድቅ አድርገዋል፡፡

ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ ክሱ “በቡቻ ውስጥ እንደነበረው ተመሳሳይ ነው፤ ‘ውሸት ነው’ እናም በዚህ ተረት ውስጥ ያለውን እውነት እንዲታወቅ እናደርጋለን” ሲሉም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

የሩሲያው ቃል አቀባይ ይህን ይበሉ እንጅ የኪቭ ባለስልጣናት በቦታው የጦር ወንጀል እንደተፈጸመ እንደሚያምኑ ይህንንም ሰንደው ለማስቀመጥ እየሞከሩ እንደሆነ በመደመጥ ላይ ናቸው፡፡

ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ በቦታው ላይ የሚገኙ መርማሪዎች በእጃቸው የታሰሩ አስክሬኖችን ጨምሮ በርካታ የማሰቃየት ድርጊት የተፈጸመባቸው ሰዎች ለመኖራቸው አመላካች የሆኑ ማስረጃ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

በጅምላ መቃብሩ ውስጥ አብዛኞቹ ንጹሀን ዜጎች ፣ ሴቶችና ህጻናትም ይገኙበታል ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያ ኃይሎች ፈጽመውታል የተባለው ድርጊት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኩልም ቢሆን በከፍተኛ ደረጃ የተወገዘ ሆኗል፡፡

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ፣ በኢዚዮም ደን መቃብሮች መገኘታቸው “እጅግ አስደንጋጭ ነው” ብለዋል።

 ድርጊቱ አስደንጋጭና የሩሲያ ኃይሎች ዩክሬን ውስጥ ከፈጸሟቸው ጭካኔ የተሞሉ ወንጀሎች ጋር የሚመሳሰል ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፤ አሜሪካ የጦር ወንጀል በመሰነድ ድጋፍ መስጠት እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በበኩላቸው “የተፈጸመውን እጅግ እናወግዛለን” ብለዋል።

በኢዚዮም ተገኘ በተባለው የጅምላ መቃብር “እጅጉን መደንገጡ” የገለጸው ደግሞ የአውሮፓ ህብረት ነው፡፡

ህብረቱ የተፈጸመውን ድርጊት አጥብቆ እንደሚያወግዝ የገለጹት የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፕ ቦሬል፤ ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህግጋቶችን የጣሰ መሆኑ ተናግረዋል፡፡

 “በሩሲያ ኃይሎች የሚፈጸመው ኢሰብዓዊ ድርጊት የዓለም አቀፍ የሰብአዊ ህግጋትን እና የጄኔቫን ስምምነቶችን የጣሰ ነው፤ በአስቸኳይ መቆም አለበት” ብለዋል ጆሴፕ ቦሬል፡፡

አክለውም ፤የአውሮፓ ህብረት በዩክሬን ውስጥ እየተፈጸመ ላለው ወንጀል ሩሲያን ተጠያቂ ለመድረግ የሚደረጉ ሁሉንም ጥረቶችን ይደግፋል ብለዋል፡፡ 

News today, social life

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7 ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

በጃፖን በሬክተርስኬል መጠኑ 6 ነጥብ 8 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከስቶ በ146 ሰዎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

የታይዋን አየር ንብረት ቢሮ እንደገለጸው ህዝብ ተራርቆ በሚኖሮበት በደቡብ ምስራቅ ታይዋን የተከሰተው መሬት መንቀጥቀጥ ባቡሮች እንዲገለበጡ፣ የስቶር መደርደሪያዎች እንዲደረመሱና መንገዶች እንዲዘጉ ምክንያት ሆኗል።

ቢሮው የመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ ታይተን ግዛት ሲሆን በአካባቢው የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ግን ጉዳት አላደረሰም ብሏል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ በትናንትናው እለት የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል።

የታይዋን የእሳት ዲፖርትመንት በአደጋው የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን እና 146 ሰዎች መጎዳታቸውን አስታውቋል።

የታይዋን የሬይል ዋይ አስተዳደር ደግሞ ስድስት ባቡሮች መስመራቸውን ስተው መግልበጣቸውን እና በሰው ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልጿል።

በአደጋው በተዘጋው መንገድ ምክንያት በተራራማ አካባቢዎች መንገድ የተዘጋባቸውን 600 ሰዎች ለማውጣት ጥረት ላይ ናቸው።

የአሜሪካው የፖስፊክ የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ማእከል ከመንቀጥቀጡ አደጋው በኋላ ማስጠንቀቂያ አውጥቶ የነበረ ቢሆንም ቆይቶ አንስቶታል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል።

በፈረንጆቹ 2016 በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 100 ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ባይደን “የአሜሪካ ጦር ታይዋንን ከቻይና ወረራ ይከላከላል” አሉ

ታይዋን በቻይና እንዳትወረር ከጦር መሳሪያ በተጨማሪ የአሜሪካ ሰራዊት አባላት እንደሚሳተፉም አስታውቀዋል

በታይዋን ጉዳይ ቻይና ከአሜሪካ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብርም ማቋረጧን ማስታወቋ ይታወሳል

የአሜሪካው ፕሬዝዳት ጆ ባይደን ጦራቸው ታይዋንን ከቻይና ወረራ እንደሚከላከል አስታወቁ።

ፕሬዝዳንት ባይደን ከሲ.ቢ.ሲ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ታይዋንን ተበመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ ቻይና ታይዋን ላይ ያልተጠበቀ ጥቃት ከከፈተች ጦራቸው ራስ ገዝ የሆነችውን ታይዋንንን ለመከላከል ወደ ስፍራው ሊያቀና ይችላል ብለዋል።

ጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የተጠየቁት ባይደን ባይደን፤ ከዩክሬን በተለየ በጦር መሳሪያ መደፍ ብቻ ሳይሆን የአሜሪካ ወታደሮች ታይዋንን ለመከላከል ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ አረጋግጧል።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በግንቦት ወር በጃፓን አድርገውት በነበረው ጉብኝት ላይ ቻይና በታይዋን ላይ ወረራ ከፈጸመች፤ አሜሪካ ወታደራዊ አጸፋ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን መናራቸውም የሚታወስ ነው።

የቻይና መከላከያ ሚኒሰቴር ከወራት በፊት በበታይዋን ጉዳይ እንደማይደራደር እና ውጊያ መግጠም ካለባትም ለመግጠም ዝግጁ መሆኑን ለአሜሪካ መግለጹ ይታወሳል።

የቻይናው መከላከያ ሚኒስትር ዌዪ ፈንጊሄ፤ ከአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ሎልዩድ አውስቲን ጋር ከኢስያ የደህንነት ጉባዔ ጎን ለጎን ተገናኝተው ባደረጉት ውይይት፤ ታይዋንን ከቻይና መገንጠል የቻይና ወታደር “ማንኛውንም አይነት ዋጋ በመክፈል ከመዋጋት ውጭ ምርጫ እንዳይኖረው ያደርጋል” ሲሉ ነበር የተናገሩት።

“ህዝባዊ ነፃ አውጪ ጦር” በመባል የሚጠራው የቻይና ጦር የሀገሩን ብሔራዊ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነትን ከማስጠበቅ በቀር ሌላ ምርጫ እንደማይኖረውም ሚኒስትሩ በወቅቱ አሜሪካን አሳስበዋል።

የአሜሪከ አፈ-ጉባኤ ናንሴ ፔሎሲ ባሳለፍነው ሐምሌ ወር ቻይና የግዛቷ አድርጋ የምትቆጥራትን ታይዋንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ቻይና አሜሪካ እና ታይዋን ጋር ያላት ግንኙነተ በከፍተኛ ደረጃ መሻከሩ የሚታወስ ነው።

ይህንን ተከትሎም ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሮችን ማቋረጧን ያሳወቀች ሲሆን ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን ማጓጓዝ፣ አደገኛ እጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን አቋርጣለች።

News today, Politics

በአፍሪካ የነበሩ የዩክሬን ወታደሮች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

የዩክሬን ሰላም አስከባሪ ኃይል ሀገራቸው ከሩሲያ ጋር ጦርነት መጀመሯን ተከትሎ ወደ ኪቭ ለመመለስ ተገደዋል ተብሏል

ወታደሮቹ በተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስር በዲሞክራቲክ ኮንጎ ነበሩ

በአፍሪካ የነበሩ የዩክሬን ወታደሮች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

የመንግስታቱ ድርጅት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ያለውን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር ከተለያዩ ፈቃደኛ ሀገራት የተውጣጣ ሰላም አስከባሪ ጦር ማሰማራቱ ይታወሳል።

በዚህ ተልዕኮ ስራ ጦር ካዋጡ ሀገራት መካከል አንዷ አሁን ላይ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ ያለችው ዩክሬን ትገኝበታለች።

ሀገራቸው ከሩሲያ ጋር የገጠመችውን ጦርነት ለመመከት በሚል በዲሞክራቲክ ኮንጎ የነበሩ 250 የዩክሬን ወታደሮችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

እነዚህ ወታደሮች ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በተመድ ዓመቻችነት ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወታደሮቹን ካጓጓዙ አየር መንገዶች መካከል አንዱ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

በተመድ ስር ያለው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ዜጎች ተቃውሞ እያስተናገደ ሲሆን፤ ሰላም አስከባሪ ጦሩ ዜጎችን ከአማጺያን ጥቃት አልታደገም በሚል አየተተቸ ይገኛል።

የሀገሬው ዜጎችም ሰላም አስከባሪ ጦሩ ሀገራቸውን ለቆ እንዲወጣ በሰላማዊ ሰልፍ በመጠየቅ ላይ ሲሆን ይህ ሰላም አስከባሪ ጦር ከሁለት ወራት በፊት 36 ተቃዋሚዎችን ተኩሶ ገድሏል ተብሏል።

ከዚሁ ተቃውሞ ጋር በተያያዘም በኬንሺያሳ ያለው የተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ቃል አቀባይ የዲሞክራቲክ ኮንጎን ሉዓላዊነት የሚጋፋ አስተያየት ሰጥቷል በሚል ሀገሪቱቱን ለቆ እንዲወጣ ተደርጓል።

ተመድ በዓለም ላይ ፈቃደኛ ከሆኑ ሀገራት ጦር በማዋጣት በ12 ሀገራት ላይ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ያለው ሲሆን ለ22 ዓመት የቆየው እና ብዙ ገንዘብ ወጪ የተደረገበት ስምሪቱ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ያለው ነው።

News today, Technology

ቻይና በ2025 ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ማጓጓዝ ልትጀምር ነው

ቻይና ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የጉዞ አይነቶችን አዘጋጅታለች
የቻይና የጠፈር ጉዞ
የአንድ ሰው የጠፈር የጉዞ ትኬት ዋጋም ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይሆናል ተብሏል

ቻይና በፈረንጆቹ 2025 የግል ተጓዦችን በክፍያ ወደ ጠፈር ለማጓጓዘ እየሰራች መሆኑ ተገለፀ።

አንድ የቻይና የሮኬት ተመራማሪ እንዳስታወቁት ከሆነ የአንድ ሰው የጉዞ ዋጋ 2 እና 3 ሚሊየን የቻይና ዩዋን (ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር) ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል።

ለጥቂት ደቂቃዎች ወደ ጠፈር ለመጓዝ የአንድ ወንበር የጨረታ ዋጋ ከ2 ነጥበ 4 ሚሊዮን ዶላር አለፈ
በፈረንጆቹ በ2018 የተመሰረተው የሎንግ ማርች ሮክት ዋና ዳይሬክተር እና መቀመጫውን ቤጂንግ ያደረገው ሲ.ኤ.ኤስ ስፔስ ኤጀንሲ መስራች የሆኑት የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ፤ ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የመጓጓዣ ዘዴዎች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

የመጀመሪያው ወደ ዓለም አቀፍ የጠፈር ማዕከል መግባት የሚያስችል ሲሆን፤ ይህም ለቱሪስቶች ጥብቅ የሆነ የአካላዊ እና የስነ ልቦናዊ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሰቀምጥ ነው ተብሏል።

ጃፓናዊው ቢሊየነር የ12 ቀናት የጠፈር ቆይታውን አጠናቆ ተመለሰ
ሁለተኛው የጉዞ አይነት ቱሪስቶች መንኮራኩር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ በሌላ በካርጎ መንኮራኩር ወደ ጠፈር እንዲሄዱ ማድረግ የሚያስችል ሲሆን፤ ይህኛው ጉዞ በአንድ መቀመጫ 450 ሺህ ዶላር እንደሚያስከፍል ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

ሶስተኛው የጉዞ አይነት ሰብ ኦርቢታል የሚባል ሲሆን፤ ይህኛው የጉዞ አይነት ለአብዛኞቹ ጎብኚዎች የተመቸ እንደመሆን የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ ገልፀዋል

News today, Technology

ባህር ስር የሚጓዘው “ፖሲዶን” ኒውክሌር ታጣቂው የሩሲያ ድሮን

ሰርጓጅ ድሮኑ ሱናሚዎችን በማስነሳት የጠላት ኢላማን የማጥፋት አቅም አለው

ከባህር ስር 1 ሺህ ሜትር ጥልቀት ላይ የሚጓዘው ድሮኑ፤ እስከ 10 ሺህ ኪ.ሜ ድረስ መሸፈን ይችላል

ሩሲያ በያዝነው የፈረንጆቹ 2022 ይፋ ካደረገቻቸው አውዳሚ የጦር መሳሪያዎች ውስጥ “ፖሲዶን” የባህር ሰርጓጅ ድሮን አንዱ ነው።

“ፖሲዶን” ሰርጓጅ ድሮን የምጽአት ቀን የሚል መጠሪያ በተሰጠው የሩሲያው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ላይ የሚገጠሙ ሲሆን፤ ከሰርጓጅ መርከቡ ላይ የሚወነጨፉ መሆኑም ታውቋል።

“ፖሲዶን” የሩሲያ ኒውክሌር ድሮን ምን የተለየ ያደርገዋል?

