News today, Politics, social life, Technology

በ11 የአለም ዋንጫዎች ላይ የታደሙት ብራዚላዊ

የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን በአርጀንቲና በ1978 የተመለከቱት ዳኔል ስብሩዚ በኳታርም የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ተከታትለዋል

“የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው ፤ በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዝግጁ ነኝ” ብለዋል

11 የአለም ዋንጫዎችን የተመለከቱት ብራዚላዊ በድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ስማቸውን ማስፈር ችለዋል።

ዳኔል ስብሩዚ የተባሉት የ76 አመት አዛውንት የሳኦሎ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ስብሩዚ በ1978 ወደ አርጀንቲና በማቅናት የመጀመሪያ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ከተመለከቱ ወዲህ አለምን በኳስ ምክንያት ዞረዋል።

የዘንድሮውን የኳታር የአለም ዋንጫ ለመታደምም ዶሃ ገብተው ሰንብተዋል።

የ76 አመቱ አዛውንት በዶሃ 11ኛ የአለም ዋንጫ ጨዋታን ሲመለከቱም የአለም የድንቃድንቅ መዝገብ ክብረወሰን ይዘዋል በሚል የምስክር ወረቀት ሰጥቷቸዋል።

የአለም ዋንጫን መመልከት ከአዳዲስ ባህልና ልምድ ጋር መተዋውቅ ነው የሚሉት ስብሩዚ ፤ የአለም ዋንጫ ከመልከ ብዙ ተሰጥኦ ባለቤቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑን አንስተዋል።

ከአርጀንቲና እስከ ኳታር አለም ዋንጫን ለመመልከት ሲጓዙም የብራዚልን ባህልና ወግ ሲያስተዋውቁ እንደነበር ተናግረዋል።

ባለፉት 44 አመታት በተለያዩ አልባሳት አጊጠው ብራዚልን እየደገፉ የሳኦ ፖሎን ባህል በስፋት ያስተዋወቁት ስፖርት አፍቃሪ፥ የአለም ዋንጫን በስታዲየም ከመመልከት የሚያስቆመኝ ሞት ብቻ ነው እያሉ ነው።

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ በሚያዘጋጁት የ2026 የአለም ዋንጫ ለምታደምም ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በራሳቸው የተያዘውን ክብረወሰን ለማሻሻል ተስፋ አድርገዋል።

News today, Politics, social life, Technology

አርጀንቲና የኳታሩን የአለም ዋንጫ ያነሳችበት ጨዋታ በምስል

አርጀንቲና ለ3ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን አንስታለች

የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን

አርጀንቲና በመለያ ምት 4 ለ 2 ፈረንሳይን አሸንፋለች

በሉሳይል ስታዲየም የተደረገው ልብ አንጠልጣይ ፍልሚያ በአርጀንቲና አሸናፊነት ተደምድሟል።

አርጀንቲና ሶስት ጊዜ መርታ አቻ በሆነችበት ምሽት ሌዮኔል ሜሲ ሁለት ጎሎችን አስቆጥሯል።

ውሃ ሰማያዊ እና ነጭ ለባሾቹ በመጀመሪያው አጋማሽ 2 ለ 0 እየመሩ ቢወጡም ፈረንሳይ በኪሊያን ምባፔ የ80 እና 81ኛ ደቂቃ ሁለት ጎሎች አቻ ሆናለች።

በተጨማሪ 30 ደቂቃውም ሜሲ ሶስተኛውን ጎል ለሀገሩ ቢያስቆጥርም የፈረንሳዩ የ23 አመት ኮከብ ኪሊያን ምባፔ ባስቆጠራት ሶስተኛ ጎል ጨዋታው በመለያ ምት ተጠናቋል። በዚህም አርጀንቲና 4 ለ 2 በሆነ የፍጹም ቅጣት ምት ጎል አሸናፊ ሆናለች።

ሊዮኔል ሜሲ ከ36 አመት በፊት ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ያሳካውን ክብር በደገመበት ምሽት የብራዚላዊውን ፔሌ የጎል አስቆጣሪነት ክብር ማሻሻል ችሏል።

የ35 አመቱ ሜሲ በ26 የአለም ዋንጫ ጨዋታዎች ተሰልፎ 13 ጎሎችን በማስቆጠሩም በብራዚላዊው ፔሌ ተይዞ የቆየውን ክብረወሰን ማሻሻል ችሏል።

አርጀንቲና በዛሬው የሉሳይል ስታዲየም ፍልሚያ ድል ማድረጓን ተከትሎ በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ተሸንፋ (በሳኡዲ አረቢያ) ዋንጫውን በመውሰድ ስፔን በ2010 የያዘችውን ሪከርድ ተጋርታለች።

የላቲን አሜሪካዋ ሀገር ፈረንሳይን በመርታት ሶስተኛ ዋንጫዋን አንስታለች።

አርጀንቲና በ1978 ፣ 1986 እና በኳታር የዓለም ዋንጫን ወስዳለች።

News today, social life

ቁጥሮች የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ስለሆነችው ትንሿ ሀገር ኳታር ምን ይላሉ?

የአለም ዋንጫን የምታዘጋጀው ኳታር ስፋት የለንደን ከተማን አታክልም

ኳታር ዶሃ

ከ3 ሚሊየን ገደማ የሚኖርባ ሲሆን፤ የኳታር ዜጎች ከ300 ሺህ አይበልጡም

ኳታር ከ200 ቢሊየን ዶላር ወጪ ያደረገችበት ግዙፉ የዓለም የእግር ኳስ መድረክ የ2022 የዓለም ዋንጫ አዘጋጅታለች።

ውድ የዓለም ዋንጫን ስላዘጋጀቸው ትንሿ ሀገር ኳታር ቁጥሮች ምን ይላሉ?

ኳታር በፈረንጆቹ 1971 ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነፃ ወጥታለች። የአልታኒ ቤተሰብ ከ1825 ጀምሮ ኳታርን እየመራ ነው።

ኳታር 3 ሚሊየን የሚጠጋ ህዝብ ይኖርባታል። ከአጠቃላይ ነዋሪው ግን የሀገሪቱ ዜጋ ከ300 ሺህ አይበልጥም። ከ100 በላይ ሀገራት ዜጎች ይኖሩባታል።

ከ80 በላይ ሀገራት ያለቪዛ መግባት ይችላሉ፤ ይህም ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት አንደኛ ከአለም 8ኛ ደረጃን እንድትይዝ አድርጓታል።

97 በመቶው የተማረ ህዝብ ያለባት ሲሆን፥ የሴቶች እጥረት ግን በስፋት ይስተዋልባታል፤ ከጠቅላላው ህዝብ 24 ነጥብ 7 በመቶው ብቻ ነው ሴት።

ኳታር ወንጀል ከማይፈፀምባቸው ሀገራትም ከ153 ሀገራት 31ኛ ደረጃን በመያዝ ሰላማዊነቷ ተመስክሮላታል።

በየብስ ከሳኡዲ አረቢያ ጋር ብቻ የምትዋሰነው ሀገር ስፋቷ ለንደንን አያክልም፤ የአሜሪካዋን ኒውዮርክ ከተማም 10 በመቶ ብቻ ነው የምትሸፍነው፤ 160 ኪሎ ሜትር ከሰሜን እስከ ደቡብ 80 ኪሎሜትር ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ትረዝማለች።

አራት ማዕዘኗ ሀገር ደሴት ሳይሆኑ ጠባብ ከሆኑ ሀገራት 11ኛ ደረጃ መያዟንም መረጃዎች ያመላክታሉ። በአሳ ሀብቷ የምትታወቀው ዶሃ የተፈጥሮ ጋዝና የነዳጅ ክምችቷ የእድገት ግስጋሴዋን አፋጥኖታል።

ከሩስያና ኢራን በመቀጠል 3ኛዋ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያለባት ኳታር ለተከታታይ አመታት ፈጣን እድገት አስመዝግባለች።

የሀገሪቱ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ወይም (ጂ ዲ ፒ) 216 ቢሊየን ደርሷል። ከ62 ሺ ዶላር በላይ የደረሰው የነፍስ ወከፍ ገቢም ከአለማችን ባለጠጋ ሀገራት ከፊት አሰልፏታል።

229 ቢሊየን ዶላር ወጪ አድርጋ በ8 ስታዲየሞች ያዘጋጀችውን የአለም ዋንጫ ለማቅረብም ስአታት ቀርተዋል

News today, Technology

የበርካቶችን ቀልብ የሳበው የቻይና “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

“J-20” ተዋጊ ጄት ዡሃይ የቻይና የአየር ትርኢት ላይ ለእይታ ቀርበዋል

“J-20” ስውር ተዋጊ ጄት

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

የ2022 የቻይና የአየር ትርኢት በደቡባዊ የሀገሪቱ ከተማ ዡሃይ መካሄድ ላይ ሲሆን፤ “J-20” ስውር ተዋጊ ጄት ለእይታ ቀርቧል።

የቻይና ሕዝብ ነፃ አውጪ ጦር ተብሎ የሚጠራው የቻይና ጦር የታጠቀው “J-20” ስውር ተዋጊ ጄቶች ዙሃይ ሰማይ ላይ መታየታቸው ለቻይና ኤር ሾው የበለጠ ድምቀትን ጨምሯል።

ለቻይና ኤር ሾው ላይ የቻይና አየር ሃይል ተዋጊዎች እና “የአየር ኤሮባቲክስ” ቡድን በዙሃይ ታላቅ የአየር ትርኢት ቢያቀርቡም አራት ጄ-20 ስውር ተዋጊዎች የተመልካችን አይን ስበዋ ነው የተባለው።

የቻይና “J-20” ተዋጊ ጄቶችን ምን የተለየ ያደርጋቸዋል…?

“J-20” ተዋጊ ጄቶች የመጀመሪያዎቹ ስሪቶች በሩሲያ የተመረቱ ሞተሮችን ይጠቀሙ የነበረ ሲሆን፤ በኋላ ላይ ግን ቻይና በራሷ ባመረተችው መንትያ ሞተር እንደተካች ይነገራል።

በችንግዱ ኤርክራፍት ግሩፕ የሚመረተው “J-20” ተዋጊ ጄት የመጀመሪያ በረራውን በፈረንጆቹ 2011 ያካሄደ ሲሆን፤ በ2017 በስራ ላይ እንደዋለም ተነግሯል።

በሰዓት እስከ 2 ሺህ 100 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር ይችላል የተባለለት “J-20” ተዋጊ ጄት፤ 19 ሺህ 390 ኪሎ ግራም ክብደት አለው ተብሏል።

 “J-20” ተዋጊ ጄት ቻይና የዓለማችን ቀዳሚ ስውር ተዋጊ ጄት ተብለው ለሚነገርላቸው የአሜሪካ ኤፍ-22 እና ኤፍ-35 ተዋጊ ጅቶች የሰጠችው ምለሽ መሆኑ ይነገራል።

በአሁኑ ወቅት 200 J-20 ተዋጊ ጄቶች የቻይና ህዝቦች ነጻነት ሰራዊት ተብሎ በሚጠራው የቻይና ጦር አየር ኃይል አገልግሎት እየሰጡ ነው።

የቻይና አየር ክልሏ ለሚጥሱ የማንኛውም ሀገር ተዋጊ ጄቶች ምለሽ የምትሰጠው በእነዚሁ “J-20” ተዋጊ ጄቶች መሆኑ ተገልጿል።

News today, Politics

ጠ/ሚ ዐቢይ “የወሰን ውዝግብ ያለባቸው አካባቢዎች በህግ አግባብና በምክክር ይፈታሉ” አሉ

መንግስት “ሌብነት” ለመዋጋት በሀገራዊ ኮሚቴ ጥናት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ስለ ሰላም ስምምነቱ “ምን እንደሚመጣ ከወዲሁ መናገር አይቻልም” ብለዋል

የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሄር ፕሬዝዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ መስከረም 30፤ 2015 ዓ.ም በሁለቱ ም/ቤቶች መክፈቻ የመንግስትን የትኩረት አቅጣጫ አሳውቀዋል።

በዚህ የመንግስት የትኩረት አቅጣጫና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ለመስጠት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ከሀገሪቱ ጠቅላላ ምጣኔ-ሀብት እስከ ፖለቲካ ባህል፤ ከሰላም ስምምነቱ እስከ ደህንነት ስጋቶች ድረስ ከም/ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች መልስና ማብራሪያ ሰጠተዋል።

የሁለት ዓመታትን ጦርነት ይገታል ተብሎ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ስለተደረሰው ሰላም ስምምነትና ስጋት ጥያቄ የተነሰላቸው ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ “ሰላምና ብልጽግናን ለማስቀጠል ሲባል ጦርነትን ማስቆም የግድ ብሏል” ብለዋል።

የኢትዮጵያን ህልውናና አንድነት የሚገዳደር ሲፈጠር ግን “መፋለም” የግድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፤ አሉ ያሏቸውን ሰላም የሚያስከፋቸው ኃይሎችን አሳስበዋል።

ስለ ስምምነቱ ውጤት ሲናገሩም “ምን እንደሚመጣ ከወዲሁ መናገር አይቻልም” ብለዋል። “ሌላውን ተወያይተን ፈር እናስይዘዋለን” በማለትም የስምምነቱ ቀጣይ ድርድሮችና ውይይቶች እንደሚኖሩ ጠቁመዋል።