“ፖሲዶን” በባህር ስር የሚጓዝ ድሮን ሲሆን፤ የኒውክሌር አረር የሚሸከም ግዙፍ የሆነ የባህር ሰርጓጅ ድሮን ነው።

የውሃ ስር ድሮን ፕሮጀክቱ መሰራት እንደተጀመረ የሚያሳየው መረጃ በ2015 ላይ እንደወጣ የዘገበው ኢውሮ ኒውስ፤ የድሮኑ ዋነኛ ዓላማም የባህር ዳርቻ ላይ የሚገኙ የጠላትን ወታራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ስፍራዎችን ለማውደም ነው።

“ፖሲዶን” የኒውክሌር የባህር ሰርጓጅ ድሮን 20 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ከባህር ስር እስከ 1000 ሜትር ጠልቆ መጓዝ እንደሚችልም ተመላክቷል።

የባህር ስር ድሮኑ እስከ 10 ሺህ ኪሎ ሜትር ድረስ የማካለል እና የጠላትን ኢላማ የመምታት አቅም ያለመው መሆኑም ተመላክቷል።

አብዛኛው የባህር ስር ድሮኑ ዝርዝር መረጃዎች እስካሁን በሚስጥር የተያዙ ሲሆን፤ ካለው ፍጥነት የተነሳ መከላከልም ሆነ ለማስቆም አዳጋች እንደሆነ ግን ተነግሯል።

የባህር ስር ድሮኑ ሰው ሰራሽ ሱናሚ ማእበሎችን ማስነሳት ይችላል የተባለ ሲሆን፤ እስከ 500 ሜትር ርዝመት ያለው ሱናሚ በማስነሳትም የባህር ዳርቻ ከተሞችን እንዳልነበሩ አድርጎ ሙሉ በሙሉ ማውደም ይችላል ተብሏል።

የብሪታኒያው ዴይሊ ሜይል ጋዜጣ እንዳስነበበው እነዚህን ድሮኖች የተሸከመው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ በነጭ ባህር ላይ መታየቱን እና በወቅቱም ዲሚትሪ ዶንስኮይ የተባለ ሌላ የጦር መርከብ አብሮት እንደበረ ይታወሳል።

News today, Politics

አፍሪካ ምን ማድረግ እንዳለባት ማንም ሊያዛት እንደማይገባ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ተናገሩ

አሜሪካ ከሩሲያ ጋር የሚወዳጁ የአፍሪካ ሀገራትን እንዳትቀጣም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል

ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጋር በዋሸንግተን ተወያይተዋል

አፍሪካ ምን ማድረግ እንዳለባት ማንም ሊያዛት እንደማይገባ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ተናገሩ።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ሰባተኛ ወሩ ላይ የሚገኝ ሲሆን ጦርነቱን ተከትሎ ምዕራባዊያን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም ለመነጠል የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ያገኛሉ።

አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያን ሀገራት ዩክሬን በሩሲያ ላይ ድልን እንድትቀዳጅ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ከመስጡ ጎን ለጎን በሞስኮ ላይ ማዕቀብ በመጣል ላይ ናቸው።

ይህ በዚህ እንዳለም አፍሪካን ጨምሮ ከሩሲያ ጋር ወዳጅነትን በሚመሰርቱ ሀገራት ላይ ግንኙነታቸውን እንዲያቋርጡ የተለያዩ ጫናዎችን በማድረግ ላይ ናቸው።

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ወደ ዋሸንግተን ተጉዘው በነጩ ቤተ መንግስት ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ተወያይተዋል።

ሩሲያ የየትኛውም የዓለማችን ባለጸጋ ሀገር ጋር የተለየ ግንኙነት የላትም ያሉት ፕሬዝዳንት ራማፎዛ አሜሪካም በአፍሪካ የተለየ ተጽዕኖ ማድረግ እንደሌለባት አክለዋል።

የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ተጽዕኖ ልታደርግ እንደማይገባ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ አፍሪካ ምን ማድረግ እንደሚገባት ማንም መናገር አይችልም ሲሉም አክለዋል።

አሜሪካ አፍሪካ ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንድታቋርጥ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረገች ሲሆን በአንድ ወር ውስጥ በተመድ የዋሸንግተን ተወካይ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ እና የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወደ አፍሪካ በመምጣት ስድስት ሀገራትን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

የመሪዎቹ ወደ አፍሪካ መምጣት ዋና አላማው ከሩሲያ ጋር ጠያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ጫና መፍጠር ሲሆን አፍሪካ ከሩሲያ ከአፈር ማዳበሪያ እና ስንዴ ውጪ ሌሎች ምርቶችን መግዛት እንደማይችሉ ተናግረውም ነበር።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በምዕራብ አፍሪካ ባደረጉት ጉብኝት አፍሪካ በሩሲያ ላይ የተለሳለሰ አቋም አሳይተዋል በሚልም ትችት ሰንዝረዋል።

News today, social life

ግብጽ በስዊዝ ካናል ላይ የ15 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ማድረጓን አስታወቀች

ግብጽ ከስዊዝ ካናል በዓመት ሰባት ቢሊዮን ዶላር ገቢ እያገኘች ነው

የዋጋ ጭማሪው ከመጭው ጥር ወር ጀምሮ የተገበራል ተብሏል

ግብጽ በስዊዝ ካናል ላይ የ15 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ማድረጓን አስታወቀች።

ሰሜን አፍሪካዊቷ ግብጽ ከቀጣዩ ጥር ወር ጀምሮ በስዊዝ ካናል በሚያልፉ መርከቦች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጓን አስታውቃለች።

ሮይተርስ የስዊዝ ካናል ሊቀመንበርን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ ግብጽ በእቃ ጫኝ መርከቦች ላይ የ15 በመቶ በትራንዚት እና በጎብኚዎች መርከቦች ላይ ደግሞ የ10 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ተጨምሯል።

የግብጽ ዋነኛ የገቢ ምንጭ የሆነው የስዊዝ ካናል በፈረንጆቹ 1869 ዓመት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት የሆነ ሲሆን ይህ የመርከቦች መጓጓዣ መስመር በቀን 50 መርከቦችን በማጓጓዝ ላይ ይገኛል።

ስዊዝ ካናል አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 153 ዓመት የሞላው ሲሆን ግብጽ ከስዊዝ ካናል ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ገልጻለች።

ስዊዝ ካናል ከ153 ዓመት በፊት ሜድትራኒያን ባህርን እና ህንድ ውቂያኖስን በማገኛኘት በአውሮፓ እና እስያ መካከል የሚደረገውን የባህር ላይ ጉዞ በማሳጠር ዘመናዊ የባህር ትራንስፖርት ያቀላጥፋል፡፡

በወቅቱ የግብጽ መሪ የነበሩት ካዲቭ እስማኤል ፓሻ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ የመርከቦች መተላለፊያ መስመር ግንባታው 10 ዓመታትን ፈጅቷል።

በዓመት 300 ሚሊዮን ቶን እቃዎች የሚተላለፉበት ስዊዝ ካናል የአገልግሎት መጠኑን ለማስፋት ግብጽ በየጊዜው የተለያዩ ማሻሻያዎችን አድርጋለች።

የአሁኑ የግብጽ ፕሬዝዳንት አልሲሲ በፈረንጆቹ 2014 ላይ በስዊዝ ካናል ላይ የተደረገውን የ8 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፋያ ግንባታ መመረቃቸው አይዘነጋም።

ስዊዝ ካናል በተሰራለት የማስፋፊያ ግንባታ መሰረት አሁን ላይ ስፋቱ 61 ሜትር በ312 ሜትር ላይ የደረሰ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት ከቻይና የመጣ ኮንቴይነሮችን የጫነች እቃ ጫኝ መርከብ መተላለፊያ መስመሩን ለአንድ ወር ዘግታ የ100 መርከቦችን እንቅስቃሴ በመግታት የዓለምን ንግድ ማስተጓጎሏ ይታወሳል።

News today, social life

የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት ያልቻሉ ሊባኖሳዊያን ባንኮችን በጦር መሳሪያ እያስፈራሩ ነው

ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት ባንኮች ለደንበኞቻቸው ገንዘባቸውን መመለስ አልቻሉም

የሊባኖስ ባንኮች የፊታችን ሰኞ ጀምሮ በደህንነት ምክንያት ስራ ለማቆም ወስነዋል

የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት ያልቻሉ ሊባኖሳዊያን ባንኮችን በጦር መሳሪያ እያስፈራሩ ነው፡፡

የመካከለኛዋ ምስራቅ ሀገር ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት ዜጎች በባንክ የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት አልቻሉም፡፡

ሊባኖስ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያጋጠማት ሲሆን የሀገሪቱ መገበያያ ገንዘብም የመግዛት አቅሙ መሽመድመዱን ተከትሎ ዜጎች ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል፡፡

አብዛኛው የሀገሪቱ ዜጎች ፍጆታ ከውጭ ሀገራት የሚገቡ በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ኢኮኖሚውን ወደ ከፋ አለመረጋጋት አስገብቶታል፡፡

በዚህም ምክንያት ባንኮች ከደንበኞቻቸው የተቆጠበ ገንዘብን መስጠት አለመቻላቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ ዜጎች የጦር መሳሪያ በድብቅ እያስገቡ የባንክ ሰራተኞችን እያስፈራሩ እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በየጊዜው የጦር መሳሪያ እየያዙ ወደ ባንኮች የሚያመሩ ዜጎች ቁጥር መጨመሩን ተከትሎ ባንኮች ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንደገጠማቸው ተጠቅሷል፡፡

ለአብነትም በትናንትናው ዕለት አንዲት እንስት የካንሰር ህክምናዋን በቱርክ እየተከታተለች ለምትገኝ እህቷ ገንዘብ መላክ በመፈለግ ወደ ባንክ ብትሄድም ባንኩ ሊያስተናግዳት ባለመቻሉ የጦር መሳሪያ ለመጠቀም መገደዷን ተናግራለች፡፡

በዛሬው ዕለትም በአምስት የሊባኖስ የተለያዩ ቦታዎች የባንክ ደንበኞች የጦር መሳሪያ ተጠቅመው ገንዘባቸውን ከባንኮች ለመውሰድ መሞከራቸው ተገልጿል፡፡

የደንበኞቻቸው የጦር መሳሪያ እየያዙ መምጣት ያሳሰባቸው የሀገሪቱ ባኮችም ከቀጣዩ ሰኞ ጀምሮ ለሶስት ቀናት አገልግሎት ላለመስጠት መወሰናቸውን አሳውቀዋል፡፡ 

News today, Politics

ጆ ባይደን፤ ቭላድሚር ፑቲን ታክቲካል ኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳይጠቀሙ አስጠነቀቁ

ባይደን፤ ፑቲን ኒውክሌር ከተጠቀመ “ጦርነቱን ከ2ኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ባልታየ ሁኔታ ይቀይረዋል” ሲሉ ተናግረዋል

ጆ ባይደን፤ “ፑቲን ቀይ መስመሩን ማለፍ የለበትም” ሲሉ አስጠንቅቀዋል

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፤ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳይጠቀሙ አስጠነቀቁ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ከሲቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ባረደጉት ቆይታ የታክቲካል የኒውክሌር መሳሪያ መጠቀም አደገኛ ሁኔታ ሊያስከትል ይችላል ብለዋል፡፡

ታክቲካል ኒውክሌር በመባል የሚታወቁት የአጭር ርቀት መሳሪያዎች ሲሆኑ፣ ስትራቴጂክ ኒውክሌር ደግሞ የረዥም ርቀት ተስወንጫፊ መሳሪያዎችን ያካትታሉ።

ፑቲን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ከተጠቀሙ “ጦርነቱን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ባልታየ ሁኔታ ይቀይረዋል” ያሉት ባይደን፤ “ፑቲን ቀይ መስመሩን ማለፍ የለባቸውም!” ሲሉም አስጠንቅቀዋል፡:

ፑቲን የኒውክሌር መሳሪያ በዩክሬን ለመጠቀም አስበው ከሆነ ምን መልዕክት ማስተላለፍ ይፈልጋሉ ተብለው በሲቢኤስ የተጠየቁት ባይደን ጋዜጠኛውን “ተው! ተው! ተው!” ሲሉ ታይተዋል።

ፕሬዝዳንት ጆ-ባይደን አሜሪካ የኒውክሌር ጥቃትን ተከትሎ ምን እርምጃ እንደምትወስድ በግልጽ ባይናገሩም “ዓለም ላይ ታይተው ከሚታወቁ ቀውሶች ሁሉ የባሰ ይሆናል፤ የሚከሰተውን ጉዳት ያህልም ምላሽ እንሰጣለን” ብለዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ይህን ይበሉ እንጅ፤ የክሬምሊን ባለስልጣናት የሶሞኑ መግለጫዎች የሚያመለለክቱት በተቃራኒው ነው፡፡

በዩክሬን ላለው ቀውስ አሜሪካን ጨመሮ ለኪቭ የጦር መሳሪያ ድጋፍ የሚያደርጉትን ምዕራባውያን ተጠያቂ የሚያደርጉት የሩሲያው መሪ ፑቲን፤ በዩክሬን ምድር ያሰብነውን ዓላማ ከማሳከት የሚገታን ኃይል የለም እያሉ ነው፡፡

በዚህም ዩክሬንን ሽፋን ደረገው የሩሲያ እና አሜሪካ ፍጥጫ አደገኛ ሁኔታ እንዳያስከትል ተሰግተዋል፡፡አሜሪካ በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ለኪቭ የሚያስፈለግ የጦር መሳሪያ በከፍተኛ ደረጃ ድጋፍ ከሚልኩ ሀገራት አንዷ መሆኗ ይታወቃል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ፤አሜሪካ 3 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የጦር መሳሪያ ድጋፍ ለዩክሬን እንደምትሰጥ በቅረቡ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

ድጋፉ ዩክሬን ፤በአየር መከላከያ እንዲሁም የመድፍ ስርዓቶችና ጥይቶችን እንድታጎለብት ብሎም ከረዠም ርቀት ጥቃቶች እራሷን መከላከል እንደምትችል ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸው ነበር፡፡

News today, Politics

አሜሪካ እና ሶማሊያ ሽብርተኝነት ለመዋጋት የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ

በሶማሊያ ፖለቲከኛች መካከል የነበረው ሽኩቻ “አልሻባብ እንዲያንሰራራ” እድል የፈጠረ መሆኑ ይነገራል

የሶማሊው ፕሬዝዳንት ፤ “አሜሪካ በሶማሊያ ዘላቂ ልማት እና እድገት ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋር ነች” ብለዋል

አሜሪካ እና ሶማሊያ ሽብርተኝነት ለመዋጋት የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ፡፡

ለይፋዊ ስራ ጉብኝት በአሜሪካ የሚገኙት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ሽብርተኝነትን መዋጋት፣ የሶማሊያ ድረቅ እና መልካም አስተዳደር ፕሬዝዳንቱ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በነበራቸው ቆይታ የመከሩባቸው አንኳር ጉዳዮች ናቸው፡፡

በውይይታቸው በተለይም ከሶማሊያ አልፎ የቀጠናው ስጋት የሆነውን ሽብርተኝነት ለመዋጋት ሀገራቱ የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በትዊተር ገጻቸው ያጋሩት መረጃ ያመለክታል፡፡

“አሜሪካ በሶማሊያ ዘላቂ ልማት እና እድገት ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋር ነች”ም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ፡፡

አሁን አሁን ከነበረበት ሁኔታ እያንሰራራ እየመጣ እንደሆነ የሚነገርለት አልሻባብን አደጋ ለመግታት በሚል፤ አሜሪካ በታጣቂ ቡድኑ ላይ የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኗ የሚታወቅ ነው፡፡

በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠናው ስጋት የሆነውን አልሻባብ ለመምታት 600 የሚሆኑ የሃገራቸውን ወታደሮች ወደ ሶማሊያ እንደሚልኩ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው።

የአሜሪካ ጦር በድጋሚ በሶማሊያ እንዲሰማራ የማድረግ ውሳኔ በየሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ተቀባይነት ማግኘቱም አይዘነጋም፡፡

ሶማሊያ አሁንም በአልሻባብ እየተፈተነች ነው። በተለይም ከምርጫ ጋር በተያያዘ በሃገሪቱ ፖሊተከኞች መካከል የነበረው ሽኩቻ ለሰላምና ጸጥታ ይሰጥ የነበረውን ትኩረት አላልቶት እንደነበር በርካቶች ያነሳሉ።