የምክር ቤቱ አባላት የሚያወዛግቡ አካባቢዎች በፕሪቶሪያው ስምምነት “በህገ-መንግስቱ ምላሽ ይሰጣቸዋል” መባሉ ላይ ጥያቄ አንስተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከወልቃይትና ራያ ጀርባ “ሽረባ” አለ ያሉ ሲሆን፤ ለዚህም የመንግስታቸው እጅ እንደሌለበት ተናግረዋል።

በተለይም የወልቃይት ጉዳይ ላይ አተኩረው ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ፤ ወልቃይት “የሁለት ህዝቦች ድልድይ ነው” መሆኑን አስምረዋል።

ወዝግቡ በህግ አግባብና በምክክር የሚፈታ ነው ብለዋል። ለወልቃይት “ዲሞክራሲያዊ እድል” መሰጠት አለበት ሲሉም ውዝግቡ በስምምነት እልባት እንደሚያገኝ ጠቁመዋል።

በአጠቃላይ መንግስታቸው ከስምምነቱ ማግስት ሶስት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን ያሳወቁት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ እርዳታ ማቅረብ፣ የወደሙ መሰረተ-ልማቶችን መገንባት እና ተፈናቃዮች መመለስ ላይ መጠመዱን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ስለ ሀገሪቱ ሰላምና ደህንነት ሲያብራሩ በተለይም ሸኔ ስለተባለው ታጣቂ ቡድን “ፍላጎቱ አይታወቅም” ብለዋል።

መንግስት “ለሰላም ሁሌም በሩ ክፍት ነው” ብለዋል። ህገ-መንግስቱን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገገር በመንግስት በኩል አቋም እንዳለም ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚንስትሩ በታጣቂው ላይ እየተወሰደ ስላለ እርምጃ ዝርዝር ማብራሪያ ባይሰጡም “ውጤቱ በተጠበቀው ልክ አመርቂ ባይሆንም ስራዎች እየተሰሩ ነው” ሲሉ እየተወሰደ ስላለ ወታደራዊ እርምጃ ፍንጭ ሰጥተዋል።

ህገ-መንግስታዊ መብት ስለሆነው ተንቀሳቅሶ የመስራት መብትም ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ ተነስቷል።

ህገ-መንግስታዊ መብት ስለመሆኑ ያልሸሸጉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ሆኖም ለሀገር ሰላም ሲባል መጉላላት እንደ ትልቅ ነገር መታየት እንደሌለበት ገልጸዋል።

ይልቁንም መንገደኞች ለፍተሻ እንዲተባበሩ ጠቁመዋል። “ወጣቶች ብር ተከፍሏቸው አዲስ አበባን ለማሸብት ይሞክራሉ” ያሉም ሲሆን፤ በዚህም የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች እየተያዙ ነው ብለዋል።

ስለ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል አስተያየታቸውን የሰነዘሩም ሲሆን፤ “የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል ችግር አለበት” ሲሉም ብቃት መመዘኛ እንዳልሆነ ተናግረዋል።። “ሰፈር ነው የሚታየው” በማለትም “ብሄር” በፖለቲካው መንገሱን ጠቁመዋል። ይህም ባህል እየሆነ ሲሄድ አደገኛ ነው በማለት “በስራ ሳይሆን በጩኸት ለውጥ ይመጣል ብለው የሚፈልጉ ሰዎች የሚያመጡት ነው” ሲሉ አሳስበዋል።

“የሽግግር መንግስት እያሉ የሚጮሁ አሉ፤ ስትጮሁ ትኖራላችውሁ፤ የኢትዮጵያን ክንፍ ነው የምትቆርጡት፤ ጥንቃቄ እናድርግ” ብለዋል።

ስለ ሙስና በሀገሪቱ መንግስት ያነሱት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ “ችግርን እንደ እድል የወሰዱ ሰዎች ቀይ መስመርን ቀይ ምንጣፍ አድርገዋል” በማለት ሌብነት በመንግስት መዋቅር ስር መስደዱን ለምክር ቤቱ አባላት ተናግረዋል።

 ሌብነት ከልምምድ እንደ መብት እየተወሰደ በመሆኑ መንግስት ተወያይቶ ሀገራዊ ኮሚቴ በማቋቋም ጥናት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

“ክሱ ብዙ ነው፤ እጅ የማይጠቆምበት ሰው የለም” በማለትም ህዝቡ ማስረጃ እንዲያቀርብ ጠይቀዋል።

News today, Politics

ኢትዮጵያ ተመድ ሩስያ ለዩክሬን ካሳ እንድትከፍል ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በመቃወም ድምጽ ሰጠች

የውሳኔ ሃሳቡን ኢትዮጵያን ጨምሮ 14 ሀገራት የተቃወሙት ሲሆን 73 ሀገራት ደግሞ ድምፅ ከመስጠት ታቅበዋል

ይህም ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ሀገራት ያልደገፉት የውሳኔ ሀሳብ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጎታል

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ትናንት ማምሻውን በሩስያ ላይ ያቀረበው አዲስ የውሳኔ ሃሳብ ተቃውሞ ገጥሞታል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ 14 ሀገራት ሩስያ በዩክሬኑ ጦርነት ላደረሰችው ጉዳት ካሳ እንድትከፍል የሚያስገድደውን የውሳኔ ሀሳብ ተቃውመውታል።

አረብ ኤሚሬትስን ጨምሮ 73 ሀገራት በድምፀ ተአቅቦ ማለፋቸውን ተከትሎም የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የመንግስታቱ ድርጅት ካወጣቸው አምስት የውሳኔ ሀሳቦች ሁሉ ይሁንታ የተነፈገው ሆኖ ተመዝግቧል።

የውሳኔ ሀሳቡ በጦርነቱ ለተገደሉና ለቆሰሉ ዩክሬናውያን ሞስኮ ካሳ እንድትከፍል የሚጠይቅ ነው።

በጦርነቱ የጠፋውን የሰው ህይወትና የደረሰውን የንብረት ውድመት የሚያጣራ አለም አቀፍ ቡድን እንዲዋቀርም ተመላክቷል በዚሁ የውሳኔ ሀሳብ።

ዩክሬን – “የውሳኔ ሃሳቡ ፍትህ ለማስፈን ትልቅ ተስፋ ነው”

በመንግስታቱ ድርጅት የዩክሬን አምባሳደር ሰርጌ ኪይልይስታይ፥ ሩስያ ዩክሬንን ለማፈራረስ የመጨረሻ አቅሟን ተጠቅማለች ብለዋል።

“ከመኖሪያ ህንፃዎች እስከ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች ያላፈራረሰችው የህዝብ ተቋም የለም፤ ባለፈው ወር ብቻ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ጥቃት አድርሳ ግማሽ ዩክሬን በጨለማ ተውጧል” ነው ያሉት አምባሳደሩ።

የሩስያ ወታደሮች ይዘዋተው በቆዩ የዩክሬን ከተሞች የፈፀሟቸውን ወንጀሎችም በማንሳት ሞስኮ ተጠያቂ እንድትሆን የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ አድንቀዋል።

ዩክሬንን መልሶ የመገንባቱ ስራ ሲካሄድ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን የመካስ እና ፍትህን የማስፈኑ ጉዳይም እኩል ሊካሄድ እንደሚገባም አብራርተዋል።

ኬቭ በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት ሳትጨምር ሳትቀንስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ ለማድረግ መዘጋጀቷንም በመጥቀስ የውሳኔ ሃሳቡን ፍትህን ለማስፈን የተስፋ ብርሃን ነው ብለውታል።

ሩስያ – “የውሳኔ ሀሳቡ ህጋዊ ያልሆነና ተፈፃሚነት የሌለው ነው”

በመንግስታቱ ድርጅት ሩስያን የወከሉት ቫስሊ ንቤንዚያ በበኩላቸው፥ የውሳኔ ሀሳቡ በአለም አቀፉ ህግ ተቀባይነት የሌለውን ነገር ህጋዊ ለማስመሰል የሞከረና ተፈፃሚነት የሌለው ነገር ነው በሚል ተቃውመውታል።

ምዕራባውያን እንዳይንቀሳቀስ ያገዱትን በቢሊየን ዶላር የሚቆጠር የሩስያ ሃብት ለመዝረፍ የተቀነባበረ ነው፤ የመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤም ይህን ዘረፋ እንዲሸፍንላቸው የውሳኔ ሃሳቡን አቀርበዋል ሲሉም ሀገራት እንዲቃወሙት ጠይቀዋል።

የውሳኔ ሀሳቡን ማፅደቅ የምዕራባውያን የጦር መሳሪያ አምራቾችን ከመጥቀምና አለምን የባሰ ውጥረት ውስጥ ከመክተት ውጭ ፋይዳ እንደሌለውም አስገንዝበዋል።

ቻይና፣ ኢራን፣ አንጎላ፣ ቬንዙዌላን ጨምሮ 16 ሀገራት ለሩስያ ድጋፋቸውን በፊርማ ገልፀው፥ ፍትህ በተገቢው የህግ ስርአት እንጂ ምንም አይነት የህግ መሰረት በሌለው የውሳኔ ሃሳብ አይደለም ብለዋል።

በፀጥታው ምክር ቤት ድምፅን በድምፅ የመሻር ስልጣን ያላት ሩስያ የሚቀርቡባትን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አድርጋለች።

በጠቅላላ ጉባኤው ግን ይሄው ድምፅን በድምፅ የመሻር ስልጣን የላትም፤ ይሁን እንጂ የጠቅላላ ጉባኤው የውሳኔ ሃሳብ እንደ ፀጥታው ምክርቤት ህጋዊ አስገዳጅነት የለውም።

በካናዳ፣ ጓቲማሚላ፣ ኔዘርላንድና ዩክሬን አነሳሽነት የቀረበው የትናንቱ ሩስያ የጦር ካሳ ትክፈል የውሳኔ ሀሳብ በ94 ሀገራት ድጋፍ ቢፀድቅም በሞስኮ ላይ ህጋዊ ጫና አያመጣም።

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮልድሚር ዜለንስኪ ባስተላለፉት የቪዲዬ መልዕክት ግን ሩስያ ላደረሰችው ኪሳራ ሁሉ ካሳ መክፈሏ ከይቀሬ ነው ብለዋል።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በበኩላቸው፥ እንዳይንቀሳቀስ ያገዱትን የሩስያ ሃብት በካሳ ስም ለዩክሬን ለመስጠት ላሰቡት ምዕራባውያን የትኛውንም ምላሽ እንሰጣለን ሲሉ ዝተዋል።

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ቻይና ለጋራ ጥቅም ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ፈቃደኛ ነች አሉ

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ የሁለቱም ኃያላን ሀገራት ግንኙነት ጥሩ የሚባል እንዳልሆነ ይታወቃል

የጆ ባይደን አስተዳደር ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ያሏት የግንኙነት መስመሮችን ክፍት እንደሚያደረግ አስታውቋል

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ቻይና ለጋራ ጥቅም ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ፍቃደኛ ናት ማለታቸው የቻይና መንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በትናንትናው እለት በተዘጋጀውና በአሜሪካ – ቻይና ግንኙነት ዙሪያ ትኩረት የሚያደረገው የጋራ ብሔራዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት ከሆነ ሁለቱም ኃያላን ሀገራት ግንኙነታቸውንና ትብብር በማጠናከር ለዓለምና መረጋጋት ትልቅ ሚና መጫወት አለባቸው ብለዋል፡፡

ዢ ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በቅርቡ በኢንዶኔዥያ በሚካሄደው ቡድን-20 ስብሰባ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሊያደርጉት ከሚችሉት ውይይት በፊት መሆኑ ነው፡፡

ጆ ባይደን በበኩላቸው “አሜሪካ ከቻይና ጋር ግጭ አትፈልግም” ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዝዳንት ዢ ለሶስተኛ ጊዜ የቻይና መሪ ሆነው መመረጣቸውን ተከትሎ ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ያሏት የግንኙነት መስመሮችን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተውም ተናግራል ፕሬዝዳንቱ።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ የሁለቱም ሀገራት ግንኙነት ጥሩ የሚባል እንዳልሆነና በበርካታ ዛቻዎች የታጀበ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በተለይም በፔሎሲ ጉብኝት ምክንያት የተበሳጨችው ቻይና እና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብርን ጨምሮ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያም ንግግርና ውይይት የነበራት ቢሆንም ሁሉንም ማቋረጧ የሚታወስ ነው፡፡ 

ከዚህ ባለፈም የፕሬዝዳንት ዢ ሺን ፒንግ አስተዳደር፤ ሀገሪቱ ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን የማጓጓዝ፣ አደገኛ ዕጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን ማቋረጡን ገልጾ ነበር፡፡

አሜሪካ በበኩሏ የቻይና ድርጊት ተገቢ እንዳለሆነ ስትሞግት ቆይታለች፡፡

ያም ሆኖ የሁለቱም ኃያላን ሀገራት መሪዎች አሁን ላይ አዲስ ተረክ ይዘው መምጣታቸው የሀገራቱ ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሷል ተብሏል፡፡

በተለይም ሀገራቱም ሀገራት ከተባበሩ ለዓለም ሰላም የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ዋና ኃላፊ ከአሜሪካ-ቻይና ትብብር ውጭ የዓለም አቀፍ ቁልፍ ጉዳዮችን ለመፍታት የሚደረግ ‘ምንም መንገድ የለም’ ብለው እንደሚያምኑ በቅርቡ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

News today, Politics, social life

የሩሲያን ጦር ምልክት በተሸከርካሪው ላይ የቀረጸው ጀርመናዊ በ4 ሺህ ዩሮ ተቀጣ

የሀምቡርግ ከተማ ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ የሩሲያን ጦር ደግፏል በሚል የገንዘብ ቅጣት ተጥሎበታል

የሩሲያ ጦር በዩክሬን ለልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ከገባ ስምንት ወር ሆኖታል

የሩሲያን ጦር ምልክት በተሸከርካሪው ላይ የቀረጸው ጀርመናዊ በ4 ሺህ ዩሮ ተቀጣ።

የጀርመኗ ሀምቡርግ ከተማ ነዋሪ የሆነ አንድ ግለሰብ የግሉ ተሸከርካሪ ላይ በነጭ ቀለም የሩሲያ ጦር ምልክት የሆነውን የዜድ (“Z”) አርማ ቀርጿል ተብሏል።

ግለሰቡ ከስምንት ወራት በፊት ለልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ግዛት የገባውን የሩሲያ ጦር ደግፏል በሚል በሀምቡርግ ከተማ ፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶበታል።

ይህ ግለሰቡ ባሳለፍነው መጋቢት ወር ላይ በነጭ ወረቀት ላይ የዜድ ምልክትን በደማቁ በመጻፍ በአደባባዮች ሲያሽከረክር እንደነበርም ተገልጿል።

የግለሰቡ ተደጋጋሚ ድርጊት ሩሲያ በዩክሬን እየፈጸመች ያለውን ጦርነት ለመደገፍ ያደረገው ጥረት ነው ያለው የሀምቡርግ አቃቢ ህግ ለማስተማሪያነት በሚል ግለሰቡ 4 ሺህ ዮሮ እንዲከፍል ቅጣት እንደተጣለበት የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።

ሩሲያ በዩክሬን እያደረገች ላለው ጦርነት የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት ወይም ድጋፍ ለማግኘት በሚል የጦር ተሸከርካሪዎቿ የዜድ ምስልን ተጠቅመው እንዲንቀሳቀሱ አድርጋለች።

በሞስኮ እና በተወሰኑ ሀገራት የዜድ ምስል የተጻፈባቸው ምልክቶች በአደባባዮች ላይ መታየት ጀምረውም የነበረ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይም ለተወሰኑ ቀናት በስፋት ተሰራጭተዋል።

ጀርመን የትኛውም ዜጋዋ የሩሲያ ጦር ምልክት የሆነው ይህ የዜድ ምስልን በአደባባይ ይዞ መገኘት አልያም ማሰራጨት ዓለም አቀፍ ወረራን መደገፍ ስለሚሆን ድርጊቱን ከልክላለች።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ስምነተኛ ወሩ ላይ የሚገኝ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ሲሰደዱ በቢሊዮን የሚቆጠር መሰረተ ልማት ደግሞ መውደሙን የተመድ ሪፖርት ያስረዳል።

News today, Politics

ፑቲን ለ3ኛ ጊዜ መሪ ሆነው ለተመረጡት ፕሬዝዳንት ዢ የእንኳን ደስ አልዎት መልእክት አስተላለፉ

ፑቲን፤ በቀጣይ የዢ የስልጣን ዘመን ሞስኮ-ቤጂንግ ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋ አለኝ ብለዋል

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ፑቲን እና የቻይናው አቻቸው ዢ መልካም የሚባል ግንኙነት ያላቸው መሪዎች ናቸው

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላደሚር ፑቲን ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን መሪ ሆነው ለተመረጡት የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ የእንኳን ደስ አልዎት መልእክት አስተላለፉ፡፡

ፑቲን በቀጣይ የዢ ጂንፒንግ የስልጣን ዘመን ሞስኮ-ቤጂንግ ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸው ተስፋም ገልጸዋል፡፡

 “በሀገራቱ መካከል ያለውን… ስትራቴጂያዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመ ገንቢ ውይይታችንን እና የቅርብ የጋራ ስራችንን ለመቀጠል ደስተኛ ነኝ” ማለታቸውንም ነው በክሬምሊን በኩል የወጣው መግለጫ የሚያመለክተው፡፡

የሩሲያው ፕሬዝዳንት አክለው፤ ለ ዢ “ብልጽግና እና አዲስ ስኬቶች” እንደሚመኙ ተናግረዋል::

ሞስኮ እና ቤጂንግ በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ባለቸው ግንኙነት የቅርብ አጋሮች ሆነው ብቅ ያሉበት አጋጣሚ ተፈጥረዋል።

በሀገራቱ መሪዎች መካከል ያለው ግንኙነትም እንዲሁ መልካም የሚባል እንደሆነ ይነገራል፡፡

መሪዎቹ በቅርቡ በኡዝቤኪስታን መዲና ሳማርካንድ ተገናኝተው በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጎልበት እንደሚሰሩ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

ቭላድሚር ፑቲን እና ዢ ጂንፒንግ “ዓለምን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረገው ሙከራ” አንቀበልም የሚል የጋራ አቋም ያላቸው መሪዎች መሆናቸው ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል ቻይና ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የመነጠል አደጋ ለተጋረጠባት ሩሲያ ያላትን ድጋፍ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ስታንጸባርቅ ይስተዋልል፡፡

 ቻይና በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ አብዛኛው ጊዜ የመሃል አቋም ስታራምድና በሞስኮ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ስትቃወም ነው የምትታየው፡፡

ይህም አሜሪካን ጨምሮ በምዕራባውያን ዘንዳ ባይወደድም፤ ፑቲን የቻይናው መሪ ዢ በዩክሬን ጉዳይ የሚያንጸባርቁት “ሚዛናዊ አቋም” እንደሚያደንቁ በቅርቡ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም ሀገራቱ ለዓለም ተምሳሌት የሆነ ገደብ የለሽ ትብብር ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም፡፡

እናም የአሁኑ የፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ለሶስተኛ የስልጣን ዘመን መሪ ሆኖ መመረጥ በሞስኮ-ቤጂንግ መካካል ያለውን ጥሩ የሚባል ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደርሷል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

News today, Politics

ታይዋን፤ ቻይና “አሮጌ አስተሳሰብን ማስወገድ አለባ” አለች

ታይዋን ልዩነቶችን በሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና በተጨባጭ መንገድ እንዲፈቱ ጠይቃለች

ቻይና “የታይዋን ነጻነትን” ለመቃወም የሚያሽችል ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አድርጋለች

ታይዋን፤ ቻይና “አሮጌ አስተሳሰብን ማስወገድ አለባ” አለች፡፡

ታይፔ ይህን ያለችው ጉበኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የታይዋን ነጻነትን በተመለከተ ያለውን ተቃውሞ በህገ መንግስቱ ላይ ካረጋገጠ በኋላ ነው፡፡

የታይዋን የድንበር ተሸጋሪ ፖሊሲዎች አስፈጻሚ አካል የሆነው የመይንላንድ ጉዳዮች ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ “የቻይና ኮሚኒስት መንግስት አዲሱ አመራር የወረራ እና የመጋጨት አስተሳሰቡን አስወግዶ ልዩነቶችን በሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና በተጨባጭ መንገድ እንዲፈቱ እንጠይቃለን” ብሏል፡፡

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ በህገ-መንግስቱ ላይ “የታይዋን ነጻነትን” ለመቃወም የሚያሽችለው ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አድርጓል፡፡

ማሻሻያው ቅዳሜ ዕለት በፓርቲው ብሔራዊ ኮንግረስ ላይ ከ 2ሺህ በላይ ተወካዮች ያሳለፉት ውሳኔ አካል ነው መባሉን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

ለአንድ ሳምንት የቆየው ይህ የኮሙኒስት ፓርቲ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግን ፓርቲውን በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በሊቀመንበርነት እንዲመሩ በመምረጥ በትናንትናው እለት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ከዚህ በተጨማሪም ቻይናን ከፈረንጆቹ 2012 ዓመት ጀምሮ በሬዝዳንትነት እየመሩ ላሉት ዢ ጂንፒንግን ተጨማሪ ስልጣንም እንደሰጠም ሽንዋ ዘግቧል።

ፕሬዝዳንቱ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ቻይናን ሲመሩ ከኮሙንስት ፓርቲ ጽንሰ ሀሳብ ባለፈ ለቻይናዊያን ይበጃል የሚሉትን ሀሳብ ወደ ተግባር መቀየር እንዲችሉ ፈቃድም ሰጥቷል።

ፓርቲው 25 አባላት ያሉት የፖሊት ቢሮ እና አዲስ ሰባት የማዕከላዊ አባላት የተመረጡ ሰዎችን ያሳወቁ ሲሆን በፖሊት ቢሮ አንድም ሴት አለማካተታቸው አነጋገሪ ሆነዋል፡፡

ቻይና ሴት የፖሊት ቢሮ አባል የሌለው ካቢኔ ስታዋቅር በ25 ዓመታት መጀመሪያው ነው ተብሎለታል፡፡

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግን በፓርቲው ጉባኤ መዝጊያ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር ለቻይና ድል እንደሚዋጉ እና እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በኮሮና ቫይረስ ፣ በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እየተፈተነ ያለውን ኢኮኖሚ ማስታግስ እንዲሁም የታይዋን ጉዳይ ለፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ ዋነኛ ትኩረት የሚሰጡባቸው ጉዳዮች ናቸው።

News today, Politics, Technology

ኢራን የጸጥታው ም/ቤት ውሳኔን በመጣስ ለኢትዮጵያ ድሮን መሸጣን አሜሪካ አስታወቀች

ኢራን ሰው አልባ የጦር አውሮፕላን (ድሮን) ለኢትዮጵያ የሸጠችው ከአንድ ዓመት በፊት ነው ተብሏል

ኢራን “ሞሃጀር” የተሰኘውን ድሮን ለኢትዮጵያ መስጠቷን አሜሪካ ገልጻለች

ኢራን የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔን በመጣስ ለኢትዮጵያ ድሮን መሸጧን አሜሪካ አስታወቀች።

የአሜሪካ መንግስት እንዳሳወቀው ኢራን ከአንድ ዓመት በፊት ክረምት ላይ ለኢትዮጵያ ሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን ማስተላለፏን ገልጿል።

ኢራን በፈረንጆቹ 2015 ላይ የጦር መሳሪያ ግብይት እንዳትፈጽም የሚከለክል ማዕቀብ በመንግስታቱ ድርጅት የተወሰነባት ሲሆን፤ ይሄንን ማዕቀብ በመጣስ ለኢትዮጵያ አስተላልፋለች ተብሏል።

2231 የተሰኘው ይህ የተመድ ውሳኔ በኢራን መጣሱን የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቪዳንት ፓቴል መናገራቸውን ዋቢ አድርጎ ሮይተርስ ዘግቧል።

ይህ የተባበሩት መንግስታት ውሳኔ በ2020 ላይ የሚያበቃ ቢሆንም በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ ማዕቀቡ እንዲራዘም ጠይቀው ነበር።

ይሁንና ይህ ማዕቀብ እንዲነሳ ያልተወሰነ በመሆኑ ኢራን ውሳኔውን በመጣስ ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጥታለች ተብሏል፡።

እንደዘገባው ከሆነ ኢትዮጵያ ከኢራን የተረከበችውን ሞሃጀር የተሰኘውን ይሄንን ድሮን ከህወሃት ጋር በሚደረገው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ላይ እንዳዋለችውም ተገልጿል።

ኢራን ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የጦር መሳሪያ ማዕቀቡን በመተላለፍ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ለጀመረችው ጦርነት ድሮን ለሞስኮ ማስተላለፏንም አሜሪካ አስታውቃለች።

ኢራን በምዕራባዊያን የሚቀርቡባትን ክሶች ውድቅ ያደረገች ቢሆንም ከሩሲያ ጋር የሰው አልባ አውሮፕላን እና ሚሳኤል ግዢ ስምምነት መፈጸሟን አምናለች።

ዩክሬን በበኩሏ ኢራን ሻሂድ፣ጄራን እና ሌሎች ስያሜ ያላቸውን ድሮኖች ለሩሲያ በመሸጥ የዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች እንዲደበደቡ አድርገዋል በሚል ከቴህራን ጋር ያላትን ግንኙነት እንደምታቋርጥ ዝታለች።

News today, Technology

ዩክሬን ከ230 በላይ የኢራን ሰራሽ ድሮኖችን መትታ መጣሏን አስታወቀች

ሩሲያ ድሮኖቹን በመጠቀም የዩክሬን መሰረተ ልማቶች እያወደመች እንደሆነ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ተናግረዋል

ዩክሬን ከኢራን ጋር ያላትን ግንኙነት ለማቋረጥ እያሰበችበት እንደሆነም ተገልጿል

ዩክሬን ከ230 በላይ የኢራን ሰራሽ ድሮኖችን መትታ መጣሏን አስታወቀች።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስምንት ወራት የሞላው ሲሆን የጦርነቱ ሁኔታ በየጊዜው እየተቀያየረ አዳዲስ ክስተቶችን እያስተናገደ ቀጥሏል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ኢራን ሰራሽ የሆኑ ከ233 በላይ ለሩሲያ የተሰጡ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወይም ድሮኖች ተመተው መውደቃቸውን ተናግረዋል፡፡