አሁኑ ላይ አሜሪካ በአልሻባብ ላይ የምትወስዳቸው እርምጃዎች አሜሪካ ቡድኑን ከማዳከም አንጻር ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል፡፡

የአሜሪካን ሚና እንደ ትልቅ የአጋርነት መገለጫ አድረጎ የሚወስደው የፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ አስተዳደር በቅረቡ “ለመረጋጋትና ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በምናደርገው ትግል አሜሪካ ወትሮም ቢሆን ታማኝ አጋራችን ናት” ሲል በትዊተር ገጹ ላይ ባወጣው ጽሁፍ ማጋራቱም የሚታወስ ነው፡፡

News today, Politics

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ከቻይና የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልእክተኛ ጋር በአስመራ ተነጋገሩ

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ፤ ጉብኝቱ በኤርትራ እና ቻይና መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የሚያጎለብት መሆኑ ተናግረዋል

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና ጉብኝት እንዲያደርጉ መጋበዛቸው ይታወሳል

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከቻይና የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሹ ቢንግን ጋር በአስመራ ተናገገሩ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ከልዩ መልዕክተኛው ጋር በነበራቸው ቆይታ በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዘለግ ያለ ውይይት ማድረጋቸው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል አስታውቀዋል፡፡

ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ “ሁለቱ ወገኖች በኤርትራ ቅድሚያ በሚሰጣቸው የልማት መስኮች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ተወያይተዋል” ብለዋል፡፡

ኤርትራ እና ቻይና በቀጣናዊ ትስስራቸው ማዕቀፍ ውስጥ የልማት ትብብር ለማካሄድ መስማማተቸውም ጭምር ተናግረዋል ፡፡

ጉብኝቱ በኤርትራ እና ቻይና መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የበለጠ ለማጎልበት የሚያችል እንደሆነ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በውይይቱ መናገራቸውም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ኤርትራ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች በትብብር የሚሰሩ ሀገራት መሆናቸው ይታወቃል፡፡

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ በየካቲት በኤርትራ ባደረጉት ይፋወዊ የስራ ጉብኝት፤ በማዕድን ልማት፣ በምጽዋና አሰብ ወደቦች ልማት፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በመሰረተ ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራትም ከስምምነት መድረሳቸው የሚታወስ ነው፡፡

በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት ቻይና ለኤርትራ ተጨማሪ የ100 ሚሊየን ዩዋን ድጋፍ ማድረጓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋንግ ዪ በወቅቱ መግለጻቸው አይዘነጋም።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በበኩላቸው የቻይናን የ100 ዓመታት የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ጉዞ እና በዓለም ዐቀፍ ሕጎች ማዕቀፍ ውስጥ ሆና ዓለምን ሚዛናዊ ለማድረግ የምታደርውን ጥረት አድንቀዋል።

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ፐሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና ጉብኝት እንዲያደርጉ ግብዣ እንደላኩላቸውም የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው አስፍረው ነበር፡፡

ኤርትራ፤ ቻይና በዓለም አቀፍ መድረክ የምታራምዳቸው አቋሞች በመደገፍ የምትታወቅ ሀገር መሆኗም ይታወቃል፡፡

News today, Politics

በአርመን እና አዘርቤጃን መካከል በተካሄደው ጦርነት ከ200 በላይ ወታደሮች ተገደሉ

አለምአቀፉ ማህበረሰብ ባለፈው ሀሙስ የተደረሰውን ተኩስ አቁም በአዎንታ ተቀብሎታል

አርመኒያ እና አዘርቤጃን ናጋርኖ ካራባክ በተባለው ተራራማ ግዛት ምክነያት ከፈረንጆቹ 1988 ጀምሮ ፍጥጫ ውስጥ ነበሩ

በቅርቡ በድጋሚ በተቀሰቀሰው የአርመን እና የአዘርቤጃን ጦርነት ከ200 በላይ ወታደሮች ተገደሉ፡፡

ሮይርስ እንደዘገበው የአርመንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሲኒያን በአርመን እና አዘርቤጃን መካከል በተቀሰቀሰው ጦርነት 135 ወታደሮች መገደላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

አሁን 135 ወታደሮች ህይወታቸው አልፏል፤ ብዙዎች ቆስለዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺኒያን “እንዳለመተል ሆኖ ይህ የመጨረሻ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሀለቱ ሀገራት በፈረንጆቹ 2020 ካደሩጉት ደምአፋሳሽ የስድስት ሳምንት ጦርነት ወዲህ በተቀሰቀሰው ጦርነት 71 ወታደሮች እንደተገደሉባት አዘርቤጃን ሪፖርት አድርጋለች፡፡

እስካሁን በሁለቱም ሀገራት የተገደሉ ወታደሮች ቁጥር ከ200 በላይ ሆኗል፡፡

አርመኒያ እና አዘርቤጃን ናጋርኖ ካራባክ በተባለው ተራራማ ግዛት ምክነያት ከፈረንጆቹ 1988 ጀምሮ ፍጥጫ ውስጥ ነበሩ፡፡ በፈረንጆቹ 1994 በተካሄድ የሰላም ድርድር ተኩስ አቁም የተፈራረሙ ቢሆንም ከዚያ ወዲህ አልፎ አልፎ ግጭት ውስጥ ሲገቡ ቆይተዋል፡፡

በቅርቡ የተጀመረውን ግጭት በሚመለከት ግን ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን በመጀመር እየተካሰሱ ይገኛሉ፡፡ አርመን፣ የአዘርቤጃን ሃይሎች ናጎርኖ ካራባክን አልፈውጥቃት በመክፈት አርመን ውስጥ ቦታ ይዘዋል የሚል ክስ ስታቀርብ፣አዘርቤጃን ደግሞ ለተፈጸመባት ትንኮሳ ምላሽ መስጠቷን ትገልጻለች፡፡

አለምአቀፉ ማህበረሰብ ባለፈው ሀሙስ የተደረሰውን ተኩስ አቁም በአዎንታ ተቀብሎታል፡፡

News today, Politics

ቱርክ፤ በሩሲያ እና ቻይና የሚመራው የጸጥታ ጥምረት አባል የመሆን አላማ እንዳላት ፕሬዝደንት ኤርዶጋን ተናገሩ

ኤስሲኦ በሩሲያ እና ቻይና የተመሰረተ የጸጥታ ጥምረት ነው

ፕሬዝደንቱ ይህን ያሉት በኡዝቤክስታን በተካሄደው የኤስሲኦ ስብሰባ ላይ ከተካፈሉ በኋላ ነው

የቱርኩ ፕሬዝደንት ኤርዶጋን የኔቶ አባል የሆነችውን ሀገራቸው የሻንጋይ ኮኦፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን(ኤስሲኦ) አባልጰየማድረግ አላማ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ኤስሲኦ በሩሲያ እና ቻይና የተመሰረተ የጸጥታ ጥምረት ነው።

ፕሬዝደንቱ ይህን ያሉት በኡዝቤክስታን በተካሄደው የኤስሲኦ ስብሰባ ላይ ከተካፈሉ በኋላ መሆኑን ሮይተር ዘግቧል።

“በዚህ እርምጃ ከእነዚህ ሀገራት ጋር ያለን ግንኙነት ወደ ልዩ ቦታ ይደርሳል” ብሐዋል ፕሬዝደንት ኤርዶጋን።

ቱርክ በአሁኑ ወቅት ቻይና ሩሲያ ህንድ ፓኪስታን ኢራን ኪሪጊስታን ፓጃኪስታን ካዛኩስታን እና ኡዝቤኪስታን ያሉበት የጸጥታ ጥምረት የውይይት አጋር ነች።

በስብሰባው ላይ ከፕሬዝደንት ፒቲን ጋር የተነጋገሩት ኤርዶጋን በደቢብ ቱርክ በሚገኘው የኑክሌር ጣቢያ ጉዳይ የነበረውን ግጭት ለመፍታት ከስምምነት መድረሳቸውን ገልጸዋል።

በፈረንቹ 2001 የተቋቋመው በሩሲያ እና ቻይና የነበረ ሲሆን ከተመሰረተ ከአራት አመት በኋላ ህንድ እና ፓኪስታንን አካቷል፤ ይህም በቀጣናው ያለውን የምእራባውያን ጫና ለመቋቋም አላማ ያደረገ ነበር፡፡

Politics, social life

አሜሪካ ኡሁሩ ኬንያታ “የኢትዮጵያና የዲ.አር.ሲ የሰላም መልዕክተኛ” ሆነው መሾማቸውን እንደምትቀበል ገለጸች

ኡሁሩ ኬንያታ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ፖለቲካዊ መፍትሔ እንዲያገኝ ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል

አሜሪካ ተለዋዋጭ ሁነታዎች በሚስተዋሉበት ቀጠና “ኬንያታ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ ተስፋ አለን” ብላለች

አሜሪካ ኡሁሩ ኬንያታ የኬንያ የአፍሪካ ቀንድ የሰላም መልዕክተኛ ሆነው መሾም በደስታ እንደምትቀበል ገለጸች፡፡

የአሜሪካ መንግስት በውጭ ጉዳይ መሰሪያ ቤቱ የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባወጣው መግለጫ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የአፍሪካ ቀንድ እና የታላላቅ ሀይቆች አካባቢ የሰላም መልዕክተኛ ሆነው መሾማቸውን በደስታ እንደሚቀበል አስታውቋል።

ቢሮው ተለዋዋጭ ሁነታዎች በሚስተዋሉበት ቀጠና ኬንያታ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ ተስፋ አለን ብሏል፡፡

“ኡሁሩ ኬንያታ በሰሜን ኢትዮጵያ እና በምስራቅ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ለተፈጠረው ግጭት የሰላም መልዕክተኛ ሆነው መሾማቸውን በደስታ እንቀበላለን፤ ኬንያታ በዚህ ጊዜ ሁለቱም ግጭቶች ለመፍታት የሚጫወቱት ሚና ወሳኝ ይሆናል” ብሏል ቢሮው በትዊተር ገጹ ላይ ባጋራው ጽሁፍ፡፡

አዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ከቀናት በፊት በነበረው በዓለ ሲመታቸው በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚያከናውኑትን ተግባር እንደሚቀጥሉ መናጋራቸው ይታወሳል።

ሁለት ዓመት ሊሞላው የተቃረበውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ተዋጊ ኃይሎችን ከማደራደር ጋር ተያይዞ ከአፍሪካ ህብረት በተጨማሪ የኡሁሩ ኬንያታ ስም በተደጋጋሚ ሲነሳ ቆይቷል።

በተለይም አሁን ላይ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ለመሰደራደር ዝግጁ መሆናቸው የሚገልጹት የትግራይ ኃይሎች፤ ከመንግስት ጋር በሚደረገው ድርድር ከአፍሪካ ህብረት ይልቅ በቅርቡ ስልጣናቸውን ያስረከቡት ኡሁሩ ኬንያታ እንዲያሸማግሏቸው በተደጋጋሚ በይፋ ጠይቀው እንደነበርም የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ለሚካሄደው ጦርነት መፍትሔ በመፈለጉ በኩል የአፍሪካ ህብረት ቀዳሚው አሸማጋይ ሊሆን እንደሚገባ ቀደም ሲል በያዘው አቋም እንደጸና መሆኑ ይታወሳል።

News today, Politics

አረብ ኤምሬትስን ጨምሮ 5 ተጨማሪ የዓለማችን ሀገራት የሻንጋይ ትብብር ድርጅትን ተቀላቀሉ

ግብጽ፣ አረብ ኢምሬትስ፣ ኳታር ፣ ባህሬን እና ኩዌት ድርጅቱን በአጋርነት ተቀላቅለዋል

የምስራቅ ሀገራት ስብስብ የሆነው የሻንጋያ ትብብር ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ በኡዝበኪስታን ተካሂዷል

በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት የሚመራውን የዓለም ተጽዕኖ ለመመከት የተቋቋመው የሻንጋይ ትብብር ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤውን በኡዝበኪስታን አካሂዷል።

በሳመርካንድ ከተማ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የቻይና፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ኢራን፣ ቱርክ እና ሌሎችም ሀገራት ፕሬዝዳንቶች እና ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተሳትፈውበታል።

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድርጅቱን በአጋርነት ተቀላቀሉት የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ ግብጽ፣ ኳታር ፣ ባህሬን እና ኩዌት እንኳን ደህና መጡ ብለዋል።

ቤላሩስን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ሀገራት ወደዚህ ድርጅት ለመቀላቀል ፍላጎት እያሳዩ ሲሆን ኢራን በይፋ ድርጅቱን መቀላቀሏም ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ፑቲን በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር የሻንጋይ ትብብር ድርጅት የዓለምን ችግር ለመፍታት የተቋቋመ እንጂ ቡድን የመመስረቻ መድረክ አይደለም ብለዋል።

ለዓብነትም ድርጅቱ የዓለም ምግብ ችግሮችን፣ ሽብርተኝነትን እና የህይል እጥረቶችን ለመፍታት ይሰራል ሲሉም ፕሬዝዳንት ፑቲን አክለዋል።

በአፍሪካ፣እስያ እና ደቡብ አሜሪካ ሀገራት መካከል በራሳቸው በብሄራዊ የመገበያያ ገንዘባቸው ሰፊ የንግድ ልውውጥ መፍጠር የድርጅቱ ዋነኛ አላማ እንደሆነም ተገልጿል።

ሞስኮ በዩክሬን በጀመረችው ጦርነት ምክንያት ማዕቀቦች እንደተጣሉባት የገለቱት ፕሬዝዳንት ፑቲን ከ300 ሺህ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ያለምንም ክፍያ ለታዳጊ ሀገራት እንደምታሰራጭም ተናግረዋል።

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ በበኩላቸው ቤጂንግ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩዋን እርዳታ ለታዳጊ ሀገራት የሰብዓዊ ድጋፎችን እንደምታደርግ በጉባኤው ላይ ገልቷል።

ሻንጋይ የትብብር ድርጅት በፈረንጆቹ 2001 ላይ በቻይናዋ ሻንጋይ የተቋቋመ ሲሆን ኡዝቤኪስታን፣ ቻይና፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ፓኪስታን፣ ታጂኪስታን፣ ኪርጊስታን፣ እና ካዛኪስታን ደግሞ መስራች ሀገራት ናቸው።

አፍጋኒስታን፣ ኢራን፣ ቤላሩስ እና ሞንጎሊያ በታዛቢነት ድርጅቱን የተቀላቀሉ ሲሆን አርመኒያ፣ አዛርባጂያ፣ ቱርክ፣ ስሪላንካ፣ ቻምቦዲያ እና ኔፓል ደግሞ ድርጅቱን ለመቀላቀል በሂደት ላይ እንደሆኑ ተገልጿል።

ከዓለማችን ህዝብ ቁጥር ውስጥ ግማሽ ገደማ የሖነው በዚህ ድርጅት ውስጥ በመደራጀት ላይ ሲሆኑ የድርጅቱ ሊቀመንበርነትን አባል ሀገራቱ በዙር እየመሩት ይገኛሉ።

የኡዝቤኪስታን ፕሬዝዳንት ሻቭካት ሚርዚቭ የወቅቱ የሻንጋይ የትብብር ድርጅትን በሊቀመንበርነት በመምራት ላይ ይገኛሉ።

News today, Politics, social life

ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ፤ “ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን ማቅረብ በሞራል ደረጃ ተቀባይነት ያለው ነው” አሉ