ሩሲያ እነዚህን ኢራን ሰራሽድሮኖቹን በመጠቀም የዩክሬን መሰረተ ልማቶች እያወደመችበት እንደሆነ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በዛሬው ዕለት ብቻ 10 ድሮኖችን መትተው መጣላቸውን አክለዋል፡፡

ሩሲያ በተለይም የዩክሬን ዋና ዋና መሰረተ ልማቶችን እያወደመች እንደሆነ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ በተለይም ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከጥቅም ውጪ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት የዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች ከሀይል አቅርቦት ውጪ ሆነዋል የተባለ ሲሆን ከተሞቹን መልሶ የሀይል አቅርቦት እንዲያገኙ ከፍተኛ ወጪ እየጠየቁ እንደሆነም ፕሬዝዳንቱ አክለዋል፡፡

ክሪሚያን ከተቀረው የሩሲያ ክፍል ጋር ለማስተሳሰር የሚውለው ድልድይ በዩክሬን ተመቶብኛል ያለችው ሞስኮ በ10 ቀናት ውስጥ ከ190 በላይ የአየር ላይ ጥቃቶችን በዩክሬን ላይ አድርሳለች ተብሏል፡፡

ሩሲያ በአጠቃላይ በ16 የዩክሬን ግዛቶች ላይ የሚሳኤል፣ የድሮን እና ሌሎች ጥቃቶችን ሰንዝራለች የተባለ ሲሆን ኢራን ሰራሽ ድሮኖች ዋነኛ የጥቃቱ መፈጸሚያ እንደሆኑ ዩክሬን አስታውቃለች፡፡

ዩክሬን ከመሰረተ ልማት ውድመት በተጨማሪ 70 ንጹሃን ዜጎቿ እንደተገደሉባት ያስታወቀች ሲሆን ኢራን ለሩሲያ የጦር መሳሪያ ድጋፍ አድርጋለች ስትልም ክስ አቅርባለች፡፡

ኢራን በበኩሏ ለሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላን እንዳልሰጠች ብትገልጽም በትናንትናው ዕለት ሚሳኤል ለመስጠት ከሩሲያ ጋር ስምምነት መፈጸሟን ዓለም አቀፍ ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡ 

News today, Technology

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ከአሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ጋር ሲነጻፀሩ

የአሜሪካን ጨምሮ የ70 ሀገራት ወታደራዊ ተቋማት ለዩክሬን ድጋፍ እያደረጉ ነው

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ከአሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

የሩሲያው “ታይገር” ብረተ እና አሜሪካው “ሀምቪ” ብረተ ለበስ ተሸከርካሪዎች በዩክሬን ጦርነት ላይ እየተፋለሙ ነው

በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ጦርነተ ከተጀም ሰባት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በርካታ ምእራባውያን ሀገራትም ለዩክሬን የመሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው።

የሩሲያ መከላካያ ሚኒሰቴር በቅርቡ፤ የ70 ሀገራት ወታደራዊ ተቋማት ለዩክሬን ድጋፍ እያደረጉ እንደሆ እና ሩሲያ በዩክሬን ምድር ምዕራባውያን ጋር እየተዋጋች እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል።

አሜሪካ ለሩሲያ በተለያየ ጊዜ የተለያየ መጠን ያለው የጦር መሳሪ ለዩክሬን የሰጠች ሲሆን፤ ከእነዚህም ውወስጥ “ሀምቪ” የተባለው ብረት ለበስ የጦር ተሽከርካሪ አንዱ ነው።

ሩሲያም በዩክሬን ካሰለፈቻቸው የጦር ተሸከርካሪዎች ውስጥ “ታይገር” ብረተ ለበስ ተሸከርካሪ ይገኛል የተባለ ሲሆን፤ በጦርነቱ ላይም የሩሲያው “ታይገር” የአሜሪካውን ሀመቪ ሲያሳድድ እንደታየ ዩሩሲያ መገናኛ ብዙሃ ምንጮች ገልጸዋል።

የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ እና አሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪዎች አቅም እና ጥንካሬ ምን ይመስላል?

የሩሲያ የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

“ታይገር ኤም “ አርዛማስክ በተባለ የጦር ተሸከርካሪ አምራች ኩብንያ ነው የተመረተው

በውጊያ ወቅት ወታደሮችን ለማጓጓዘ እንዲሁም መሳሪያዎችን ለማቀበል ይውላል

ፍጥነት፤ በሰዓት ከ125 እስከ 140 ኪሎ ሜትር ድረስ ይጓዛል

በጨለማ ውስጥ ያለምንም ችግር እንዲጓዝ የሚያችል የእይታ መሳሪያ ተገጥሞለታል

ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ አካል እና መስታወት ተገጥሞለታል

የሚታጠቃቸው መሳሪያዎችም

“2A72” አውቶማቲክ ጠመንጃ ከ30 ሚሊ ሜትር ካሊበር ጋር

“AGS-30” አውቶማቲክ የእጅ ቦምብ እና የጭስ ቦምብ ማስወንጨፊያ

ኮርኔት-ዲ ፀረ-ታንክ ሚሳይል ስርዓት እና ተንቀሳቃሽ የአየር ክልል መከላከያዎችን ይገኙበታል

አሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ

“ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ በውጊያ ወቅት ወታደሮችን ለማጓጓዘ እንዲሁም መሳሪያዎችን ለማቀበል ይውላል

ፍጥነት፤ በሰዓት ከ105 እስከ 113 ኪሎ ሜትር ድረስ ይጓዛል

ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ አካል እና መስታወት ተገጥሞለታል

በተጨማሪም ከጎን እና ከኋላ ሙሉ በሙሉ የጥይት መከላከያ ተለጥፎለታል

የሚታጠቃቸው መሳሪያዎችም

• M2፣ M240፣ እና M249 ካሊበር መሳሪያ

• 25 ሚሊ ሜትር ፀረ አውሮፕላን መሳሪያ

• Mk-19 ቦምብ እና የጭስ ቦምብ ማስወንጨፊያ ከ40 ሚሊ ሜትር ካበር ጋር

• ፀረ ታንክ እና AIM-120 ሚሳዔል ማስወንጨፊያዎች እንዲሁም 105 ሚሜ መድፍ ይገኙበታል

News today, Politics

ቦሪስ ጆንሰን ዳግም ለብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትርነት እንደሚወዳደሩ ተገለጸ

ቦሪስ ጆንሰንን ተክተው ጠቅላይ ሚንስትር ሊዝ ትሩስ ስልጣን ለመልቀቅ መወሰናቸው ይታወሳል

ሪሺ ሱናክ፣ ሞርዳንት እና ቤን ዋላስ የቦሪስ ጆንሰን ዋነኛ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል

የብሪታንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ዳግም ለጠቅላይ ሚንስትርነት እንደሚወዳደሩ ተገለጸ።

የቀድሞው ጋዜጠኛ እና የለንደን ከንቲባ የነበሩት ቦሪስ ጆንሰን ቴሬዛ ሜይን በመተካት ብሪታንያን ከፈረንጆቹ 2019 እስከ አሳለፍነው ነሀሴ ወር ጠቅላይ ሚንስትር ነበሩ።

የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የወጣውን ህግ ተላልፈዋል፣ ይዋሻሉ እና ሌሎች ያልተገቡ ባህሪያት አሏቸው በሚል የሀገሪቱ ምክር ቤት አባላት ጫና አሳድረውባቸው ስልጣን ለመልቀቅ ተገደውም ነበር።

ይሄንን ተከትሎም የ50 ዓመቷ ሊዝ ትሩስ ከሌሎች እጩዎች ጋር በመወዳደር እና አብላጫ ድምፅ በማግኘት ከመስከረም ጀምሮ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ።

ይሁንና በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በዋጋ ግሽበት እየተፈተነ ያለውን የብሪታንያ ኢኮኖሚ ለማረጋጋት እርምጃ እንደሚወስዱ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም ስልጣን ከያዙ በኋላ በወሰዷቸው እርምጃዎች የብሪታንያ መገበያያ ገንዘብ ፓውንድ ስተርሊንግ ከዶላር እና ዩሮ አንጻር አቅሙ መዳከሙ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ቀውስ አስከትሏል።

ይሄንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚንስትሯ በደረሰባቸው ጫና ስልጣናቸውን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ እንደምያስረክቡ አስታውቀዋል።

ሊዝ ትሩስ በብሪታንያ መሪ ታሪክ ለአጭር ቀናት ብሪታንያን በመምራት የመጀመሪያዋ የሆኑ ሲሆን እሳቸውን ለመተካት እጩዎች ከወዲሁ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

ከአራት ወር በፊት ስልጣን የለቀቁት ቦሪስ ጆንሰን እንዲመለሱ በርካታ ብሪታንያዊያን በትዊተር ቦሪስ ይመለስ የሚል ዘመቻ ጀምረዋል።

ይሁንና የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር በስልጣን ዘመናቸው አሳይተውታል የተባለው ምርመራ አለመጠናቀቁ በቀላሉ ወደ ቀድሞ ቦታቸው እንዳይመለሱ ሊያደርጋቸው ይችላል ተብሏል።

ከቦሪስ ጆንሰን በመቀጠል የቀድሞው የብሪታንያ ፋይናንስ ሚንስትር እና የሊዝ ትሩስ ተቀናቃኝ የነበሩት ሪሺ ሱናክ እንዲሁም የቀድሞው የብሪታንያ መከላከያ ሚንስትር ቤን ዋላስ እና ሙርዶንት የቦሪስ ዋነኛ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ተገልጿል

News today, Politics

ኢራን ዜጎቿ ዩክሬንን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበች

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ሩሲያ በኢራን ድሮኖች እየደበደበችን ነው ማለታቸው አይዘነጋም

በዩክሬን ጦርነት የኢራን ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቅም ላይ ውለዋል መባሉ ቴህራን ውድቅ አድርጋለች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዩክሬን የሚኖሩ የኢራን ዜጎች ለደህንነታቸው ሲሉ ለቀው እንዲወጡ ጠይቋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ዲፓርትመንት በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ ፤በዩክሬን ውስጥ እየጨመረ የመጣውን የጸጥታ ችግር ግምት ውስጥ በማስገባት ሁሉም የኢራን ዜጎች ወደዚያ ሀገር ከመጓዝ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል፡፡

ዲፓርትመንቱ የኢራን ዜጎች እንዲረጋጉ እንዲሁም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በኪቭ የሚገኘውን የኢራን ኤምባሲ ማነጋገር እንደሚችሉም ጠቁሟል፡፡

ዬክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ባሳለፍነው ሳምንት በሰጡት መግለጫ ፤ሩሲያ የኢራንን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም ጥቃት እያደረሰችብን ነው ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡

በዚህም የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለሩሲያ የጦር መሳሪያ አቅረባለች በሚል ኢራን ላይተጨማሪ ማዕቀብ ሊጥል እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

የዩክሬን ዋና ከተማ ኪቭና ሌሎች ዩክሬን ከተሞች ላይ በተሰነዘርው ጥቃትና በደረሰው ፍንዳታ የኢራን ሻሄድ 136 ድሮች ጥቅም ላይ እንደዋሉ ሮይተርስ ዘግቧል።

በዚህም ሩሲያ የኢራን ድሮኖችን እየተጠቀመች ነው የምትለው ዩክሬን የአውሮፓ ህብረት በቴህራን ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጥል በመወትወት ላይ ናት።

የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲምትሪ ኩሌባ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “የአውሮፓ ህብረት ለሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖች በማቅረብ በኢራን ላይ ማዕቀብ ሊጥል ይገባል” ብለዋል።

በዚህም መሰረት በርካታ የህብረቱ ሚኒስትሮች ኢራን በጦርነቱ ውስጥ ያላትን “ግልጽ” ተሳትፎ በመጥቀስ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርበዋል።

በዛሬው እለት የአውሮፓ ህብረት መሪዎች እያካሄዱት ባለው ስብሰባ በቴህራን ተጨማሪ እርምጃዎችን ለመውሰድ ከስምመነት ሊደርሱ እንደሚችሉ ሮይተርስ ከህብረቱ የውስጥ ሰዎች ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክት ዘግቧል።

በተጨማሪም አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ የኢራን አጥፍቶ ጠፊ አውሮፕላኖች በዩክሬን ጦርነት ጥቅም ላይ ውለዋል መባሉን ተከትሎ የጸጥታው ምክር ቤት ዝግ ስብሰባ ጠርተዋል።

ሩሲያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች መጠቀሟን እንዳይመረምር አስጠንቅቃለች፡፡

 ኢራን በበኩሏ ለዩክሬን ጦርነት የምትጠቀመው ወታደራዊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለሩሲያ አስረክባለች የሚለውን ውንጀላ ውድቅ አድርጋለች፡፡ 

News today, Politics

ሩሲያ የዩክሬኑን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠየቁ

ሩሲያ የዩክሬኑን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠየቁ

ሩሲያ ከሁለት ሺህ በላይ መካናይዝድ ጦሯን ግድቡ ወደሚገኝበት አካባቢ አሰማርታለች

ሩሲያ የዩክሬኑን ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘውን ግዙፍ ግድብ እንዳትመታ ምእራባውያን እንዲያስጠነቅቋት ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠይቀዋል፡፡

ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘው ግድብ ከተመታ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጨማሪ ዜጎች በውሀ ሊጥለቀለቁ እንደሚችሉ ተሰግቷል።