አባ ፍራንሲስ፤ እራስን መከላከል ህጋዊ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ “ለሀገሩ ያለውን ፍቅር መግለጫ ነው” መሆኑም ተናግረዋል

ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ፤ የዩክሬን ጦርነት ራስን ለመከላከል የሚደረግ “ፍትሃዊ ጦርነት” ነው ብለዋል

የዓለም ካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ፤ ራሷን በመከላከል ላይ ላለችው ዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን ማቅረብ “በሞራል ደረጃ ተቀባይነት ያለው ነው” አሉ።

ሊቀ ጳጳሱ ይህን ያሉት ከሶስት ቀን የካዛኪስታን ቆይታ ሲመለሱ በአውሮፕላን ውስጥ ሆነው በነበረቻው 45 ደቂቃ የፈጀ ቃለ ምልልስ ላይ ከአንድ ጋዜጠኞች “ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ መላካችው ትክክል ነው?” ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ነው።

አባ ፍራንሲስም “ይህ ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው ፤ ነገር ግን መርሆችን ባከበረ መልኩ የሚደረግ ከሆነ ከሞራል አኳያ ተቀባይነት ያለው ውሳኔ ነው” ብለዋል።

የዩክሬን ጦርነት ራስን ለመከላከል የሚደረግና በመርህ ደረጃም “ፍትሃዊ” የሚባል ጦርነት መሆኑ ለዚህም የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሃሳባቸው እንድትጋራ የሚያስችል ማብራሪያም መስጠታቸውም ሮይተርስ ዘግቧል።

“እራስን መከላከል ህጋዊ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር መግለጫ ነው” ሲሉም አክለዋል። ሊቀ ጳጳሱ የሩሲያ – ዩክሬን ጦርንት እንዲያበቃ ምኞታቸው መሆኑንም ገልጸዋል።

ጦርነቱ እንዲቆም “ዩክሬን ለውይይት ክፍት እንድትሆን” የጠየቁት ሊቀ ጳጳሱ፤ በቅርቡ ከዩክሬን ጋር ምንም ዓይነት የድርድር ተስፋ እንደማይኖር ስለገለጸችው ሩሲያ ግን ያሉት ነገር የለም።

ያም ሆኖ ሊቀ ጳጳስ ፍራሲስ፤ ከሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሞስኮ ተገናኝቶ ለመምከር ፍላጎት እንዳላቸው ባሰለፍነው ግንቦት ወር አስታውቀው እንደነበር አይዘነጋም።

ሊቀ ጳጳሱ፤ ከጣሊያኑ ኮሬ ዴላ ሴራ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ ወደ ሞስኮው መምጣት እፈልጋለሁ ሲሉ ለፑቲን መልዕክት መላካቸውንም ተናግረው ነበር።

መልዕክቱ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት በተጀመረ በ20ኛው ቀን የተላከ መሆኑንም ነበር ሊቃ ጳጳስ ፍራንሲስ የተናገሩት።

የዓለም ካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ጥያቄ ብያቀርቡም፤ በክሬምሊን ባለስልጣነት በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።

News today, social life

ደቡብ ሱዳን ነዳጅ ወደ ውጭ ለመላክ ጅቡቲ ወደብ ላይ ቦታ መግዛቷ አስታወቀች

የደቡብ ሱዳን መንግስት የነዳጅ ሚኒስትር ከፖርት ሱዳንና ሞምባሳ በተጨማሪ ጅቡቲን እንጠቀማለን ብለዋል

ደቡብ ሱዳን አሁን ላይ ነዳጅ የምትልከው “ፖርት ሱዳንን በመጠቀም ብቻ” መሆኑ ይታወቃል

ደቡብ ሱዳን ድፍድፍ ዘይትን ወደ ውጭ ለመላክ የጅቡቲ ወደብ እንደ አማራጭ መጠቀም እንደምርፈልግ አስታወቀች፡፡

የደቡብ ሱዳን መንግስት የነዳጅ ሚኒስትር ፉት ካንግ ኩል በነዳጅ ጉዳይ እየመከረ ባለውና የጅቡቲው የኢነርጂ እና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር ዩኑስ አሊ ጌዲ በተገኙበት የጁባው ኮንፈረንስ እንደተናገሩት ደቡብ ሱዳን ነዳጅን ወደ ውጭ ለመላክ እና እቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በጅቡቲ ወደብ ላይ 12 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ገዝታለች ብሏል፡፡

 “እኛ ፖርት ሱዳን እና ሞምባሳን ብቻ ስንጠቀም ቆይተናል ነገር ግን በቅርቡ ወደ ጅቡቲ ለመሄድ ወስነናል” ሲሉም አክለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጀምስ ሞርጋ ለአል ዐይን አማርኛ እንደናገሩት “በሞምባሳ በኩል ነዳጅ መላክ አንችልም፤ ስለዚህም ጅቡቲን መጠቀም ግድ ይለናል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን ነዳጅ ለመላክ መሰረተ ልማት ወሳኝ በመሆኑ በቅድሚያ “ከደቡብ ሱዳን-አትዮጵያ እስከ ጅቡቲ የሚያገናኘው መስመር መዘርጋት አለበት”ም ብለዋል አምባሳደሩ፡፡

ደቡብ ሱዳን፤ በሱዳን የተፈጠረውን የፖለቲካ አለመረጋጋት ተከትሎ ፖርት ሱዳንን በመጠቀም ነዳጅ ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ለማቆም ተገዳ የነበረ ቢሆንም፤ አንጻራዊ ሁኔታ መፈጠሩን ተከትሎ አሁን ፖርት ሱዳን ብቸኛ ነዳጅ የምትልክበት ወደብ አድርጋ በመጠቀም ላይ ትገኛለች፡፡

ደቡብ ሱዳን ኢኮኖሚዋ በነዳጅ ንግድ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ይታወቃል፡፡ 

News today, Politics

ጀርመን በአውሮፓ ግዙፍ ሆነ የታጠቀ ጦር ለመገንባት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

የጀርመኑ መሪ ኦላፍ ሾልዝ የአውሮፓ ሀገራት በኔቶ ጥላ ስር ሆነው ኃላፊነታቸው እንዲወጡ አሳስበዋል

የሩስያ-ዩክሬን ጦርነት ጀርመን የመከላከያ ፖሊሲዋን እንድትለውጥ አስገድዷል

የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው የአውሮፓን ጸጥታ ለመምራት የሚያችላት ግዙፍ ሆነ የታጠቀ ጦር ለመገንባት ዝግጁ ነች አሉ፡፡

ኦላፍ ሾልዝ፤ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ፊት ባደረጉት ንግግር “ጀርመን ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ያላትና በአህጉሪቱ መሃል ያለች ሀገር እንደመሆኗ፤ ሰራዊታችን በአውሮፓ ውስጥ የመደበኛ መከላከያ የማዕዘን ድንጋይ መሆን አለበት” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የሩስያ-ዩክሬን ጦርነት ፤ ጀርመን በመከላከያ ፖሊሲዋ ላይ ለውጥ በማድረግ ጦሯን ይበልጥ ለማጠናከር የ100 ቢሊዮን ዩሮ ልዩ ተጨማሪ ፈንድ ለማድረግ ያስገደደ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር ጀርመን በወዳጆቿ የተከበበች ሀገር ናት የሚል የተሳሳተ እምነት እንደነበራቸው ያነሱት ኦላፍ ሾልዝ፤ ጀርመን ከራሷ አልፎ የአውሮፓን ደህንነት የሚያረጋጋ ጦር የመገንባቷ ጉዳይ ግድ መሆኑም አንስተዋል፡፡

“ጀርመን ለአህጉራችን ደህንነት የመሪነት ሀላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን በግልጽ እና በታማኝነት እያሳየን ነው” ብለዋል ኦላፍ ሾልዝ።

ኦላፍ ሾልዝ፤ የአውሮፓ ሀገራት በሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ጥላ ስር ሆነው የበለጠ ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል።

“እኛ አውሮፓውያን በኔቶ ውስጥ የበለጠ ሀላፊነት መውሰድ አለብን፤ ዘመናዊ እና ብቃት ያለው ጦር ያሏቸው ሁለቱ የአውሮፓ ሀገራት ፊንላንድ እና ስዊድን በቅርቡ ወደ ኔቶ መቀላቀላቸው በጣም ጥሩ ነው” ማታቸውም ዩሮ ኒውስ ዘግቧል፡፡

 ኦላፍ ሾልዝ ባለፈው አመት በአፍጋኒስታን እንደነበረው እንደ ኢራቅ ፣ ማሊ እና ኒጀር በመሳሰሉና የአውሮፓ ምክር ወይም የስልጠና ተልእኮዎችን የሚያስፈልጋቸው ሀገራት ላይ ተልእኮዎችን ለመወጣት የሚያስችሉ “የአውሮፓ ዋና መስሪያ ቤቶች” ማቋቋም እንደሚደግፉም ተናግረዋል፡፡

ለዩክሬን ወታደራዊ ድጋፍ ለመላክ ዘግይተዋል ተብለው ሲተቹ የነበሩት የጀርመኑ መራሄ መንግስት፤ አሁን ላይ ለኪቭ የሚያደርጉት ድጋፍ አጠናክረው መቀጠላቸው የሚታወቅ ነው፡፡

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸውም ይታወሳል።

ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ መግለጻቸውም አይዘነጋም

News today, Technology

በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር የሚጓዘው በራሪ ሞተር ሳይክል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ አዲስ በራሪ ሞተር ሳይክል ይፋ አድርጓል

በራሪው ሞተር ሳይክል በቀጣዩ 2023 ለገበያ ይቀርባል ተብሏል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የዓለማችን የመጀመሪያው በራሪ ሞተር ሳይክል ከሰሞበኑ ይፋ አድርጓል።

በአሜሪካ ዴትሮይት እየተካሄደ ያለው አውቶሞቲቭ ሾው ላይ የቀረበው በራሪው ሞተር ሳይክል የበርካቶችን ቀልብ ይዟል።

በራሪ ሞተር ሳይክሉን የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የሰራው ሲሆን፤ ሞተር ሳይክሉ ለ40 ደቂቃ ያክል አየር ላይ መብረር ይችላል።

ዚቱሪስሞ በራሪ ሞተር ሳይክሉ በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መብረር የሚችል መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል።

የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ ኩባንያው ከበራሪ ሞተር ሳይክል በተጨማሪ ድሮኖች እና በራሪ መኪናዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ በጃፓን መሸጥ ጀምሯል ያሉት ስራ አስፈጻሚው፤ በአሜሪካ እና በሌሎች የዓለም ሀገራት ከ2023 ጀምሮ ለገበያ ይቀርባል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ የተገመተለት ዋጋም 777 ሸህ ዶላር ነው።

8የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ እስከ ፈረንጆቹ 2025 ባለው ጊዜ በኤሌክትሪ የሚሰራውን በራሪ ሞተር ሳይክል ዋጋ ወደ 55 ሺህ ዶላር የመቀነስ ተስፋ እንዳለ አስታውቀዋል።

News today, Politics

አራን፤ በሩሲያ እና ቻይና የሚመራውን የጸጥታ ጥምረት ልትቀላቀል ነው

ኤስሲኦ ተሰኘው የጸጥታ ቡድን የተመሰረተው በፈረንጆቹ 2011 ነበር

በአሜሪካ የሚደገፈው የአረብ-እስራኤል ጥምረት ኢራን ከሩሲያ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት እንድትመሰርት ገፋፍቷታል ተብሏል

የአሜሪካን የኢኮኖሚ ማእቀብ ለመቋቋም ጥረት እያደረገች ያለችው ኢራን በሩሲያ እና በቻይና የሚመራው የሴንትራል እሲያ የጸጥታ አካል ቋሚ አባል ለመሆን ቀርባለች፡፡

ባለፈው ሃሙስ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አሚርአብዶላሂያን ስብሰባውን በዚህ ሳምንት ያካሄደውን የሻንጋይ ኮኦፐሬሽን ድርጅት(ኤስሲኦ) ለመቀለቀል የሚያስችል መግባባቢያ ሰነድ መፈረማቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በፈረንቹ 2001 የተቋቋመው በሩሲያ እና ቻይና የነበረ ሲሆን ከተመሰረተ ከአራት አመት በኋላ ህንድ እና ፓኪስታንን አካቷል፤ ይህም በቀጣናው ያለውን የምእራባውያን ጫና ለመቋቋም አላማ ያደረገ ነበር፡፡

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢንስታግራም ገጻቸው እንደጻፉት ኢራን የኤስሲኦ ሙሉ አባል ለመሆን በመፈረም፣ ኢራን የኢኮኖሚ፤የንግድ እና የኢነርጅ ትብብር የምታደርግበት አዲስ ምእራፍ ውስጥ ገብታለች ሲሉ ጽፈዋል፡፡

የኢራን ፕሬዝደንት ኢብራሂም ሬኢሲ በኡዝቤክስታን የተካሄውን የተካፈሉ ሲሆን በወቅቱም ከሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን ጋር ተገናኝተው የነበሩ መሆኑን የኢራን ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡

አውዛጋቢ በሆነው የኢራን የኑክለር ጉዳይ ምእራባውያን የጣሉባትን መእቀብ የምትቋቋምበትን መንገድ የኤስሲኦ አባልት እንዲረዷት መጠየቋን ተከትሎ ነበር ወደ ቡድኑ እንድትገባ የተፈቀደላት፡፡

 ያእደገ የመጣው ማእቀብ እና በአሜሪካ የሚደገፈው የአረብ-እስራኤል ጥምረት የኢራኑን መሪ ከሩሲያ ጋር ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት እንድትመሰርት እንደገፋፋቸው ዘገባው ጠቅሷል፡፡

“ኢራን ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ከኢኮኖሚ እስከ ኤሮስፔስ እና የፖለቲካ ዘርፎች ለማሳደግ ቆርጣ ተነስታለች” ሲሉ ራይሲ ለፑቲን በስብሰባቸው ወቅት ተናግረዋል።

“በቴህራን እና በሞስኮ መካከል ያለው ትብብር በአገሮቻችን ላይ በዩኤስ ማዕቀቦች ላይ የተጣለውን ውስንነት በእጅጉ ያስወግዳል”ብለዋል።

News today, social life

ስደተኞችን በግል ጄት ጭነው አውሮፓ ያሻገሩ ተከሰሱ

የቤልጂየም ፖሊስ ሁለት ጄቶችን ይዟል።
የምስሉ መግለጫ,ስደተኞቹ ሐሰተኛ የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ታድለዋል

15 መስከረም 2022

የግል ጄት በመጠቀም ስደተኞችን ወደ ምዕራብ አውሮፓ ያሻገሩ አምስት ሰዎች ተከሰሱ።

አምስቱ ሰዎች የተከሰሱት በጣሊያን ፍርድ ቤት ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ስደተኞቹን ወደ አውሮፓ በግል አውሮፕላን ጭነው ያስገቡት ለሰዎቹ ሐሰተኛ የዲፕሎማት ፓስፖርት ካደሏቸው በኋላ ነው ተብሏል።