ስምንት ወራት የሞላው የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በየጊዜው አዳዲስ ክስተቶችን ማስተናገዱን ቀጥሏል።

ሩሲያ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ በዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን ጥቃት በማድረስ ላይ እንደሆነች ተገልጿል።

በዚህ የሩሲያ ጥቃትም ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን የሀይል መሰረተ ልማቶች መውደማቸውን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ተናግረዋል።

የሩሲያ ጥቃት መቀጠሉ ያሳሰባቸው የዩክሬን ፕሬዝዳንት ኖቫ ካኮቭካ የተሰኘው ግዙፉ የዩክሬን ግድብ እንዳይመታባቸው ሞስኮን ተማጽነዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ይህ ለደቡብ ዩክሬን ግዛቶች ዋነኛ የሀይል ምንጭ የሆነው ይህ ግዙፍ ግድብ ከተመታ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመቋረጡ ባለፈ በርካታ ዜጎች ሊጥለቀለቁ እንደሚችሉ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።

ሩሲያ በዚህ የዩክሬን ግድብ አካባቢ ከሁለት ሺህ በላይ መካናይዝድ ጦሯን ማስጠጋቷ ግድቡን ልታወድም እንደምትችል ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ምዕራባውያን እና ተመድ ሩሲያ የዩክሬንን ግድብ እንዳትመታ ጫና እንዲያደርጉ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠይቀዋል።ሩሲያ ከአንድ ወር በፊት የዩክሬን ግዛት የሆኑ አራት ግዛቶችን በህዝበ ውሳኔ ወደ ሞስኮ መጠቅለሏ ይታወሳል።

የመንግስታቱ ድርጅት ባሳለፍነው ሳምንት የሩሲያን ህዝበ ውሳኔ የሚቃወም ውሳኔ በአብላጫ መወሰኑም አይዘነጋም።

News today, Technology

“አውዳሚው” የሚባለው ዘመናዊ የአሜሪካ የጦር መርከብ

የዘርፉ ባለሙያዎች “አጓጊ ግን የከሸፈ የመርከብ ጽንሰ-ሀሳብ” ይሉታል

አሜሪካ ካላት ግዙፍ የጦር መሳሪያዎች ውስጥ “ዩ.ኤስ.ኤስ ዙምዋልት” የጦር መርከብ አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

4 ነጥብ 4 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደወጣበት የሚነገረው የጦር መርከቡ በርካታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎቸን የጣጠቀ እንደሆነ ይነገርለታል።

በፈረንጆቹ 2008 ግንባታው የተጀመረው የጦር መርከቡ በ2013 ላይ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ በፈረንጆቹ 2016 ላይ በአሜሪካ ባህር ኃይል ስራ ላይ እንደዋለም መረጃዎች ያመለክታሉ።

አሁን ላይ አሜሪካ ሁለት ዙምዋልት አውዳሚ የጦር መርከቦችን ያላት ሲሆን፤ እነዚህ “ዩ.ኤስ.ኤስ ሞንሶር” እና “ዩ.ኤስ.ኤስ ላይደን ቢ ጆንሰን” የሚል መጠሪያ ያላቸው ናቸው።

አውዳሚ ነው የተባለው የጦር መርከቡ አሜሪካ ካላት ጦር መርከቦች የወጣበት ዋጋ በእጥፍ የሚበልጥ ነው ብለዋል።

የቢላዋ ቅርጽ ያለው የመርከቡ የፊት ክፍል በከባድ የባህር ክፍል ላይ በቀላሉ እንዲጓዝ የሚያስችለው መሆኑንም ድፌንስ ኒውስ በመረጃው አስታውቋል።

መርከቡ 158 የባህር ኃይል አባላትን አሳፍሮ የሚጓዝ ሲሆን፤ 16 ሺ ቶን ገደማ ክብደት በመያዝ በሰዓት እስከ 56 ኪሎ ሜትር መብረር ይችላል ተብሏል።

መርከቡ ባለብዙ ተግባር ራዳሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ከውኃ አካል ላይ ወደ ላይ ሚሳዔል ለማስወንጨፍ የሚያስችሉ 80 ሴሎች እንዳሉትም ተነግሯል።

ሆኖም ግን መርከቡ የፀረ መርከብ፣ የፀረ ባሀር ስርጓጅ ፣ የአየር መከላከያ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፊያ የሌለው መሆኑ እንደክፍተት ይነሳበታል።

የወታደራዊ ጉዳዮች ባለሙያ የሆኑት ሴባስቲያን ሮብሊን፣ የመርከቡ ጽንሰ ሀሳብ እጅግ አጓጊ ነገር ግን የከሸፈ ነው ሲሉ ይገልጹታል።

News today, Technology

“አይበገሬው” የሚል መጠሪያ የተሰጠው “CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር

“CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር ለመንቀሳቀስ ሁለት አብራሪዎች ያስፈልጉታል

የተለያዩ የጦር መሳሪያ የሚተኩሰው ሄሊኮፕተሩ በሰዓት 445 ኪ.ሜ ይበራል

አሜሪካ ካሏት የጦር ሄሊኮፕተሮች ውስጥ “አይበገሬው” የሚል መጠሪያ የተሰጠው “CV-22 ኦስፕሬይ” ሄሊኮፕተር አንዱ ነው።

ቦይንግ እና ሄል ሄሊኮፕተር ቴክስትሮን ኩባንያዎች በጥምረት ያመረቱት ሄሊኮፕተሩ በፈረንጆቹ በ2006 ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰማራ ሲሆን፤ የተለያዩ ተልእኮዎችንም መፈጸም እንደቻለ ይነገርለታል።

ሄሊኮፕተሩ ከተሳተፈባቸው ዉጊያዎች ውስጥም ቀዳሚ እና ግዙፉ አሜሪካ በኢራቅ ያካሄደችው ዘመቻ እንደሆነም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት።

በውጊያ ወቅት የጦር መሳሪያዎችን ለመተኮስ እና ወታደሮችን ለማጓጓዝ የሚውለው ሄሊኮፕተሩ፤ በአንድ ጊዜ ተቀምጠው ከሆነ 24 ወታደሮችን ቆመው ከሆነ ደግሞ 32 ወታደሮችን ጭኖ መጓዝ ይችላል ተብሏል።

CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር ምን የተለየ ያደርገዋል?

ሮልስ ሮይስ አሊሰን AE1107C ሞተር የተገጠመለት ሄሊኮፕተሩ ለመነሳትም ይሁን ለማረፍ መደርደሪያ አያስፈልገውም የተባለ ሲሆን፤ ቀጥ ብሎ ወደላይ የሚነሳ እና ባለበት ተወዳች እየተምዘገዘገ ማረፍ ይችላል።

የረቀቁ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር ዲጂታል ካርታ፣ ዲጂታል ሙሉ በሙሉ ዲጂታል የሆነ የአብራሪዎች ክፍል (ኮክፒት) እንዲሁም ራስን የመከላከል ስርዓቶች ተገጥመውለታል።

ሄሊኮፕተሩ ከባባድ ሮኬቶችን ጨምሮ ኒውክሌርን መቋቋም ይችላል የተባለ ሲሆን፤ “አይበገሬው” የተባለውም ከዚሁ በመነሳት ነው።

ሄሊኮፕተሩን ለማብረር ሁለት አብራሪዎች እና ሁለት የበረራ ኢንጂነሮች (መሃንዲሶች) የግድ ያስፈልጉታል ነው የተባለው።

CV-22 ኦስፕሬይ ሄሊኮፕተር በሰዓት 445 ኪሎ ሜትር የሚበር ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ ነዳጅ ብቻ ከ925 ኪሎ ሜትሮች በላይ መብረር የሚችል ይችላል።

አየር ላይ ነዳጅ ከተሞላለት ደግሞ በየትኛውም የአየር ሁኔታ ውስጥ ከ3300 በላይ ኪሎ ሜትር ያለማቋረጥ መጓዝ እንደሚችል ተነግሯል።

ሄሊኮፕተሩ ላይ ወደላይ መተኮስን የሚያስችላቸው 7.62 ሚሊ ሜትር ሚኒገን ተገጠመለት ሲሆን፤ በመወጣጫው ላይ ደግሞ ካሊበር ማችን ገን ተገጥሞለተል።

News today, social life

የብሪታንያው ፓውንድ በ37 ዓመታት ታሪክ ውስጥ ዝቅተኛ የመግዛት አቅም አስመዘገበ

የአውሮፓ ህብረት መገበያያ ዩሮ በ20 ዓመት ታሪክ ውስጥ ከዶላር በታች ተመንዝሯል

የሩሲያው ሩብል ደግሞ ከሰባት ዓመት በኋላ መነቃቃት አሳይቷል ተብሏል

የብሪታንያው ፓውንድ በ37 ዓመታት ታሪክ ውስጥ ዝቅተኛ የመግዛት አቅም አስመዘገበ፡፡

የአሜሪካ ዶላር፣ የአውሮፓ ህብረት ዩሮ፣ የብሪታንያ ፓውንድ ስተርሊንግ ፣ የቻይናው ዩዋን እና የሩሲያው ሩብል በዓለማችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ ዋነኛ መገበያያ ገንዘቦች ናቸው፡፡

ከእነዚህ መገበያያ ገንዘቦች ጀርባ ሀገራቱ ያሉ ሲሆን የዓለምን ኢኮኖሚ ለመቆጣጠርም የንግድ ፉክክሩ በእነዚሁ ሀገራት መካከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ወደ ጦርነት ካመራች በኋላ የዓለም ንግድ እና ዲፕሎማሲ መዛነፍ ገጥሞታል፡፡

በአሜሪካ አስተባባሪነት በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እና ሩሲያ በማዕቀቡ ላለመጎዳት የወሰደቻቸው የአጸፋ እርምጃዎች በዓለም ምግብ እና ነዳጅ ላይ ተከታታይ የዋጋ ጭማሪ እንዲደረግ አስገድዷል፡፡

በዚህም ምክንያት የአውሮፓ ህብረት ሀገራት መካከል የጋራ መገበያያ የሆነው ዩሮ ከሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በፊት ከዶላር በላይ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ቅናሽ አሳይቷል፡፡

ከጦርነቱ በፊት አንድ ዩሮ ከአሜሪካ ዶላር ጋር ሲነጻጸር የዜሮ ነጥብ 14 ብልጫ የነበረው ሲሆን በአሁኑ ወቅት አንድ ዩሮ ከዶላር ጋር ሲነጻጸር የዜሮ ነጥብ 33 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል፡፡

ይህም ዩሮ ከአሜሪካ ጋር ሲነጻጸር የመግዛት አቅሙ ከ20 ዓመት በኋላ ቅናሽ ማሳየቱ ሲገለጽ ለዩሮ አቅም መዳከም ደግሞ በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ምክንያት በሞስኮ ላይ ማዕቀብ መጣሉን ተከትሎ በአውሮፓ ያጋጠመው የነዳጅ እጥረት እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የብሪታንያ ፓውንድ ስተርሊን ደግሞ በ37 ዓመት ታሪክ ውስጥ የታየ ታሪካዊ የመግዛት አቅም መዳከም እንደሆነ ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡

የብሪታንያ ብሄራዊ ስታስቲክስ ቢሮ እንዳለው ከሆነ አንድ ፓውንድ በ1 ነጥብ 14 ዶላር እየተመነዘረ ሲሆን ይህም ከፈረንጆቹ 1985 ጀምሮ ዝቅተኛው ሆኖ ተመዝግቧል ተብሏል፡፡

ፓውንድ ስተርሊን ከአሜሪካ ዶላር ጋር ሲነጻጸር የ15 በመቶ ብልጫ እንዲሁም ከዩሮ ጋር ደግሞ የ12 በመቶ ብልጫ እንደተወሰደበት በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

የሩሲያው ሩብል ደግሞ ከፈረንጆቹ 2015 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዶላር ጋር ያለውን ልዩነት ያጠበበ ሲሆን ሞስኮ ነዳጇን በሩብል ለመሸጥ መወሰኗ እና ለእስያ ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ መሸጧ ለመገበያያ ገንዘቧ ማገገም ዋነኛ ምክንያቶች እንደሆኑ ተጠቅሷል፡፡

አሁን ላይ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ60 ነጥብ 8 የሩሲያ ሩብል በመመንዘር ላይ የሚገኝ ሲሆን በአውሮፓ አሁንም የነዳጅ እጥረቱ የቀጠለ በመሆኑ የዩሮ እና ፓውንድ ስተርሊንግ አቅም እየቀነሰ ሊሄድ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ 

News today, Politics

ቻይና ጥቃት ከፈጸመች አሜሪካ ታይዋንን እንደምትከላከል ባይደን ተናገሩ

ቻይና “ጥቃት ከፈጸመች” አሜሪካ ታይዋንን እንደምትከላከል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በድጋሚ አስጠነቀቁ።

ፕሬዝዳንቱ ከሲቢኤስ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ የአሜሪካ ኃይሎች ታይዋንን ይከላከላሉ ወይ ተብለው ሲጠየቁ “አዎ” ብለው መልሰዋል።