ፓስፖርቱ የካሪቢያን ደሴት የሆነችው ሴንት ኪተስ ኤንድ ኔቪሰ እንደሆነ ተመላክቷል።

የግል አውሮፕላኑ እነዚህን ስደተኞች ከቱርክ ከጫናቸው በኋላ በአንድ የአውሮፓ አገር አየር ማረፊያ አራግፈዋቸዋል።

በዚያም ግለሰቦቹ እውነተኛ ማንነታቸውን በመግለጽ የጥገኝነት ጥያቄን አቅርበዋል።

ፖሊስ እንደሚለው እነዚህን ግለሰቦች በግል ጄት ጭኖ አውሮፓ ለማስገባት ተጠርጣሪው ቡድን ከእያንዳንዳቸው 10ሺህ ዩሮ ሳይቀበል አልቀረም።

ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው ከተጠረጠሩት አምስት ግለሰቦች መሀል ሦስቱ በሮምና በብራስልስ ከተሞች ተይዘዋል።

ሁለቱ አሁንም በፍለጋ ላይ ናቸው።

 ከተጠርጣሪዎቹ አንዱ ጣሊያናዊ ሲሆን ሦስት የግብጽ ዜጎችና አንዲት ቱኒዚያዊት ሴት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፖሊስ ኃላፊ የሆኑት ኮስታንቲኖ ስኩዲየር ለሮይተርስ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ የሌላ ግዙፍ ሕገ ወጥ የስደተኛ አሸጋጋሪ ቡድን አባላት እንደሆኑ ግምት በመውሰድ ክስ ተመሥርቶባቸዋል።

ወንጀለኞቹን አድኖ በመያዙ ረገድ ቤልጅየም፣ ጀርመን፣ ኦስትሪያ፣ ፈረንሳይ እና የአሜሪካ የጸጥታና ደኅንነት አካላት እገዛ እንዳደረጉ ተነግሯል።

News today, Politics

ኪም ጆንግ ኡን የሰሜን ኮሪያን “የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር” ሲሉ አወጁ

የሀገሪቱ ፓርላማ በአደጋ ወቅት በጠላት ኢላማዎች ላይ የኒውክሌር ጥቃት እንድትፈጽም የሚፈቅ ህግ አጽድቋል

በኒውክሌር ጉዳይ ድርድር የለም ያሉት ኪም ጆንግ ኡን “ሰላም ሊገኝ የሚችለውም በኃይል ብቻ ነው” ብለዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸውን “የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር” ሆናለች ሲሉ አወጁ፡፡

ኪም ጆንግ ኡን ሊቀለበስ የማይችል ነው ባሉት ውሳኔያቸው፤ ሀገራቸው የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር የሆነችበትን አዲስ ህግ ይፋ አድርገዋል።

” ሀገራችን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ሆናለች” ብለዋል ኪም ጆንግ ኡን።

“በአዲሱ ህግ መሰረት የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቻችን ጉዳይ መደራደር የማይታሰብ ነው፤ ሰላም ሊገኝ የሚችለውም በኃይል ብቻ ነው” ሲሉም አክለዋል፡፡

“ሀገራችንን ከኒውክሌር ነፃ ለማድረግ ምንም አይነት ድርድር አይኖርም” ሲሉም ነው የተደመጡት ኪም ጆንግ ኡን፡፡

የሀገሪቱ ፓርላማም ዛሬ ረፋድ ላይ ሀገሪቱ አደጋዎች በሚጋረጡባት ወቅት በጠላት ኢላማዎች ላይ የኒውክሌር ጥቃትን እንድትጀምር የሚፈቅደውን ህግ አጽድቋል፡፡

በዚህም ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መያዝን እንደ ህጋዊ ጉዳይ ፣አስፈላጊና መሰረታዊ መብት አድርጋ በመመልከት ባጸደቀችው አዲስ ህግ ራሷን “የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ያላት ሀገር” መሆኗ አውጃለች ሲል የኮሪያ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡

ነገር ግን በአዲሱ ህግ መሰረት የኒውክሌር ጦር መሳሪያን ከማንም ጋር እንደማትጋራ እንዲሁም የአቶሚክ ቴክኖሎጂ እና ቁሳቁስ እንደማታስተላልፍም አስታውቃለች።

ሰሜን ኮሪያ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኒውክሌር ሙከራ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።

እንደፈረንጆቹ በ2018 የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕና ሌሎች መሪዎች ሰሜን ኮሪያ ኒውክሌር ማበልጸጓን እንድትተው ኪም ጆንግ ኡንን ለማሳመን ያደረጉት ጥረት እንዳልተሳካ የሚታወስ ነው፡፡

News today, Politics

ከ80 በመቶ በላይ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በተሳሳተ መንገድ ላይ እንዳለች ያምናሉ ተባለ

እድሜያቸው 55 እና ከዛ በላይ የሆኑ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ ናት ብለው ያምናሉ ተብሏል

የአሜሪካው ሞንማውዝ የተሰኘው ዩንቨርስቲ በአሜሪካ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያጠናውን ጥናት ይፋ አድርጓል

ከ80 በመቶ በላይ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በተሳሳተ መንገድ ላይ እንዳለች እንደሚያምኑ ጥናት አመለከተ።

የአሜሪካው ሞንማውዝ ዩንቨርስቲ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ አሜሪካዊያን አሁን ባለው አስተዳድር  ላይ ያላቸውን አመለካከት ለማወቅ ጥናት አካሂዷል

በዚህ ጥናት ላይ 978 ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን በጥናቱ ከተሳተፉ ሰዎች መካከል ከ80 በላይ ያህሉ አሜሪካ በተሳሳተ መንገድ እየተጓዘች እንደሆነ ያምናሉ።

በጥናቱ ከተሳተፉት ውስጥ እድሜያቸው 55 እና ከዛ በላይ ከሆናቸው ሰዎች ውስጥ 16 በመቶዎቹ ግን ሀገራቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ መሆኗን ያምናሉ ሲል ዘ ሂል የተሰኘው የአሜሪካው ሚዲያ ዘግቧል።

በዚህ ጥናት መሰረት አሜሪካ በታሪኳ በህዝቧ ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው የጥናት ውጤት አሳይታለች ተብሏል።

ዩንቨርሲቲው ግንቦት ወር ላይ ተመሳሳይ ጥናት ማካሄዱ የተገለጸ ሲሆን በሀምሌ ወር ላይ የተገኘው የጥናት ውጤት ግን ሀገራቸው በተሳሳተ ጎዳና ላይ እንደሆነች የሚያምኑ አሜሪካዊያን ቁጥር በ9 በመቶ ጨምረዋል።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንእና ካቢኔያቸው

የጥናቱ ተሳታፊዎች ከመላው የአሜሪካ ግዛቶች የተካተቱ ሲሆን በዚህ ጥናት መሰረት አሜሪካ በታሪኳ ከፍተኛው ችግር ላይ ትገኛለች ተብሏል።

በትናቱ ከተሳተፉ ሰዎች ውስጥ 92 በመቶ የሚሆኑት የሪፐብሊካን ፓርቲ ደጋፊዎች አሜሪካ በተሳሳተ መንገድ ላይ ነች ብለው ያምናሉም ተብሏል።

በጥናቱ ከተሳተፉ የሪፐብሊካን ፓርቲ ደጋፊዎች ውስጥ 6 በመቶዎቹ ብቻ ሀገራቸው በትክክለኛውም መንገድ ላይ ናት የሚል አመለካከት እንዳላቸው ተገልጿል።

በአሜሪካ የጋዝ ምርቶች ዋጋ ማሻቀብ፣ እና የኑሮ ውድነቱ የአሜሪካዊያን ዋነኛ የወቅቱ ችግር እንደሆነም በጥናቱ የተሳተፉ ሰዎች ተናግረዋል።

ይሄንንም ተከትሎ በጥናቱ ከተሳተፉ አሜሪካዊያን ውስጥ 38 በመቶ የሚሆኑ አሜሪካዊያን በቅርቡ የሚካሄደውን የኮንግረስ ምርጫ ዲሞክራቶች እንዲቆጣጠሩት ሲፈልጉ 36 በመቶዎቹ መላሾች ደግሞ ኮንግረሱን ሪፐብሊካኖች እንዲይዙት እንደሚፈልጉም ጥናቱ ያሳያል።

News today, Politics

ዶላርን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው-ፑቲን

ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ተስማምታለች

ከዓለም ዙሪያ

2022/9/12 13:28 GMT

ፕሬዝደንት ፑቱን

ሩሲያ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት መስማማቷ ይታወሳል

ዶላን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ፕሬዝደንት ፑቲን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝደንት ፑቱን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ንግግር ባሰሙበት ወቅት ሩሲያ ከምእራባውያን የተሰነዘሩባትን መእቀቦች መቋቋም መቻሏን መግጻቸውን የሩሲያው አርቲ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ማእቀቦቹን የተቋቋመችው የተለያዩ የመከላከያ መንገዶችን በመጠቀም ነው ብለዋል ፑቲን፡፡

በቀጣይ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች ላይ የተናገሩት ፑቲን ዶላርን ከመገበያያነት የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ላይ “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ አሜሪካን ጨምሮ ምእራባውያን በሺዎች የሚቆጠሩ ማእቀቦችን ጥለውባታል፡፡ ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ከስምምነት መድረሷ ይታወሳል፡፡

ሩሲያ ምእራባውያን ለሚገዙት ጋዝ በሩሲያ ገንዘብ ሩብል እንከፍሉ በማድረግ እና ከዚህም አለፍ ሲል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዝጋት በምእራባውያን ሀገራት የአጸፋ እርምጃ ወስዳለች፡፡ በቅርቡ ለጥገና በሚል የዘጋችው ጋዝን ከሩሲያ ወደ ጀርመን የሚደውስደው ኖርድ ስትሪም 1 የተሰኘውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር እንደማትከፍት መግለጽ ይታወሳል፡፡

ጀርመን በሩሲያ ውሳኔ በእጅጉ አዝናለች፡፡

ሩሲያ እውቅና የሰጠቻቸው ሉሃንስክ ግዛት አሁን ሙሉበሙሉ ነጻ የወጣ ሲሆን የዶምባስ ግዛትን ሙሉ ለሙሉ ነጻ ለማውጣት ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡፡

ዩክሬን በቅርቡ በሩሲያ ሃይሎች ላይ ድል በመቀዳጀት የተወሰኑ ቦታዎች ማስለቀቋን እየገለጸች፤ ነገርግን ሩሲያ ቦታ የለቀቀችው ጦሯን በደንብ ለማደራጀት ነው ብላለች፡፡

News today, Politics

ለንግሥት ኤልዛቤጥ ቀብር የቻይና መንግሥት መጋበዙ የምክር ቤት አባላትን አስቆጣ

በዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ ሥርዓተ ቀብር ላይ የቻይና መንግሥት ተወካዮች እንዲገኙ የቀረበው ግብዣ እንዲሰረዝ የዩናይትድ ኪንግደም ፖለቲከኞች እና የምክር ቤት አባላት ጠየቁ።

የቻይና መንግሥት ተወካዮች በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ በዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) መንግሥት መጋበዛቸው አሳስቦናል በማለት ለአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ደብዳቤ ከጻፉት መካከል የወግ አጥባቂው ፓርቲ ጉምቱ አባላት ይገኙበታል።

የምክር ቤት አባላቱ በቻእና አነሳ በሆኑት ዊገር ሙስሊም ማኅብረሰብ አባላት ላይ “የዘር ማጥፋት” ወንጀል የሚያስጽሙት ባለሥልጣንት መጋበዛቸው አሳሳቢ ነው ብለዋል።

የፊታችን ሰኞ መስከረም 09/2015 ዓ.ም. በሚከናወነው የንግሥቲቱ ሥርዓተ ቀብር ላይ እንዲገኙ ለቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ይፋዊ ጥሪ የቀረበ ቢሆንም ፕሬዝዳንቱ ግን ይገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም።

ፕሬዝዳንቱ በዚህ ሳምንት ከሁለት ዓመታት በኋላ በመጀመሪያቸው በሆነው የውጭ አገር የሥራ ጉብኝት ጉዟቸው ወደ ካዛኪስታን እና ኡዝቤኪስታን አቅንተዋል።

የቻይናው ‘ሳውዝ ቻይና ሞርኒን ፖስት’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ምክትል ፕሬዝዳንት ዋንግ ኪሻን ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በንግሥቷ ቀብር ላይ ማን ይገኛል?

በንግሥቲቱ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ወደ 500 የሚጠጉ ርዕሳነ ብሔራት እና የውጭ አገር ተወካዮች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አብዛኞቹ መሪዎች በንግድ አውሮፕላን በረራዎች እንዲመጡ የተጠየቁ ሲሆን፤ ምዕራብ ለንደን ከሚገኝ ቦታ በአውቶብስ እንደሚጓጓዙም ተነግሯቸዋል ተብሏል።

በዕለቱ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከሚገኙት መካከል ከመላው አውሮፓ የሚመጡ ንጉሣውያን ቤተሰብ አባላት ይገኙበታል።

የቤልጂየም፣ የኔዘርላንድስ፣ የስፔን ነገሥታት የሚገኙ ሲሆን፣ የኖርዌይ፣ የስዊድን፣ የዴንማርክ እና የሞናኮ ንጉሣውያን ቤተሰቦችም በቀብሩ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

ከአገራት መሪዎች መካከል የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከእነ ባለቤታቸው በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደሚገኙ ዋይት ሐውስ አረጋግጧል።

ከኮመንዌልዝ አገራት መሪዎች መካከል የአውስትራሊ፣ የካናዳ እና የኒው ዚላንድ ጠቅላይ ሚንስትሮች ጥሪውን ተቀብለዋል።

የጀርመን፣ የጣሊያን፣ የፈረንሳይ፣ የደቡብ ኮሪያ፣ የብራዚል እና የቱርክ ፕሬዝዳንቶችም እንደሚገኙ ይጠበቃል።

ያልተገባዙትስ እነማን ናቸው?