እሑድ በተሰራጨው ቃለ መጠይቅ የአሜሪካ ፖሊሲ እንዳልተለወጠ ዋይት ሐውስ በድጋሚ እንዲናገር አስገድዶታል።

የዋሽንግተን ፖሊሲ ሁሌም “ስትራቴጂካዊ አሻሚነት” ያለው ሲሆን ታይዋንን ለመከላከል ቃል ባይገባም አማራጩን ደግሞ ሙሉ ለሙሉ አያስቀርም።

ታይዋን በምሥራቅ ቻይና የባሕር ዳርቻ ላይ የምትገኝ ራስ ገዝ ደሴት ስትሆን ቤይጂንግ የግዛቴ አካል ናት ስትል ትገልጻለች።

በጉዳዩ ላይ ዋሽንግተን ቁርጥ ያለ አቋም ሳትይዝ ለረዥም ጊዜ በዲፕሎማሲያዊ ዥዋዥዌ ተጉዛለች። በአንድ በኩል ከቤይጂንግ ጋር ላላት ግንኙነት መሠረት የሆነውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ ታከብራለች።

በዚህ ፖሊሲ ታይዋን የቻይና አካል ስትሆን አቋሙም መገዳደሪያ የለውም። ስለዚህ አሜሪካ ታይዋንን እንደ የተለየ አገር ዕውቅና የማትሰጥ ሲሆን ከደሴቱ ጋር ምንም አይነት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትም የላትም። ነገር ግን የጠበቀ ግንኙነት ፈጥራለች።

አሜሪካ ከግዛቲቱ ጋር ባላት ውል መሰረት ለታይዋን የጦር መሳሪያ ትሸጣለች። ውሉ ደሴቲቱ ራሷን የምትከላከልበትን መንገድ ማቅረብ ያስፈልጋል ይላል።

ባይደን ከሲቢኤስ ቴሌቪዥን 60 ደቂቃ ከተሰኘው ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ይህንን በድጋሚ አስረግጠዋል።

“የአንድ-ቻይና ፖሊሲ አለ። ታይዋንም ነጻነቷ ላይ ራሷ ትወስናለች። እኛ አንንቀሳቀስም፣ ነፃነታቸውን አናበረታታም። ይህ የራሳቸው ውሳኔ ነው” ብለዋል።

ባይደን ታይዋን ጥቃት ከደረሰባት ለመከላከል ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚኖር በግንቦት ወር ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተዋል። ዋይት ሐውስም በፍጥነት አሜሪካ ከረዥም ጊዜ ፖሊሲዋ አትወጣም በማለት በፍጥነት ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

አሁንም ዋይት ሐውስ ባይደንን የሚቃረን መግለጫ አውጥቷል። “ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በቶኪዮ ይህንኑ ተናግረዋል። የታይዋን ፖሊሲ እንዳልተለወጠም ግልፅ አድርገዋል። ይህ እውነት ነው” ብሏል።

ይህ ግን በአንድ ዓመት ውስጥ ፕሬዝደንቱ ከይፋዊ የአገሪቱ አቋም ርቀው ለወታደራዊ እርምጃ ቃል ሲገቡ ይህ ለሦስተኛ ጊዜ ነው። በጥቅምት እና በግንቦት ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተዋል።

በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ለታይዋን 1.1 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያዎች እና ፀረ ሚሳኤሎች ለመሸጥ ተስማምታለች። ይህም የቻይናን ክፉኛ አስቆጥቷል።

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በነሐሴ ወር በደሴቲቱ ያደረጉት አወዛጋቢ ጉብኝት በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለውን ውጥረት አባብሶታል። ባይደን ጉብኝቱን ቀደም ብለው “ጥሩ ሃሳብ አይደለም” ብለው ነበር።

በምላሹ ቤይጂንግ በታይዋን ዙሪያ ለአምስት ቀናት የቆየ ወታደራዊ ከበባ በማድረግ ልምምድ አካሂዳለች።

ዩናይትድ ስቴትስ ወደ ደሴቲቱ ሚሳኤል መተኮሱን ብትናገርም ቤይጂንግ ግን ይህንን አላረጋገጠችም። ቻይና የተኮሰችው ሚሳኤሎች ምንም አይነት ስጋት እንዳልፈጠሩ ታይዋን ተናግራለች።

ቀደም ብሎ ተቀርጾ እሑድ በተላለፈው ቃለ መጠይቅ ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት የኬሚካል ወይም የታክቲካል የጦር መሳሪያ እንዳትጠቀም ባይደን አስጠንቅቀዋል።

News today, Politics

አሜሪካ እና ታሊባን የእስረኛ ልውውጥ አደረጉ

በልውውጡ ፤ ታሊባን ለ17 ዓመታት ያክል በአሜሪካ እጅ የቆየው የጦር አዛዥ ባሻር ኑርዛይን ተቀብሏል

የጦር አዛዡ ባሻር ኑርዛይን ታሊባን ወደ ትጥቅ ትግል ሲገባ ለቡድኑ “የጦር መሳሪያ ድጋፍ” ሲያደረግ የነበረ ነው ተብሏል

ታሊባን በአሜሪካ እጅ የነበረውን የጦር አዛዥ ለማስፈታት ከሁለት አመት በላይ ታስሮ የነበረውን አሜሪካዊ የባህር ኃይል አርበኛ ለዋሽንግተን አሳልፎ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

የአፍጋኒስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካን ሙታቂ በካቡል ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ዛሬ ማርክ ፍሬሪችስ ለአሜሪካ ተላልፎ ተሰጥቷል ፤ እኛም የጦር መሪው ሃጂ ባሻር ኑርዛይ በካቡል አየር ማረፊያ ተሰጥቶናል” ብለዋል።

ልውውጡ የተከናወነው “ከረጅም ድርድር በኋላ” መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በካቡል ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አንድ የሀገራችን ልጅ ወደ ሀገሩ ሲመለስ የነበረውን አስደናቂ ስነ ስርዓት በማየታችን ደስተኛ ነን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኑርዛይ በአውሮፕላን ማረፊያው ሲደርስ በአዲሱ የአፍጋኒስታን እስላማዊ ኢሚሬትስ (አይኢኤኤ) መንግስት የጀግና አቀባበል እንደተደረገለትም ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

በማህበራዊ የትስስር ገጾች በመዘዋወር ላይ ያሉ ፎቶዎች የሚያሳትም፤ኑርዛይን የአበባ ጉንጉን በያዙና ጭንብል በለበሱ የታሊባን ባለስልጣናት አቀባበል ሲደረግለት ነው፡፡

ለበርካታ አመታት በአሜሪካ እጅ የቆየው የጦር አዛዡ ባሻር ኑርዛይ ወደ ሀገሩ ከተመለሰ በኋላ በሰጠው መግለጫ የታሊባን አመራሮች እሱን ለመስፈታት የተጓዙት የድርድር ርቀት አድንቋል፡፡

“ታሊባን ጠንካራ ቁርጠኝነቱን ባያሳይ ኖሮ ዛሬ እዚህ ባልነበርኩ ነበር” ብሏል ኑርዛይ።

ባሻር ኑርዛይ – ከሄሮይን ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ለ17 ዓመታት በአሜሪካ ታስሮ የቆየ የጦር አዛዥ ሲሆን ማርክ ፍሬሪችስ ደግሞ እንደፈረንጆቹ በ2020 ታፍኖ ተወስዶ በታሊባን ቁጥጥር ስር የቆየ የአሜሪካ የባህር ኃይል አርበኛ ነው፡፡

የአሜሪካ የባህር ኃይል አርበኛው ማርክ ፍሬሪችስ በአፍጋኒስታን ውስጥ በግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ በሲቪል መሃንዲስነት ሲሰራ የነበረ እንደሆነም ነው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገለጸው፡፡

ኑርዛይ በታሊባን ውስጥ ምንም አይነት ኦፊሴላዊ ቦታ አልነበረውም ነገር ግን በ 1990 ዎቹ ውስጥ ጠንካራው እንቅስቃሴ ብቅ ባለበት ወቅት “ጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ ለታሊባን ጠንካራ ድጋፍ ያደረግ ነበር” ያሉት ደግሞ የአፍጋኒስታን መንግስት ቃል አቀባይ ዛቢሁላህ ሙጃሂድ ናቸው፡፡

ከአንድ አመት በፊት የአሜሪካና አጋሮቿ ጦር ከ20 ዓመታት ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በኋላ አፍጋኒስታንን ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ፤ ታሊባን አፍጋኒስታንን እያስተዳደረ እንደሚገኝ የሚታወቅ ነው፡፡ 

News today, Politics

ሞስኮ፤ የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን የጦር ወንጀል ፈጽመዋል የሚለውን ውንጀላ “ውሸት” ነው አለች

ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ፤ የሩሲያ ኃይሎች በኢዚዮም የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ሲሉ ከሰዋል

ኢዚዮም በተባለ ስፍራ 450 የሚጠጉ በጅምላ ተቀብረው የነበሩ አስክሬኖች እንደተገኙ መረጃዎች እየወጡ ነው

ሞስኮ፤ የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት የጦር ወንጀል ፈጽመዋል የሚለውን ውንጀላ “ውሸት” ነው አለች፡፡

የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ኃይሎች የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የዩክሬኗ ካርኪቭ ግዛት መልቀቃቸውን ተከትሎ ኢዚዮም በተባለ ስፍራ 450 የሚጠጉ በጅምላ ተቀብረው የነበሩ አስክሬኖች እንደተገኙ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡

በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጡት የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ክሱ መሰረተ ቢስ ነው ሲሉ ውድቅ አድርገዋል፡፡

ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ ክሱ “በቡቻ ውስጥ እንደነበረው ተመሳሳይ ነው፤ ‘ውሸት ነው’ እናም በዚህ ተረት ውስጥ ያለውን እውነት እንዲታወቅ እናደርጋለን” ሲሉም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

የሩሲያው ቃል አቀባይ ይህን ይበሉ እንጅ የኪቭ ባለስልጣናት በቦታው የጦር ወንጀል እንደተፈጸመ እንደሚያምኑ ይህንንም ሰንደው ለማስቀመጥ እየሞከሩ እንደሆነ በመደመጥ ላይ ናቸው፡፡

ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ በቦታው ላይ የሚገኙ መርማሪዎች በእጃቸው የታሰሩ አስክሬኖችን ጨምሮ በርካታ የማሰቃየት ድርጊት የተፈጸመባቸው ሰዎች ለመኖራቸው አመላካች የሆኑ ማስረጃ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

በጅምላ መቃብሩ ውስጥ አብዛኞቹ ንጹሀን ዜጎች ፣ ሴቶችና ህጻናትም ይገኙበታል ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያ ኃይሎች ፈጽመውታል የተባለው ድርጊት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኩልም ቢሆን በከፍተኛ ደረጃ የተወገዘ ሆኗል፡፡

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ፣ በኢዚዮም ደን መቃብሮች መገኘታቸው “እጅግ አስደንጋጭ ነው” ብለዋል።

 ድርጊቱ አስደንጋጭና የሩሲያ ኃይሎች ዩክሬን ውስጥ ከፈጸሟቸው ጭካኔ የተሞሉ ወንጀሎች ጋር የሚመሳሰል ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፤ አሜሪካ የጦር ወንጀል በመሰነድ ድጋፍ መስጠት እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በበኩላቸው “የተፈጸመውን እጅግ እናወግዛለን” ብለዋል።

በኢዚዮም ተገኘ በተባለው የጅምላ መቃብር “እጅጉን መደንገጡ” የገለጸው ደግሞ የአውሮፓ ህብረት ነው፡፡

ህብረቱ የተፈጸመውን ድርጊት አጥብቆ እንደሚያወግዝ የገለጹት የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፕ ቦሬል፤ ድርጊቱ ዓለም አቀፍ ህግጋቶችን የጣሰ መሆኑ ተናግረዋል፡፡

 “በሩሲያ ኃይሎች የሚፈጸመው ኢሰብዓዊ ድርጊት የዓለም አቀፍ የሰብአዊ ህግጋትን እና የጄኔቫን ስምምነቶችን የጣሰ ነው፤ በአስቸኳይ መቆም አለበት” ብለዋል ጆሴፕ ቦሬል፡፡

አክለውም ፤የአውሮፓ ህብረት በዩክሬን ውስጥ እየተፈጸመ ላለው ወንጀል ሩሲያን ተጠያቂ ለመድረግ የሚደረጉ ሁሉንም ጥረቶችን ይደግፋል ብለዋል፡፡ 

News today, social life

የአውሮፓ ሀገራት ለኑሮ ውድነት ድጎማ 300 ቢሊየን ዩሮ ወጪ ማድረጋቸው ተገለጸ

ሩሲያ የአውሮፓ ህብረት የጣለብንን ማዕቀብ ሳያነሳ ነዳጅ አልክም ብላለች

ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያ፣ ስፔን እና ግሪክ በነዳጅ ዋጋ መናር ክፉኛ የተጎዱ ሀገራት ናቸው ተብሏል

የአውሮፓ ስድስት ሀገራት ለኑሮ ውድነቱ ድጎማ 300 ቢሊየን ዩሮ ወጪ ማድረጋቸው ተገለጸ።

የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ሰባት ወራት ሊሆነው ጥቂት ቀናት የቀሩት ሲሆን ጦርነቱን ተከትሎ የዓለም ነዳጅ እና ምግብ ዋጋ በየዕለቱ እየጨመረ ይገኛል።

ሩሲያ ለአውሮፓ ሀገራት 40 በመቶ የነዳጅ ፍላጎትን የምትሸፍን ቢሆንም ጦርነቱን ተከትሎ ነዳጅ ወደ አውሮፓ እንዳትልክ ማዕቀብ ተጥሎባታል።

በሩሲያ ነዳጅ ላይ ጥገኛ የሆኑት አውሮፓውያን ደግሞ ታይቶ በማይታወቅ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት እየተጎዱ ሲሆን የዜጎቻቸውን ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ አማራጮችን በመከተል ላይ ናቸው።

ስድስት የአውሮፓ ሀገራት ብቻ እስካሁን ለሀይል ድጎማ በሚል ያወጡት ገንዘብ 300 ቢሊዮን ዩሮ እንደደረሰ ሮይተርስ ዘግቧል።

እነዚህ ሀገራት ከዓመታዊ መጠባበቂያ በጀታቸው ላይ 23 በመቶውን ለነዳጅ ድጎማ ያዋሉት ሲሆን ጉዳቱ ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።

የጀርመን መንግስት ካሳለፍነው የካቲት ወር ጀምሮ ለነዳጅ ድጎማ ያወጣው ወጪ 95 ቢሊዮን ዩሮ ሲደርስ ከአውሮፓ ሀገራት በጦርነቱ ከተጎዱ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ሆናለች።

ሌላኛዋ በነዳጅ ዋጋ መናር ከተጎዱ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ፈረንሳይ ስትሆን 67 ቢሊዮን ዩሮ ለነዳጅ ድጎማ ወጪ አድርጋለች ተብሏል፡፡ ይህም በዓመታዊ ምርቷ ላይ የ5 በመቶ ጉድለት እንዲመዘገብ አድርጓል ተብሏል።

ነዳጅን ተጠቅመው ለህብረተሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለሚሰጡ ተቋማት የነዳጅ ድጎማ በማድረጓ 52 ቢሊዮን ዩሮ ወጪ ያደረገችው ሌላኛዋ አውሮፓት ሀገር ደግሞ ጣልያን ናት።

ደቡብ አውሮፓዊቷ ስፔንም ለነዳጅ ድጎማ በሚል 30 ቢሊዮን ዩሮ ወጪ ያደረገች ሲሆን በባንኮች እና ግዙፍ የሀይል ልማት ተቃማት ላይ የግብር ቅነሳ ማድረጓንም አስታውቃለች።

ሆላንድ፣ ግሪክ እና ሆላንድም ዜጎቻቸው በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንዳይጎዱ በሚል እያንዳንዳቸው ከ6 እስከ 10 ቢሊዮን ዩሮ ወጪ አድርገዋልም ተብሏል።

News today, Politics

በሶማሊያ መንግስት የሚደገፉ ሚሊሻዎች 45 የአልሸባብ ታጣቂዎችን ገደሉ ተባለ

አልሸባብ በቅርቡ አንድ ሆቴል በመክበብ 21 ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል

የሶማሊያ ፕሬዝደንቱ አልሸባብን ለማጥፋት ጠንካራ እንቅስቃሴ እየታየ መሆኑን ተናግረዋል

በሶማሊያ መንግስት የሚደገፉ ሚሊሻዎች ቢያንስ 45 የአልሸባብ ታጣቂዎችን መግደላቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ግድያው የአልቃይዳ አጋር በሆነው ቡድን እና በፌዴራል መንግስት በሚደገፉ ሚሊሻዎች መካከል ከፍተኛ ግጭት የታየበት የግዛት የቅርብ ጊዜ ክስተት ነው ተብሏል።

አልሸባብ በሶማሊያ የሸሪዓ ህግን በጥብቅ እንዲተገበር ለማስገደድ ከአስር አመታት በላይ ጦርነት ከፍቷል።

ቡድኑን ለማጥፋት በአካባቢውም ሆነ በግዛቱ ሃይሎች ጥረት ቢደረግም ቡድኑ በመላ ሀገሪቱ ብጥብጥ ማድረጉን እንደቀጠለ ነው። 

ባለፈው ወር ታጣቂ ቡድኑ በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ የሚገኘውን ሆቴል ለ30 ሰአታት ከበባ በማድረግ በትንሹ 21 ሰዎች ሲገደሉ ከመቶ በላይ ማቁሰሉ ይታወሳል።

በሰኔ ወር የአልሸባብ ታጣቂዎች ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስኗቸው አቅራቢያ እና አዋሳኝ መንደሮች ላይ በርካታ ጥቃቶችን ፈጽመው ከ12 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል።

 በጥቃቱ በደርዘን የሚቆጠሩ የቡድኑ ታጣቂዎችም ተገድለዋል።

ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ግን አርብ ዕለት ሀገራቸው ከአልሸባብ ጋር በምታደርገው ትግል ትልቅ ስኬት እያየች ነው ብለዋል።

ፕሬዝደንቱ አልሸባብን ለማጥፋት ጠንካራ እንቅስቃሴ እየታየ መሆኑን ተናግረዋል።

News today, social life

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7 ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል

በታይዋን የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ጉዳት አስከተለ

በጃፖን በሬክተርስኬል መጠኑ 6 ነጥብ 8 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከስቶ በ146 ሰዎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

የታይዋን አየር ንብረት ቢሮ እንደገለጸው ህዝብ ተራርቆ በሚኖሮበት በደቡብ ምስራቅ ታይዋን የተከሰተው መሬት መንቀጥቀጥ ባቡሮች እንዲገለበጡ፣ የስቶር መደርደሪያዎች እንዲደረመሱና መንገዶች እንዲዘጉ ምክንያት ሆኗል።

ቢሮው የመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ ታይተን ግዛት ሲሆን በአካባቢው የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ግን ጉዳት አላደረሰም ብሏል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ በትናንትናው እለት የተከሰተውን መሬት መንቀጥቀጥ መጠኑ 7ነጥብ2 እና ጥልቀቱ 10 ኪ.ሜ መሆኑን ገልጿል።

የታይዋን የእሳት ዲፖርትመንት በአደጋው የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን እና 146 ሰዎች መጎዳታቸውን አስታውቋል።

የታይዋን የሬይል ዋይ አስተዳደር ደግሞ ስድስት ባቡሮች መስመራቸውን ስተው መግልበጣቸውን እና በሰው ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልጿል።

በአደጋው በተዘጋው መንገድ ምክንያት በተራራማ አካባቢዎች መንገድ የተዘጋባቸውን 600 ሰዎች ለማውጣት ጥረት ላይ ናቸው።

የአሜሪካው የፖስፊክ የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ማእከል ከመንቀጥቀጡ አደጋው በኋላ ማስጠንቀቂያ አውጥቶ የነበረ ቢሆንም ቆይቶ አንስቶታል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በዋና ከተማዋ ታያፒ ጨምሮ በመላው ታይዋን ተሰምቷል ተብሏል።

በፈረንጆቹ 2016 በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 100 ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ባይደን “የአሜሪካ ጦር ታይዋንን ከቻይና ወረራ ይከላከላል” አሉ

ታይዋን በቻይና እንዳትወረር ከጦር መሳሪያ በተጨማሪ የአሜሪካ ሰራዊት አባላት እንደሚሳተፉም አስታውቀዋል

በታይዋን ጉዳይ ቻይና ከአሜሪካ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብርም ማቋረጧን ማስታወቋ ይታወሳል

የአሜሪካው ፕሬዝዳት ጆ ባይደን ጦራቸው ታይዋንን ከቻይና ወረራ እንደሚከላከል አስታወቁ።

ፕሬዝዳንት ባይደን ከሲ.ቢ.ሲ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ታይዋንን ተበመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ ቻይና ታይዋን ላይ ያልተጠበቀ ጥቃት ከከፈተች ጦራቸው ራስ ገዝ የሆነችውን ታይዋንንን ለመከላከል ወደ ስፍራው ሊያቀና ይችላል ብለዋል።

ጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የተጠየቁት ባይደን ባይደን፤ ከዩክሬን በተለየ በጦር መሳሪያ መደፍ ብቻ ሳይሆን የአሜሪካ ወታደሮች ታይዋንን ለመከላከል ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ አረጋግጧል።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በግንቦት ወር በጃፓን አድርገውት በነበረው ጉብኝት ላይ ቻይና በታይዋን ላይ ወረራ ከፈጸመች፤ አሜሪካ ወታደራዊ አጸፋ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን መናራቸውም የሚታወስ ነው።

የቻይና መከላከያ ሚኒሰቴር ከወራት በፊት በበታይዋን ጉዳይ እንደማይደራደር እና ውጊያ መግጠም ካለባትም ለመግጠም ዝግጁ መሆኑን ለአሜሪካ መግለጹ ይታወሳል።

የቻይናው መከላከያ ሚኒስትር ዌዪ ፈንጊሄ፤ ከአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ሎልዩድ አውስቲን ጋር ከኢስያ የደህንነት ጉባዔ ጎን ለጎን ተገናኝተው ባደረጉት ውይይት፤ ታይዋንን ከቻይና መገንጠል የቻይና ወታደር “ማንኛውንም አይነት ዋጋ በመክፈል ከመዋጋት ውጭ ምርጫ እንዳይኖረው ያደርጋል” ሲሉ ነበር የተናገሩት።

“ህዝባዊ ነፃ አውጪ ጦር” በመባል የሚጠራው የቻይና ጦር የሀገሩን ብሔራዊ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነትን ከማስጠበቅ በቀር ሌላ ምርጫ እንደማይኖረውም ሚኒስትሩ በወቅቱ አሜሪካን አሳስበዋል።

የአሜሪከ አፈ-ጉባኤ ናንሴ ፔሎሲ ባሳለፍነው ሐምሌ ወር ቻይና የግዛቷ አድርጋ የምትቆጥራትን ታይዋንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ቻይና አሜሪካ እና ታይዋን ጋር ያላት ግንኙነተ በከፍተኛ ደረጃ መሻከሩ የሚታወስ ነው።

ይህንን ተከትሎም ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሮችን ማቋረጧን ያሳወቀች ሲሆን ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን ማጓጓዝ፣ አደገኛ እጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን አቋርጣለች።

News today, Technology

የአሜሪካው ናሳ ወደ ጨረቃ ሊያመጠቅ የነበረው ሮኬት ለሁለተኛ ጊዜ ከሸፈ

ሮኬቱ ላይ ነዳጅ መፍሰስ በማጋጠሙ ማስወንጨፉ ለሁለተኛ ጊዜ ተቋርጧል

የአሜሪካው ናሳ “አርቴሚስ 1” ሮኬት

አሜሪካ ከ50 ዓመታት በኋላ ተመራማሪዎችንና መሳሪያዎቻቸውን ወደ ጨረቃ ለመላክ እየሰራች ነው

የአሜሪካው ናሳ “አርቴሚስ 1” የተባለ ሮኬትን ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ ያደረገው ሙከራ ለሁለተኛ ጊዜ መክሸፉ ተሰምቷል።

የናሳ ተመራማሪዎች በትናትናው እለት ሮኬቱን ለማስወንጨፍ የሚረዳውን የጠፈር ማስወንጨፊያ ስርዓት ለማስጀምር በተደጋጋሚ ቢሞክሩም ለሁለተኛ ጊዜ ሳይሳካቸው ቀርቷል።

የሮኬቱ ማስወንጨፍ ለሁለተኛ ጊዜ ሳይሳካ የቀረው በማስወንጨፊያው ላይ ባጋጠመው የነዳጅ መፍሰስ እንደሆነም ታውቋል።

ይህንን ተከትሎም የዘርፉ ባለሙያ ኢንጂነሮች በሮኬቱ ላይ ድጋሚ ፍተሻ ያደርጋሉ የተባለ ሲሆን፤ ይህም ጊዜ ሉወስድ ይችላል ተብሏል።

ፍተሸው ከማስወንጨፊያ ስፍራ ይልቅ በመስሪያ ቦታው ላይ ተወስዶ ሊካሄድ እንደሚችል እና ይህም የሮኬቱን የማስወንጨፊያ ጊዜ እስከ ጥቅምት ወር ሊያዘገየው ይችላል ነው የተባለው።

ናሳ ሮኬቱን ባሳለፍነው ሰኞ ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ ሞክሮ የነበረ ሲሆን፤ ሆኖም ግን አራቱ ትላልቅ ሞተሮች በትክክለኛ የሥራ ሙቀት ላይ መሆናቸውን ተቆጣጣሪዎች ማረጋገጥ ባለማቻላቸው ተቋርጦ ነበር።

ሮኬቱን የማስወንጨፍ ሙከራ ከትናትናው ጋር ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፤ መሳካት ግን አልቻለም።

አሜሪካ ከ50 ዓመታት በኋላ ተመራማሪዎችንና መሳሪያዎቻቸውን ወደ ጨረቃ ለመላክ እየሰራች ሲሆን፤ ይህም የአፖሎ ፕሮጀክት እአአ በ1972 ካበቃ በኋላ የተሰራ ነው።

6100 ሜትር የሚረዝመው ሮኬት አላማው ኦሪዮን የተባለውን ካፕሱል ወደ ጨረቃ ለማድረስ አላማ ኖሮት የተሰራ መሆኑንም ከናሳ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