ከሩሲያ፣ ከቤላሩስ እና ከሚያንማር በዩናይትድ ኪንግደም ንግሥት የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ የተጋበዙ ባለሥልጣንት የሉም።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በንግሥቲቱ ቀብር ላይ የመገኘት ዕቅድ እንደሌላቸው ቃል አቀባያቸው ቀደም ሲል ተናግረው ነበር።

ዩናይትድ ኪንግደም ከሶሪያ፣ ከቬንዙዌላ እና ከአፍጋኒስታን ጋር ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስለሌላት ከእነዚህ አገራት በሥነ ሥርዓቱ ላይ የሚገኝ አይኖርም።

ሰሜን ኮሪያ፣ ኢራን እና ኒካራጉዋ ደግሞ አምባሳደሮቻቸውን ብቻ እንዲልኩ ተጋብዘዋል።

News today, Politics

የቻይናና የሩሲያ የባህር ኃሎች በፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ የውጊያ ልምምድ አካሄዱ

በሩሲያና በቻይና መርከቦች መካከል የመረጃ ልውውጥ እና የኢላማ ተኩስ የልምምዱ አካል ናቸው

የቻይናና የሩሲያ የባህር ኃሎች

የጦር ልምምዱ በሩሲያና በቻይና ባህር ኃሎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ነው

የቻይና እና የሩሲያ ባህር ኃይሎች በፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ ታክቲካዊ የውጊያ ልምምድ ማድረጋቸው ተገለፀ።

በጦር ልምምዱ ላይ የሩሲያ ባህር ኃይል አባላት ከቻይና አቻቸው ጋር የኮሙዩኒኬሽን እና ሌሎችም ወታደራዊ ልምምዶችን ማድረጋቸውን አር.ቲ ዘግቧል።

በልምመዱም በቻይና እና በሩሲያ የጦር መርከቦች መካከል ግንኙነት እንዴት መለዋወጥ እንደሚችል፣ የባህር ላይ የተኩስ ልምምድ እና የጦር መርከብ ሄሊኮፕተር ድጋፍ አሰጣጥ ላይ ልምምድ አድርገዋል።

የውጊያ ልምምዱ በቤጂንግ እና በሞስኮ የባህር ኃይሎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏ።

በተጨማሪም ልምምዱ የእሲያ-ፓስፊክ ቀጠናን ሰላም እና መረጋጋት ለማስጠበቅ እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ እንቅቃሴዎችን ለመጠበቅ ያለመ ነው።

የቻይና እና የሩሲያ ወታደሮች ከሳምንታት በፊት ሩሲያ አስተናጋጅነት በተካሄደው የቮሶቶክ 2022 ወታደራዊ ልምምድ ላይ የጋራ ልምምድ አድርገው እንደነበረ ይታወሳል።

በዚሁ ልምምድ ላይ የቻይና እና የሩሲያ ወታደሮች በጋራ ወታደራዊ የኢላማ ተኩስ ልምምድ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በዚህም የሩሲያ የፓስፊክ የባህር ኃይል እና የቻይና ባህር ኃይል ከጦር መርከቦች ላይ በመሆን የምድር ላይ ኢላማዎችን የመምታት የተኩስ ልምምድ አካሂደዋል ነው የተባለው።

በወቅቱም ቻይን ቻይና የጦር ልምምዱ ከወቅቱ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር እንደማይገናኝ መግለጿ ይታወሳል።

News today, Politics

ለዩክሬን የረጅም ርቀት መሳሪያ ማስታጠቅ ቀይ መስመርን ማለፍ ነው ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች

ዩክሬን የረጅም ርቀት ተተኳሽ የጦር መሳሪያ እንዲሰጣት ለአሜሪካ ጥያቄ አቅርባለች

የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 206ኛ ቀኑ ላይ ይገኛል

ለዩክሬን የረጅም ርቀት መሳሪያ ማስታጠቅ ቀይ መስመርን ነው ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች፡፡

ከስድስት ወር በፊት የተጀመረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ሀያላን ሀገራት ጎራ ለይተው ድጋፍ በማሰባሰብ ላይ ይገኛሉ፡፡

በዚህ ጦርነት ሩሲያ እንድትሸነፍ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የተለያዩ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን በማስታጠቅ ላይ ናቸው፡፡

ዩክሬንም ከነዚህ ሀገራት የሚደረግላትን የጦር መሳሪያ በመጠቀም በሩሲያ ተይዘው የነበሩ ቦታዎችን መልሳ በማስለቀቅ ላይ ስትሆን አሜሪካ የረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ የጦር መሳሪያዎች እንዲሰጧት ጠይቃለች፡፡

ሩሲያ በበኩሏ ለዩክሬን የረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ የጦር መሳሪያ ማስታጠቅ ማለት ቀይ መስመርን ማለፍ ነው ስትል አስጠንቅቃለች፡፡

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እንዳሉት አሜሪካ ለዩክሬን የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያ ካስታጠቀች ሞስኮ ራሷን ለመከላከል ስትል እርምጃ ትወስዳለች ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የአሜሪካ መከላከያ ዋና አዛዥ ሊዮድ ኦስቲን ሀገራቸው ለዩክሬን ተጨማሪ የ675 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው የጦር መሳሪያዎች ልትሰጥ እንደምትችል ተናግረዋል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው ከአሜሪካ እና ምዕራባዊያን በሚደረግላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በሩሲያ ጦር ተይዘው የነበሩ አካባቢዎችን እያስለቀቁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሩሲያ የተያዙ ሌሎች የዩክሬን ግዛቶችን ለማስለቀቅም የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያዎች እና ሌሎች አጋዥ መሳሪያዎች ድጋፍ እንዲደረግላቸው ለአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት ሀገራት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ለሰባት ወራት በዘለቀው የሩሲያ ጦርነት ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ወታደሮች እና ንጹሃን የተገደሉ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሀገራት እንደተሰደዱ ተመድ ገልጿል፡፡ 

News today, Politics, social life

ግብፅና ኳታር በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች በትብብር ለመስራት ስምምነት ተፈራረሙ

የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ ከ4 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር ጉብኝት አድርገዋል

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም በሁለትሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል

የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አል ሲሲ በኳታር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተገልቷል።

ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ ከአራት ዓመታት ወዲህ በሳለፍነው ማክሰኞ ለመጀመሪያ ጊዜ ዶሃ ሲደርሱም በኳታር ኢሚር ታሚም አቀባባበል ተደርጎላቸዋል።

በትናትናው እለትም የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ እና የኳታሩ ኢሚር ታሚም በሀገራ የሆለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተመካክረዋል።

በዚህም የኳታሩ ኢሚር ታሚም ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እንዲያደግ እየሰሩት ላው ስራ ማማስገናቸውን የኳታር የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል።

የፕሬዝዳንት አል ሲሲ ግብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናከር እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በበኩላቸው፤ ግብጽ ከኳታ ጋር በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ እና በደህንነት ዘርፎች ከኳታር ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ውይይቱን ተከትሎም ሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተካሄደ ሲሆን፤ ከስምምነቶቹ ውስጥም ልማትና ኢንቨስምንት እንዲሁም የማህበራዊ ዘርፍ ይገኝበታል።

News today, Politics

የስዊድኗ ጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ማግዳሊና አንደርሰን የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ ለፓርላማው አስገብተዋል

ጠቅላይ ሚኒስትሯ መልቀቂያ ያስገቡት ፓርቲያቸው በምርጫ መሸነፉን ተከትሎ ነው

የስዊድኗ ጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ ፡፡

ባለፈው እሁድ በስዊድን የህግ አውጪ ምክር ቤት ምርጫ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን ሀገሪቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነት የሚመሩት አንደርሰን ፓርቲ በምርጫው ተሸንፏል፡፡

ይሄንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትር አንደርሰን የግድ መንግስታቸውን አፍርሰው በምርጫው ላሸነፈው ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች ስልጣን ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም ጠቅላይ ሚኒስትር አንደርሰን ለሀገሪቱ ህግ አውጪ ምክር ቤት የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

የስዊድን ግራ ዘመመም ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የነበረውን ምርጫ አሸንፈፈው ጠቅላይ ሚኒስትር ማግደሊና አንደርሰንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሾመው የነበረ ሲሆን አሁን በተካሄደው ምርጫ ደግሞ ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች በጠባብ ልዩነት አሸንፈዋል፡፡

ግራ ዘመም ፓርቲዎች ምርጫውን 173 ለ176 ድምጽ ልዩነት የተሸነፉ ሲሆን የሞደሬት ፓርቲ መሪ የሆኑት ኡልፍ ክሪሰትረሰን አዲስ መንግስት እንደሚመሰርቱ ይጠበቃልም ተብሏል፡፡

ላለፉት 11 ወራት ስዊድንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት አንደርሰን የኑሮ ውድነት፣ የስደተኞች አያያዝ እና የግድያ ወንጀሎች መበራከት በምርጫው እንዲሸነፉ ዋነኛ ምክንያቶች እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

የስዊድን ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች በሀገራቸው አጥፊዎች ረጅም ዓመት የሚቆይ እስር እንዲፈረድባቸው ማድረግ ፣ስደተኞች ለሀገራቸው ደህንነት አደጋ በማይሆኑበት መንገድ እንዲያዙ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የምረጡኝ ቅስቀሳቸው ዋነኛ አጀንዳዎች ነበሩ፡፡

News today, Politics

የጀርመን መራሄ መንግስት “ሩሲያ ከዩክሬን ምድር ሙሉ በሙሉ ለቃ እንድትወጣ” ፑቲንን ጠየቁ


ኦላፍ ሾልዝ፤ ፑቲን በተቻለ ፍጥነት ወደ “ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ” እንዲመጡ አሳስበዋል
የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ “ሩሲያ ከዩክሬን ምድር ሙሉ በሙሉ ለቃ እንድትወጣ” ፑቲንን ጠየቁ፡፡


ኦላፍ ሾልዝ ከፑቲን ጋር በነበራቸው 90 ደቂቃ በፈጀ የስልክ ቆይታ ፤ “ፑቲን በተቻለ ፍጥነት ተኩስ አቁመው ወደ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲመጡና ወታደራቸው ሙሉ በሙሉ ከዩክሬን ምድር በማውጣት የዩክሬን ግዛት ሉዓላዊነት እንዲያከብሩ” ማሳሰባቸው ቃል አቀባያቸው ስቴፈን ሃበስተሬት አስታውቋል፡፡


ኦላፍ ሾልዝ በተጨማሪም ሩሲያ በተደጋጋሚ የምትወቅሰውን እህል ከዩክሬን ወደ ውጭ የመላክ ጉዳይ የተደረሰውን የእህል ስምምነት እንድታከብር ፑቲንን መናገራቸውም ኤኤፍፒ ዘግቧል።


ፑቲን የእህል ስምምነቱን እንዳያጣጥሉ እና ሙሉ በሙሉ መተግበሩን እንዲቀጥሉም የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ተማጽነዋል፡፡


ኦላፍ ሾልዝ አሁን ላይ የጦርነቱ የስህበት ማዕከል ስለሆነው የዛፖሪዝሂያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደህንነት ጉዳይ በተመለከተም ለፑቲን ጥያቄ አንስተው ተወያይተዋል፡፡


በዚህም የጀርመኑ መሪ ፑቲን “ምንም አይነት መባባስ እንዲያስወግዱና በዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የተመከሩትን እርምጃዎች (ነጻ ቀጠና እንዲቋቋም) ሙሉ በሙሉ እንዲተገብሩ” ጠይቀዋል።


የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ከፑቲን ጋር ዘለግ ያለ ቆይታ ያደረጉት፤ ሞስኮ በርሊን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላክ ቀይ መስመር እየጣሰች ነው የሚል ማስጠንቀቅያ በሰጠቀችበት ማግስት መሆኑ ነው፡፡


በጀርመን የሩሲያ አምባሳደር ሰርጌይ ናቼቭ ፤ የዩክሬን መንግስት ጀርመን ስሪት አውዳሚ ጦር መሳሪያዎችን እየታጠቀ መሆኑ ሀቅ ነው ማለታቸው አይዘነጋም፡፡
የጦር መሳሪያዎች በሩሲያ ጦር ላይ ብቻ ሳይሆን በዶንባስ ክልል በሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ለማጥቃት እየዋሉ እንደሆነም ነበር የተናገሩት አምባሳደሩ፡፡


የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸው ይታወሳል።


ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በገልጸውላቸዋል።


ጀርመን ቀይ መስመር አልፋለች ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች
ጀርመንም ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ለማቅረብ በሚል ፖሊሲ እስከ ማሻሻል ደርሳ እንደነበረ ይታወሳል።


ሩሲያም በተለያዩ ጊዜያት ከምእራባውያን ለዩክሬን ያበረከቷቸው የረጅም ርቀት ሮኬትን ጨምሮ ይለያዩ የጦር መሳሪያዎችን አወደምኩ ማለቷ አይዘነጋም።

News today, Politics

ዢ ዢንፒንግ እና ፑቲን ስለ ዩክሬን ጦርነት እንደሚወያዩ ተገለጸ

የቻይናው መሪ ዢ ዢንፒንግ እና የሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ስላለው ጦርነት እና በሌሎች “ዓለም አቀፋዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች” ዙሪያ በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚወያዩ ክሬምሊን ገለጸ።

መሪዎቹ በኡዝቤኪስታን የሚወያዩ ሲሆን ለምዕራቡ ዓለም “አማራጭ” በሚያሳየው ስብሰባ ላይ ነው የሚገናኙት ብሏል ክሬምሊን።

ዢ ዢንፒንግ እና ቭላድሚር ፑቲን

ዢ ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት በኋላ የመጀመሪያውን የባሕር ማዶ ጉብኝታቸውን እያደረጉ ነው።

ጉብኝቱ ዢ ሦስተኛ የሥልጣን ዘመን ለማግኘት በሚጥሩበት እና ፑቲን ከምዕራቡ ዓለም ጋር ያላቸው ግንኙነት በዩክሬን ጦርነት ምክንያት ዝቅተኛ ደረጃ በደረሰበት ወቅት የሚካሄድ ነው።

ዢ የሦስት ቀን ጉብኝታቸውን በካዛኪስታን ረቡዕ ጀምረዋል።

ከዚያም ለሁለት ቀናት በሚቆየውና በሳምርካንድ በሚካሄደው የሻንጋይ የትብብር ድርጅት (ኤስሲኦ) ስብሰባ ላይ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ይገናኛሉ።

ፑቲን ከሕንድ፣ ከፓኪስታን፣ ከቱርክ እና ከኢራን መሪዎች ጋርም ይገናኛሉ።

ከቻይናው መሪ ጋር የሚያደርጉት ውይይት “በተለየ መልኩ ጠቃሚ ነው” ሲሉ የክሬምሊን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቃል አቀባይ ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል።

ጉባኤው እየተካሄደ ካለው “ትልቅ የፖለቲካ ለውጥ ጀርባ የሚደረግ ነው” ብለዋል።

ኤስሲኦ እአአ በ2001 ከቀድሞ የሶቪየት ማዕከላዊ እስያ አራት አገራት ጋር የተመሠረተ ነው።

ቻይና እና ሩሲያ ድርጅቱን ለምዕራባውያን ቡድኖች እንደ አማራጭ ለማቀረብ ደፋ ቀና ሲሉ ቆይተዋል።

የዢ ጉብኝት ዜሮ ኮቪድ የተባለው ፖሊሲ በቀጠለበት እና በቻይና በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም የእንቅስቃሴ ገደብ በተጣለበት ወቅት ነው።

የተቀረው ዓለም ከቫይረሱ ጋር አብሮ መኖርን በመማር ወደ ቀድሞ  ሕይወት ሲመለስ ቤጂንግ ድንገተኛ ሁኔታ በተፈጠረ ቁጥር ሁሉንም ከተሞቿን እና ግዛቶችን መዝጋቷን ቀጥላለች።

ዢ ለመጨረሻ ጊዜ ከአገር ውጭ ጉብኝት ያደረጉት እአአ ጥር 2020 ምያንማርን ለመጎብኘት ሲያቀኑ ነው።

ይህም የመጀመርያው የእንቅስቃሴ ገደብ በውሃን ከመጣሉ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ነበር።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቻይና ለመቆየት የተገደዱ ሲሆን ሐምሌ ላይ ከዋናው ቻይና ውጭ ወደ ሆንግ ኮንግ አቅንተዋል።

ፑቲንም በውጭ አገራት ያልተለመደ ጉዞ እያደረጉ ነው።

የሩሲያ ወታደሮች ዩክሬንን ከወረሩ በኋላ በሐምሌ ወር ቴህራን ላይ ከቱርክ እና ከኢራን መሪዎች ጋር ካደረጉት ስብሰባ ወዲህ ይህ ሁለተኛው የውጭ ጉብኝታቸው ነው።

ሁለቱ መሪዎች በዚህ ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ ነው የሚገናኙት። ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት በየካቲት ወር ቤጂንግ ባዘጋጀችው የክረምት ኦሊምፒክ ነው።

በየካቲት የተካሄደውን ስብሰባ ተከትሎ ሁለቱ መሪዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ በአገሮቻቸው መካከል ያለውን ወዳጅነት “ገደብ የለሽ” ብለውታል።

ሩሲያ ከቀናት በኋላ ዩክሬንን ወረረች። ቻይና ወረራውን ማውገዟንም ሆነ መደገፏን አልገለፀችም።

ቤጂንግ ለጦርነቱ ተጠያቂዎቹ ሁለቱም ወገኖች ናቸው ትላለች።

ቻይና በሩሲያ ላይ የተጣለው ዓለም አቀፍ ማዕቀብ አካል አይደለችም። በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥም እያደገ መሄዱን ቀጥሏል።

ከዩክሬን ወረራ በኋላ ሕንድ እና ቻይና ከሩሲያ የሚያስገቡት ነዳጅ ጨምሯል።

ቻይና ከምዕራቡ ዓለም እና በተለይም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት በቅርብ ወራት ወዲህ ውጥረት ነግሦበታል።

የታይዋን ጉዳይ ደግሞ ነገሩን አባብሶታል። ቻይና ደሴቱን የግዛቴ አካል ነው ትላለች።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ደሴቲቱን መጎብኘታቸውን ተከትሎ “ምላሽ ለመስጠት” በሚል ቤጂንግ በታይዋን ዙሪያ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ አድርጋለች።

የቻይናን ጉዳይ የሚከታተሉ ባለሙያዎች እንደሚሉት በእንቅስቃሴ ገደብ እና ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ምክንያት ተግዳሮቶች ቢኖርባቸውም፣ ዢ ከሁለት ዓመት በኋላ ቻይናን ለቀው ለመውጣት መወሰናቸው በአመራሩ ላይ ያላቸውን እምነት ያሳያል።

ተንታኞች እንደሚሉት በመጪው ጥቅምት በሚካሄደው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ኮንግረስ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ለሦስተኛ ጊዜ እንዲመረጡ ይጠብቃሉ።

የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ማነው?

ኤስሲኦ በቻይና፣ ሩሲያ፣ ካዛኪስታን፣ ኪርጊስታን፣ ታጃኪስታን እና ኡዝቤኪስታን የተመሠረተ የአውሮፓ እና እስያ አገራት የፖለቲካ ፣ የምጣኔ ሀብት እና የደኅንነት ድርጅት ነው።

ኢራን በ2001 የተቋቋመውን ድርጅት ለመቀላቀል ፍላጎት አላት።

ቻይና በቤልት ኤንድ ሮድ ፕሮጀክቶቿ በቀጠናው ትልቅ መዋዕለ ንዋይ የምታፈስ ሲሆን አባላቱ በንግድ ዙሪያ ይወያያሉ።

ቤጂንግ ከአውሮፓ ጋር ለምታደርገው የንግድ ልውውጥ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን ለመዘርጋት የምትፈልግ ሲሆን የመካከለኛው እስያ አገራት ደግሞ ከቻይና ጋር የበለጠ ግንኙነት ለመፍጠር ጉጉት አላቸው።

ኪርጊስታን በ2023 ከቻይና እና ኡዝቤኪስታን ጋር የሚያገናኛትን አዲስ የባቡር መስመር ዝርጋታ እንደምትጀምር አስታውቃለች።

News today, Politics

ጀርመን ቀይ መስመር አልፋለች ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች

ጀርመን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላኳ ነው ከሩሲያ ማስጠንቀቂያ የደረሳት

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ

በበርሊን የሩሲያ አምባሳደር ጀርመን ለዩክሬን ያቀረበቻቸው የጦር መሳሪያዎች ነጹሃን እየተጎዱበት ነው ብለዋል

ጀርመን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላክ ቀይ መስመር እየጣሰች ነው ሲሉ በበርሊን የሩሲያ አምባሳደር አስጠነቀቁ።

በጀርመን የሩሲያ አምባሳደር ሰርጌይ ናቼቭ፤ የዩክሬን መንግስት ጀርመን ስሪት አውዳሚ ጦር መሳሪያዎችን እየታጠቀ መሆኑ ሀቅ ነው ብለዋል።

ነገር ግን በእነዚህ የጦር መሳሪያዎች በሩሲያ ጦር ላይ ብቻ ሳይሆን በዶንባስ ክልል በሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ለማጥቃት እየዋሉ ነው፤ ይህ ደግሞ ቀይ መስመርን መጣስ ነው ማለታቸውን አር.ቲ ዘግቧል።

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸው ይታወሳል።

አዲሱ የጦር መሳሪያ “ሱፐር ሞዴል ዊፐን” በመባል እንደሚጠራም መራሄ መንግስቱ የተናገሩ ሲሆን፤ በተጨማሪም ትልቅ የአየር መከላከያ ስርዓት፤ ራዳር እና ድሮኖች ለዩክሬን እንደሚላኩ አረጋግጠዋል።

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በገልጸውላቸዋል።

ዩከሬን እና ሩሲያ ወደ ጦርነት መግባታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ጀርመንም ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ለማቅረብ በሚል ፖሊሲ እስከ ማሻሻል ደርሳ እንደነበረ ይታወሳል።

ሩሲያም በተለያዩ ጊዜያት ከምእራባውያን ለዩክሬን ያበረከቷቸው የረጅም ርቀት ሮኬትን ጨምሮ ይለያዩ የጦር መሳሪያዎችን አወደምኩ ማለቷ አይዘነጋም።

News today, Politics

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃቶች እያደረስኩ ነው አለች

ሞስኮ የኪቭ ጦር በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች እየፈጸመ ነው ስትል ከሳለች

ፕሬዝደንት ዜለንስኪ በመልሶ ማጥቃት 6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ኃይሎች ነጻ ወጥቷል ብለዋል

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ “መጠነ ሰፊ ጥቃቶች” እያደረስኩ ነው አለች፡፡

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ጦር ላይ “የአየር፣ የሮኬት እና መድፍ የተቀናጀ ከፍተኛ ጥቃት እያደረሱ ነው” ብሏል፡፡

የክሬምሊን ባለስልጣናት የኪቭ ጦር መልሶ በያዘው ግዛት ውስጥ በሲቪሎች ላይ በደል ፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።

የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቃል አቀባይ በካርኪቭ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች መፈጸማቸው የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ መሆኑን ተናግረዋል።

https://facebook.com/KeAlemiZuriya

“ብዙ የቅጣት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው…ሰዎች እየተሰቃዩ ፣ እየተንገላቱ ነው “ሲሉም ነው ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።

ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች የወሰዱት እርምጃን ተከትሎ የሩሲያ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት ውስጥ ከሚገኙት ሁለት አካባቢዎች (ባላክሊያ እና ኢዚየም ) ለማፈግፈግ መገደዳቸው ሮይተርስ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡

በዚህም የዩክሬን ባለስልጣነት ወታደሮቻቸው ለሩሲያ ኃይሎች ወሳኝ አቅርቦት ማዕከል የሆነችውን ኩፒያንስክ መቆጣጠራቸው ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡

ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በሰጡት መገለጫ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።

የዩክሬን ባለስልጣነት ይህን ይበሉ እንጂ፤የተወሰደው የማፈግፈግ እርምጃ በምስራቅ ዩክሬን የመትገኘውን ዶንባስ ግዛት ነጻ ለማውጣት የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግ ያለመ መሆኑን የምትገለጸው ሩሲያ በዩክሬን ምድር ፈለገቸውን ዓለማ ከመፈጸም የሚያግዳት ኃይል እንደሌለ በመግለጽ ላይ ናት፡፡

ሩሲያ፤ “ዓላማዬን እስከማሳካ የሚቆም ወታደራዊ ዘመቻ የለም” ስትል በትናንትናው እለት መግለጿም አይዘነጋም፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻው መጀመሪያ ላይ የተቀመጡት አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ይቀጥላል” ብለዋል።

አሁን ላይ የሩሲያ አየር፣ ሮኬቶችና መድፍ ኃይሎች የኩፒያንስክ እና ኢዚዩም የከተማ ማዕከሎችን ጨምሮ በዩክሬን የጦር ኃይሎች ይዞታወች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በመሰንዘር ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ከኪቭ ጋር ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ንግግሮች ተጠይቀውም፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ኤኤፍፒ ዘግቧል።

News today, Politics

የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት ከ40 ዓመት ገደማ በኋላ ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ


የዋሸንግተን መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት ዝቅ ያለው በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ በመናሩ ነው


የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ከ40 ዓመት በኋላ ቅናሽ ማሳየቱ  ተገለጸ።
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስድስት ወራት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ በዓለም ምግብ እና ነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ እንዲመዘገብ ምክንያት ሆኗል።


 ጦርነቱ በዓለም ዲፕሎማሲ ላይ የተለያዩ መፋለሶችን ያስከተለ ሲሆን ሀገራት ከትብብር ይልቅ ጎራ ለይተው እንዲሰለፉ እያደረገም ይገኛል።
ባለፈው ሳምንት ብቻ 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ከመጠባበቂያዋ በማውጣት ለዜጎቿ እንዲሸጥ አድርጋለች።


አሜሪካ ከአንድ ዓመት በፊት በመጠባበቂያ ክፍሏ ያስቀመጠችው ነዳጅ 621 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ነበር።


ይሁንና በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መከሰትን ተከትሎ ባጋጠመ የነዳጅ ዋጋ መናር ምክንያት ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት በሚል ከመጠባበቂያ ክፍሏ እያወጣች በመሸጥ ላይ እንደምትገኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።
አሁን ላይ የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት መጠን 434 ሚሊዮን በርሜል ላይ ደርሷልም ተብሏል።


ከፈረንጆቹ 1984 ዓመት ጀምሮ የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት መጠን አሁን ካለበት መጠን ዝቅ ብሎ እንደማያውቅ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።


የአሜሪካ የነዳጅ አጠቃቀም መጠን በዚሁ ከቁጠለ ብሄራዊ የነዳጅ አጠቃቀም መጠን ወደ 358 ሚሊዮን በርሜል ዝቅ ይላል ተብሏል።


የዓለም ቀዳሚ ሰባት የበለጸጉ ሀገራት ስብስብ የሆነው የቡድን ሰባት ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ የዋጋ ተመን ማውጣታቸው ይታወሳል
ሩሲያ በበኩሏ ነዳጇን በሚያዋጣት ዋጋ ብቻ እንደምትሸጥ ገልጻ ወደ አውሮፓ የምትልከውን ነዳጅ ሙሉ ለሙሉ ማቋረጧ አይዘነጋም። 

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya

News today, Politics

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃቶች እያደረስኩ ነው አለች


የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ጦር ላይ “የአየር፣ የሮኬት እና መድፍ የተቀናጀ ከፍተኛ ጥቃት እያደረሱ ነው” ብሏል፡፡


የክሬምሊን ባለስልጣናት የኪቭ ጦር መልሶ በያዘው ግዛት ውስጥ በሲቪሎች ላይ በደል ፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።


የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቃል አቀባይ በካርኪቭ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች መፈጸማቸው የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ መሆኑን ተናግረዋል።


“ብዙ የቅጣት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው…ሰዎች እየተሰቃዩ ፣ እየተንገላቱ ነው “ሲሉም ነው ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።


ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች የወሰዱት እርምጃን ተከትሎ የሩሲያ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት ውስጥ ከሚገኙት ሁለት አካባቢዎች (ባላክሊያ እና ኢዚየም ) ለማፈግፈግ መገደዳቸው ሮይተርስ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡


በዚህም የዩክሬን ባለስልጣነት ወታደሮቻቸው ለሩሲያ ኃይሎች ወሳኝ አቅርቦት ማዕከል የሆነችውን ኩፒያንስክ መቆጣጠራቸው ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡
ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በሰጡት መገለጫ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።


የዩክሬን ባለስልጣነት ይህን ይበሉ እንጂ፤የተወሰደው የማፈግፈግ እርምጃ በምስራቅ ዩክሬን የመትገኘውን ዶንባስ ግዛት ነጻ ለማውጣት የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግ ያለመ መሆኑን የምትገለጸው ሩሲያ በዩክሬን ምድር ፈለገቸውን ዓለማ ከመፈጸም የሚያግዳት ኃይል እንደሌለ በመግለጽ ላይ ናት፡፡


ሩሲያ፤ “ዓላማዬን እስከማሳካ የሚቆም ወታደራዊ ዘመቻ የለም” ስትል በትናንትናው እለት መግለጿም አይዘነጋም፡፡


የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻው መጀመሪያ ላይ የተቀመጡት አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ይቀጥላል” ብለዋል።


አሁን ላይ የሩሲያ አየር፣ ሮኬቶችና መድፍ ኃይሎች የኩፒያንስክ እና ኢዚዩም የከተማ ማዕከሎችን ጨምሮ በዩክሬን የጦር ኃይሎች ይዞታወች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በመሰንዘር ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል።


ቃል አቀባዩ ከኪቭ ጋር ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ንግግሮች ተጠይቀውም፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ኤኤፍፒ ዘግቧል።

News today, Politics

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ
አርመን እና አዘርባጃን ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው


የአርመኒያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኒኮል ፓሺኒያን በትናንትናው እለት ከአዘርባጃን ጋር በነበረው ጦርነት 49 የአርመን ወታደሮች ተገድለዋል ሲሉ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።


በአርመን ፖርላማ ቀርበው ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዘርባጃን የአርመንን ይዞታዎች ማጥቃቷን እና ጦርነቱ አሁንም መቀጠሉን ተናግረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ግጭቱ ወደ ጦርነት እንዲያመራ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው።


በአርመን እና አዘርባጃን መካከል ለአስርት አመታ ያሰቆጠረው አለመግባባት ኒጋርኖ ካራባክ በተባለ ቦታ መጀመሩ ይታወሳል።


በኒጋርኖ ካራባክ የተመረው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ቆሞ የነበረ ቢሆንም በድጋሚጨሊቀሰቀስ ችሏል።
ሪሲያ እና አሜሪካ ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

Politics

ሩሲያ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት መስማማቷ ይታወሳል

ዶላን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ፕሬዝደንት ፑቲን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝደንት ፑቱን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ንግግር ባሰሙበት ወቅት ሩሲያ ከምእራባውያን የተሰነዘሩባትን መእቀቦች መቋቋም መቻሏን መግጻቸውን የሩሲያው አርቲ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ማእቀቦቹን የተቋቋመችው የተለያዩ የመከላከያ መንገዶችን በመጠቀም ነው ብለዋል ፑቲን፡፡

በቀጣይ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች ላይ የተናገሩት ፑቲን ዶላርን ከመገበያያነት የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ላይ “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ አሜሪካን ጨምሮ ምእራባውያን በሺዎች የሚቆጠሩ ማእቀቦችን ጥለውባታል፡፡ ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ከስምምነት መድረሷ ይታወሳል፡፡

ሩሲያ ምእራባውያን ለሚገዙት ጋዝ በሩሲያ ገንዘብ ሩብል እንከፍሉ በማድረግ እና ከዚህም አለፍ ሲል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዝጋት በምእራባውያን ሀገራት የአጸፋ እርምጃ ወስዳለች፡፡ በቅርቡ ለጥገና በሚል የዘጋችው ጋዝን ከሩሲያ ወደ ጀርመን የሚደውስደው ኖርድ ስትሪም 1 የተሰኘውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር እንደማትከፍት መግለጽ ይታወሳል፡፡

ጀርመን በሩሲያ ውሳኔ በእጅጉ አዝናለች፡፡

ሩሲያ እውቅና የሰጠቻቸው ሉሃንስክ ግዛት አሁን ሙሉበሙሉ ነጻ የወጣ ሲሆን የዶምባስ ግዛትን ሙሉ ለሙሉ ነጻ ለማውጣት ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡፡

ዩክሬን በቅርቡ በሩሲያ ሃይሎች ላይ ድል በመቀዳጀት የተወሰኑ ቦታዎች ማስለቀቋን እየገለጸች፤ ነገርግን ሩሲያ ቦታ የለቀቀችው ጦሯን በደንብ ለማደራጀት ነው ብላለች፡፡

Politics

ዩጋንዳ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ከፈለች

ዩጋንዳ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ከፈለች

የዩጋንዳ ወታደሮች ከ23 ዓመት በፊት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ግዛት ገብተው ጥቃት ፈጽመው ነበር።

ዲሞክራቲክ ኮንጎም ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት በመውሰድ ክስ መስርታ ነበር።

በዚህ ችሎት ላይ የዩጋንዳ ወታደሮቿ ባደረሱት ጉዳት መሰረት ለዲሞክራቲክ ኮንጎ 325 ሚሊዮን ዶላር በአምስት ዙር ክፍያ ካሳ እንድትከፍል የተወሰነባት ቢሆንም ላለፉት በርካታ ዓመታት ሳትከፍል ቆይታለች፡፡

በችሎቱ የተረታችው ዩጋንዳም ከ325 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ውስጥ 65 ሚሊዮን ዶላር ገንዘቡን ከቀናት በፊት እንደከፈለች ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

የዲሞክራቲክ ኮንጎ መንግስት ቃል አቀባይ ከዩጋንዳ መንግስት 65 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ክፍያው እንደተከፈላቸው አረጋግጠዋል፡፡

ዩጋንዳ የጎረቤቷን ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሉዓላዊ ድንበሯን ጥሳ በመግባት ከ10 ዓመት በላይ በርካታ ቦታዎችን በመቆጣጠር እና አማጺያንን በመርዳት ወንጀል ተከሳ ጥፋተኛ ተብላለች፡፡

በመጨረሻም ዩጋንዳ ጥፋቷን አምና ካሳዋን መክፈል መጀመሯን እና ከጎረቤቷ ጋር መልካም ግንኙነት እንደምትፈልግ አስታውቃለች፡፡

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya

Politics

ሩሲያ፤ “ዓላማዬን እስከማሳካ የሚቆም ወታደራዊ ዘመቻ የለም” አለች


የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” ብለዋል
ሞስኮ ይህን ያለችው ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርመጃ የሩሲያ ኃይሎች ቁልፍ ወታደራዊ ይዞታዎች ለመልቀቅ መገደዳቸውን ተከትሎ “ሩሲያ በዩክሬን የጀመረችው ዘመቻ ታቆም ይሆን?” በሚል ለሚነሳው ጥያቄ በሰጠችው ምላሽ ነው።


 ፕሬዝደንት ዘሌሰንኪ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የማጥቃት እርምጃ 2 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱን ተናገሩ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻው መጀመሪያ ላይ የተቀመጡት አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ይቀጥላል” ብለዋል።


አሁን ላይ የሩሲያ አየር፣ ሮኬቶችና መድፍ ኃይሎች የኩፒያንስክ እና ኢዚዩም የከተማ ማዕከሎችን ጨምሮ በዩክሬን የጦር ኃይሎች ይዞታወች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በመሰንዘር ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል።


ቃል አቀባዩ ከኪቭ ጋር ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ንግግሮች ተጠይቀውም፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ኤኤፍፒ ዘግቧል።


ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች የወሰዱት እርምጃን ተከትሎ የሩሲያ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት ውስጥ ከሚገኙት ሁለት አካባቢዎች (ባላክሊያ እና ኢዚየም ) ለማፈግፈግ መገደዳቸው ሮይተርስ ዘግቧል።


በዚህም የዩክሬን ባለስልጣነት ወታደሮቻቸው ለሩሲያ ኃይሎች ወሳኝ አቅርቦት ማዕከል የሆነችውን ኩፒያንስክ መቆጣጠራቸው በመግለጽ ላይ ናቸው።
ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ ቅዳሜ በሰጡት መገለጫ፤ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “2 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።


የጦር ግስጋሴው ሩሲያ በሚያዝያ ወር በኪቭ ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ከወጣች በኋላ የተገኘ በጣም ጠቃሚ ስኬት ነው ተብሎለታል።
ሩሲያ፤ በቁጥጥሯ ስር ባሉ የዩክሬን ግዛቶች በመጪው ህዳር ወር “ህዝበ ውሳኔ” ልታካሂድ ነው
የዩክሬን ባለስልጣነት ይህን ይበሉ እንጂ ፤ የሩሲያ ወታደሮች ያፈገፈጉት የዩክሬን መሪዎች እንደሚሉት ሳይሂን ለዓላማ እንደሆነ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢጎር ኮናሼንኮቭ ተናግረዋል።


ወታደሮቹ ከባላክሊያ እና ኢዚየም አካባቢዎች አፍግፍገው በዶኔትስክ ክልል ተሰባስበዋል ያሉት ኢጎር ኮናሼንኮቭ ፤ የተወሰደው የማፈግፈግ እርምጃ በምስራቅ ዩክሬን የመትገኘውን ዶንባስ ግዛት ነጻ ለማውጣት የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግ ያለመ መሆኑ ገልጸዋል።

News today, Politics, social life

የንግስት ኤልሳቤጥ ለ70 ዓመት የብሪታኒያ ንግስት ነበሩ

የብሪታንያ ንግስት ኤልሳቤጥ በ96 ዓመታቸው ማረፋቸው ተገለፀ።

ንግስቲቱ በስኮትላንድ ቤኪንግሀም ቤተ መንግሥት ማረፋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

የንግስቲቱ የቀብር ስነ ስርዓት ከ10 ቀን በኋላ ክብራቸውን በጠበቀ መንገድ እንደሚከናወንም ተገልጿል።

የንግስት ኤልሳቤትን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ ልዑል ቻርልስ የብሪታንያ በነገው ዕለት ንጉስ ሆነው እንደሚሾሙም ይጠበቃል።

ላለፉት 70 ዓመታት የብሪታንያ ንግስት የነበሩት ንግስት ኤልሳቤት በ96 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል።

ንግስቲቱ በኮሮና ቫይረስ እንዳይጠቁ የእንግሊዝ መንግሥት ልዩ ጥበቃ ሲያደርግላቸው ቆይቶ ነበር።

ከትናንት በስቲያ የብሪታንያ አዲሷን ጠቅላይ ሚንስትር ሊዝ ትሩስን ሹመት ያጸደቁት ንግስቲቱ ዛሬ ከሰዓት መጠነኛ ህመም ከተሰማቸው በኋላ ምሽት ላይ ህይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል።

በመላው ብሪታንያ ሀዘን ላይ የወደቁ ሲሆን የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላም ዝቅ ብሎ ከመውለብለቡ ባለፈ የብሪታንያ ብዙሀን መገናኛዎች ሌሎች ጉዳዮችን መዘገብ አቁመዋል።

Politics

ሀገራቱ ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ ላይ በጣሉት ማእቀብ ምክንያት ነው

የሩሲያ ጉዝፉ የነዳጅ ኩባንያ ጋዝፕሮም ቻይና የጋዝ ግብይትን ከዶላር ይልቅ በሩብል እና በዩዋን እንድተክፍለው የሚያስችል ስምምነት መፈራረሙን አስታወቀ።

የጋዝፕሮም ዋና ስራ አስፋጻ አሌክሲ ሚለር፤ ቻይና እና ሩሲያ የተፈራረሙት አዲሱ የክፍያ ስርዓት ሁለቱንም ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ እና አስተማማኝ ነው ሲሉ ተስምተዋል።

ከቻይና ጋር የተደረሰው አዲሱ ስምምነት ሂሳብ ለመስራት ቀላል እንደሆነ እና ለሌሎችም ምሳሌ እንደሚሆን ሚለር አክለው አስታውቀዋል።

ሁለቱም ሀገራት በዶላር መገበያየትን አቁመው መቼ በራሳቸው ገንዘብ መገበያየት ይጀምራሉ ለሚለው ግን ጋዝፕሮም ዝርዝር ከመስጠት ተቆጥቧል።

ሁለቱ ሀገራት መገበያያቸውን ከዶላር ወደ ራሳቸው የመቀየር ሂደት ሩሲያ ዶላር እና ዮሮን ጨምሮ በምእራባውያን ከሚዘወሩ መገበያያዎች ላይ ካላት ጥገኝነት የማላቀቅ አካል እንደሆነ ተነግሯል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በገባቸው ጦርነት ከምዕራባውያን 6 ሺህ ማእቀቦች የተጣሉባት ሲሆን፤ ሩሲያም ይህንን ተከትሎ ከቻይና እና ከምእራባውያን ውጪ ከሆኑ ሀገራት ጋር ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቷን ለማጠናከር እየሰራች ተገኛለች።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በያዝነው የፈረንጆቹ 2022 ላይ የአውሮፓ ደንበኞቻቸው ከሩሲያ ጋዝን መግዛት መቀጠል ከፈለጉ በጋዝፕሮም ባንክ የሩብል የባንክ ሂሳብ እንዲከፍቱ ማሳሰባቸው ይታወሳል።

ይህንን ስምምነት አልቀበል ላሉ የተወሰኑ ኩባንያዎች ሩሲያ ጋዝ ማቅረብ ያቆመች ሲሆን፤ ይህም የጋዝ እና የነዳጅን ጨምሮ የኃይል ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል።

News today, social life

በቻይና በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 ደረሰ

በቻይና ሲቹዋን ግዛት በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል

በቻይና በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 ደርሷል፡፡

ከፈረንጆቹ 2017ወዲህ በቻይና ደቡብ ምእራብ በምትገኘው ሲቹዋን ግዛት በተከሰተው ጠንካራ ነው በተባለው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የነፍስ አድን ሰራተኞች በአስቸካሩ ሆኔታ ውሰት ሉ ሰዎችን ለማውጣት እና መሰረታዊ አገልግቶችን ለለመረስ እየሰሩ መሆናቸውንም ሀገባው ጠቅሷል፡፡

በአደጋው ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው 250 ሰዎች ህክም እየተደረገላቸው ይገኛል፤ ከተጎጅዎች መካል 10 የሚሆኑት ከባድ አደጋ የደረሰባቸው ናቸው ተብሏል፡፡

የነፍስ አድን ሰራተኞች ህይወታቸው ለአደጋ የተጋለጡ 200 ሰዎች ለማውጣት፣ ቴለኬኮሙኒኬሽንን፣ መብራት እና የውሃ አገልግሎቶችን ለመመለስ በመጣደፍ ላይ ናቸው፡፡

ሮይተርስ የቻይና ሚዲያዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው የነፍስ አድን ሰራተኞቹ በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 በሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ለተጎዱ ሰዎች የምግብ አቅርቦት እያደረሱ ነው፡፡

በሲቹያን ግዛት የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እስከ ግዛቷ ተራራ ቦታዎች ድርስ ንዝረቱ መሰማቱን ዘገባው ገልጿል፡፡

Politics

ባይደን፤ ፊንላንድ እና ስዊድን ኔቶን ለመቀላቀል ያቀረቡትን ጥያቄ በፊርማቸው አጸደቁ

ባይደን የአሜሪካ ኮንግረስ ከወር በፊት አሳልፎት የነበረውን የውሳኔ ሃሳብ ነው ያጸደቁት

2022/8/10 6:11 GMT

የሀገራቱን ጥያቄ የደገፉ የኔቶ አባል ሃገራት ቁጥር 23 ደርሷል

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፤ ፊንላንድ እና ስዊድን ኔቶን ለመቀላቀል ያቀረቡትን ጥያቄ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡

ባይደን የአሜሪካ ኮንግረስ ከወር በፊት አሳልፎት የነበረውን የውሳኔ ሃሳብ ነው ያጸደቁት፡፡

የሁለቱ የኖርዲክ ሃገራት ኔቶን መቀላቀል ጥምረቱን የበለጠ እንደሚያጠናክረው ነው ባይደን የተናገሩት፡፡

ፕሬዝዳንቱ ጠንካራ የዲሞክራሲ፣ ወታደራዊ ተቋማት ባለቤት ናቸው ያሏቸውን ፊንላንድን እና ስዊድንን ግልጽና ጠንካራ ምጣኔ ሃብትን ለመገንባትም ችለዋል በሚል አሞግሰዋቸዋል፡፡

የ76 ዓመቱ አዛውንት በቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የስልጣን ዘመን ስለመላላቱ የሚነገርለትን የአሜሪካንና የአጋሮቿን ግንኙነት መልሶ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ቃል በመግባት ነበር ወደ ስልጣን የመጡት፡፡

የአሜሪካ ደህንነት መሰረት ነው ሲሉም ኔቶን አሞካሽተዋል፡፡ ሃገራቸው በአትላንቲክ ቀጣና ለሚኖራት ጥምረት ያላትን ቁርጠኝነትንም ገልጸዋል፡፡

የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር (ኔቶ) አባል ለመሆን የሚጠይቁ አዳዲስ ሃገራት የጥምረቱን አባል ሃገራት ሙሉ ድጋፍ ማግኘት አለባቸው፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት መጀመሯን ተከትሎ የኪቭ እጣ ፋንታ ሊገጥመን ይችላል በሚል ኔቶን ለመቀላቀል የጠየቁት ፊንላንድ እና ስዊድንም ከ30ዎቹ የጥምረቱ አባል ሃገራት የ23ቱን የተረጋገጠ ድጋፍ ማግኘታቸውን ፍራንስ 24 ዘግቧል፡፡

የኔቶን በአትላንቲክ ቀጣና መስፋፋት አጥብቃ ስትቃወም የነበረችው ሩሲያ ፊንላንድ እና ስዊድን ኔቶን መቀላቀላቸው ያን ያህል ስጋት እንዳይደለ ብትገልጽም ከበድ ያለ የአጸፋ ምላሽን ልትሰጥ እንደምትችል ግን ማስጠንቀቋ ይታወሳል፡፡