News today, Technology

አፕል በአደጋ ወቅት ኔትዎርክ ከሌለበት ስፍራ በሳተላይት መልእት የሚልክ አይፎን 14 ይፋ አደረገ


አፕል ለስፖርተኞች የሚሆን “አልትራ” ስማርት ሰዓትም አስተዋውቋል

አፕል የመኪና አደጋ ቀደሞ መለየት የሚያችል ቴክኖሊጂ የተገጠመለት ስማርት ስልክም አስተዋውቋል

የአሜሪካው የቴክኖሎጂ ኩባያ አፕል በትናትናው ምሽት በበርካቶች ዘንድ ሲጠበቅ የነበረውን አይፎን 14 ስማርት ስልክን ጨምሮ ሌሎችም አዳዲስ የቴክኖለጂ ምርቶችን አስተዋውቋል።

አፕል ኩባያ በትናትናው እለት ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ በቴክኖሎጂ የረቀቁ የአይፎን 14 ስማርት ስልኮች፣ ስማርት ሰዓት እንዲሁም የማዳመጫ ምርቶቹን ይፋ አድርጓል።

ክባያው ሁለት የአይፎን 14 ስማርክ ስልክ አይነቶችን ያስተዋወቀ ሲሆን፤ እነዚህም አይፎን 14 እና አይፎን 14 ፕላስ ናቸው።

ስማርት ስልኮቹ በቴክኖሎጂ የረቀቁ ናቸው የተባለ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ በአደጋ ጊዜ ኔትዎርክ በሌለበት አካባቢ ላይ ስንሆን ከሳተላይት ጋር በመገናኘት መልእክት ለመላክ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተገጥሞለታል።

ስማርት ስልኩ ያለ ሞባይል ኔዎርክ ከሳተላይት ጋር ተገናኝቶ መልእክት ለመላክ ዝቅተኛው 15 ሰከንድ ከፍ ካለ ደግሞ ጥቂት ደቂቃዎችን ሊፈጅበት ይችላል።

አዲሱ አይፎን 14 ከጀርባው ላይ ሶስት 12 ሜጋ ፒክስል ጥራት ያላቸው ካራዎች የተገጠሙ ሲሆን፤ የፊትለፊት (ሰልፊ) ካሜራውም 12 ሜጋ ፒከስል መሆኑ እና ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን የማስካከል ቴክኖሎጂም ተገጥሞለታል።

የአይፎን 14 ካሜራዎች ፈጣን እንቅስቃሴ ያላቸውን ቁሶች ፎቶ ማንሳት ጨምሮ በዝቅተኛ ብርሃን ፎቶ በማንሳት ረገድ 49 በመቶ ማሻሻያ እንደተረገም ኩባያው አስታውቋል።

ለስማርት ስልቹ የመሸጫ ዋጋ የተቆረጠላቸው ሲሆን፤ በዚህ የአይፎን 14 ዋጋ 799 የአሜሪካ ዶላር፣ የአይፎን 14 ፕላስ ደግሞ 999 ዶላር መሆኑም ታውቋል።

አፕል ኩባንያ ትናንት ካስተዋወቃቸው የቴክኖሎጂ ምርቶች ውስጥ ሲሪየስ 8 የተሰኘው ስማርት ሰዓትም ይገኝበታል።

ሲሪየስ 8 የተሰኘው ስማርት ሰዓት የመኪና አደጋ ቀደሞ መለየት የሚያስችል ቴክኖሊጂ የተገጠመለት ሲሆን፤ አደጋ ከደረሰ በኋላም የአደጋው የደረሰበትን አካባቢ የሚጠቁም መልእክት መላክ ይችላል ተብሏል።

ስማርት ሰዓቱ በተጨማሪም ለሴቶች የወር አበባን መከታተል እንዲሁም የሰውነትን ሙቀት በመለካት ክትትል ማድረግን ጨምሮ በርካታ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በውስጡ ይዟል።

አልትራ የተባለው ስማርት ሰዓትም አፕል ትናንት ካስተዋወቃቸው ውስጥ ሲሆን፤ በተለይም ለስፖርተኞች የሚያለግል ነው ተብሏል።

አልትራ ስማርት ሰዓት ውሃ የማያስገባ በመሆኑ ለዋነተኞች እንዲሁም በቀላሉ የማይሰበር እና አቧሯ የማያስገባ መሆኑ ደግሞ ለአትሌቶች እና ለሌሎችም ስፖርተኞች ያገለግላል።

News today, Politics

በአፍሪካ የነበሩ የዩክሬን ወታደሮች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

የዩክሬን ሰላም አስከባሪ ኃይል ሀገራቸው ከሩሲያ ጋር ጦርነት መጀመሯን ተከትሎ ወደ ኪቭ ለመመለስ ተገደዋል ተብሏል

ወታደሮቹ በተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስር በዲሞክራቲክ ኮንጎ ነበሩ

በአፍሪካ የነበሩ የዩክሬን ወታደሮች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

የመንግስታቱ ድርጅት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ያለውን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር ከተለያዩ ፈቃደኛ ሀገራት የተውጣጣ ሰላም አስከባሪ ጦር ማሰማራቱ ይታወሳል።

በዚህ ተልዕኮ ስራ ጦር ካዋጡ ሀገራት መካከል አንዷ አሁን ላይ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ ያለችው ዩክሬን ትገኝበታለች።

ሀገራቸው ከሩሲያ ጋር የገጠመችውን ጦርነት ለመመከት በሚል በዲሞክራቲክ ኮንጎ የነበሩ 250 የዩክሬን ወታደሮችም ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

እነዚህ ወታደሮች ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በተመድ ዓመቻችነት ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወታደሮቹን ካጓጓዙ አየር መንገዶች መካከል አንዱ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

በተመድ ስር ያለው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ዜጎች ተቃውሞ እያስተናገደ ሲሆን፤ ሰላም አስከባሪ ጦሩ ዜጎችን ከአማጺያን ጥቃት አልታደገም በሚል አየተተቸ ይገኛል።

የሀገሬው ዜጎችም ሰላም አስከባሪ ጦሩ ሀገራቸውን ለቆ እንዲወጣ በሰላማዊ ሰልፍ በመጠየቅ ላይ ሲሆን ይህ ሰላም አስከባሪ ጦር ከሁለት ወራት በፊት 36 ተቃዋሚዎችን ተኩሶ ገድሏል ተብሏል።

ከዚሁ ተቃውሞ ጋር በተያያዘም በኬንሺያሳ ያለው የተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ቃል አቀባይ የዲሞክራቲክ ኮንጎን ሉዓላዊነት የሚጋፋ አስተያየት ሰጥቷል በሚል ሀገሪቱቱን ለቆ እንዲወጣ ተደርጓል።

ተመድ በዓለም ላይ ፈቃደኛ ከሆኑ ሀገራት ጦር በማዋጣት በ12 ሀገራት ላይ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ያለው ሲሆን ለ22 ዓመት የቆየው እና ብዙ ገንዘብ ወጪ የተደረገበት ስምሪቱ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ያለው ነው።

News today, Technology

ቻይና በ2025 ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ማጓጓዝ ልትጀምር ነው

ቻይና ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የጉዞ አይነቶችን አዘጋጅታለች
የቻይና የጠፈር ጉዞ
የአንድ ሰው የጠፈር የጉዞ ትኬት ዋጋም ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይሆናል ተብሏል

ቻይና በፈረንጆቹ 2025 የግል ተጓዦችን በክፍያ ወደ ጠፈር ለማጓጓዘ እየሰራች መሆኑ ተገለፀ።

አንድ የቻይና የሮኬት ተመራማሪ እንዳስታወቁት ከሆነ የአንድ ሰው የጉዞ ዋጋ 2 እና 3 ሚሊየን የቻይና ዩዋን (ከ287 ሺህ እስከ 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር) ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል።

ለጥቂት ደቂቃዎች ወደ ጠፈር ለመጓዝ የአንድ ወንበር የጨረታ ዋጋ ከ2 ነጥበ 4 ሚሊዮን ዶላር አለፈ
በፈረንጆቹ በ2018 የተመሰረተው የሎንግ ማርች ሮክት ዋና ዳይሬክተር እና መቀመጫውን ቤጂንግ ያደረገው ሲ.ኤ.ኤስ ስፔስ ኤጀንሲ መስራች የሆኑት የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ፤ ግለሰቦችን ወደ ጠፈር ለማጓጓ ሶስት አይነት የመጓጓዣ ዘዴዎች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

የመጀመሪያው ወደ ዓለም አቀፍ የጠፈር ማዕከል መግባት የሚያስችል ሲሆን፤ ይህም ለቱሪስቶች ጥብቅ የሆነ የአካላዊ እና የስነ ልቦናዊ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሰቀምጥ ነው ተብሏል።

ጃፓናዊው ቢሊየነር የ12 ቀናት የጠፈር ቆይታውን አጠናቆ ተመለሰ
ሁለተኛው የጉዞ አይነት ቱሪስቶች መንኮራኩር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ በሌላ በካርጎ መንኮራኩር ወደ ጠፈር እንዲሄዱ ማድረግ የሚያስችል ሲሆን፤ ይህኛው ጉዞ በአንድ መቀመጫ 450 ሺህ ዶላር እንደሚያስከፍል ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

ሶስተኛው የጉዞ አይነት ሰብ ኦርቢታል የሚባል ሲሆን፤ ይህኛው የጉዞ አይነት ለአብዛኞቹ ጎብኚዎች የተመቸ እንደመሆን የሮክት ተመራማሪው ያንግ ዪክያንግ ገልፀዋል

News today, Technology

ባህር ስር የሚጓዘው “ፖሲዶን” ኒውክሌር ታጣቂው የሩሲያ ድሮን

ሰርጓጅ ድሮኑ ሱናሚዎችን በማስነሳት የጠላት ኢላማን የማጥፋት አቅም አለው

ከባህር ስር 1 ሺህ ሜትር ጥልቀት ላይ የሚጓዘው ድሮኑ፤ እስከ 10 ሺህ ኪ.ሜ ድረስ መሸፈን ይችላል

ሩሲያ በያዝነው የፈረንጆቹ 2022 ይፋ ካደረገቻቸው አውዳሚ የጦር መሳሪያዎች ውስጥ “ፖሲዶን” የባህር ሰርጓጅ ድሮን አንዱ ነው።

“ፖሲዶን” ሰርጓጅ ድሮን የምጽአት ቀን የሚል መጠሪያ በተሰጠው የሩሲያው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ላይ የሚገጠሙ ሲሆን፤ ከሰርጓጅ መርከቡ ላይ የሚወነጨፉ መሆኑም ታውቋል።

“ፖሲዶን” የሩሲያ ኒውክሌር ድሮን ምን የተለየ ያደርገዋል?

“ፖሲዶን” በባህር ስር የሚጓዝ ድሮን ሲሆን፤ የኒውክሌር አረር የሚሸከም ግዙፍ የሆነ የባህር ሰርጓጅ ድሮን ነው።

የውሃ ስር ድሮን ፕሮጀክቱ መሰራት እንደተጀመረ የሚያሳየው መረጃ በ2015 ላይ እንደወጣ የዘገበው ኢውሮ ኒውስ፤ የድሮኑ ዋነኛ ዓላማም የባህር ዳርቻ ላይ የሚገኙ የጠላትን ወታራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ስፍራዎችን ለማውደም ነው።

“ፖሲዶን” የኒውክሌር የባህር ሰርጓጅ ድሮን 20 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ከባህር ስር እስከ 1000 ሜትር ጠልቆ መጓዝ እንደሚችልም ተመላክቷል።

የባህር ስር ድሮኑ እስከ 10 ሺህ ኪሎ ሜትር ድረስ የማካለል እና የጠላትን ኢላማ የመምታት አቅም ያለመው መሆኑም ተመላክቷል።

አብዛኛው የባህር ስር ድሮኑ ዝርዝር መረጃዎች እስካሁን በሚስጥር የተያዙ ሲሆን፤ ካለው ፍጥነት የተነሳ መከላከልም ሆነ ለማስቆም አዳጋች እንደሆነ ግን ተነግሯል።

የባህር ስር ድሮኑ ሰው ሰራሽ ሱናሚ ማእበሎችን ማስነሳት ይችላል የተባለ ሲሆን፤ እስከ 500 ሜትር ርዝመት ያለው ሱናሚ በማስነሳትም የባህር ዳርቻ ከተሞችን እንዳልነበሩ አድርጎ ሙሉ በሙሉ ማውደም ይችላል ተብሏል።

የብሪታኒያው ዴይሊ ሜይል ጋዜጣ እንዳስነበበው እነዚህን ድሮኖች የተሸከመው ቤልግሮድ ሰርጓጅ መርከብ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ በነጭ ባህር ላይ መታየቱን እና በወቅቱም ዲሚትሪ ዶንስኮይ የተባለ ሌላ የጦር መርከብ አብሮት እንደበረ ይታወሳል።

News today, Politics

አፍሪካ ምን ማድረግ እንዳለባት ማንም ሊያዛት እንደማይገባ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ተናገሩ

አሜሪካ ከሩሲያ ጋር የሚወዳጁ የአፍሪካ ሀገራትን እንዳትቀጣም ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል

ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጋር በዋሸንግተን ተወያይተዋል

አፍሪካ ምን ማድረግ እንዳለባት ማንም ሊያዛት እንደማይገባ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ተናገሩ።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ሰባተኛ ወሩ ላይ የሚገኝ ሲሆን ጦርነቱን ተከትሎ ምዕራባዊያን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም ለመነጠል የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ያገኛሉ።

አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያን ሀገራት ዩክሬን በሩሲያ ላይ ድልን እንድትቀዳጅ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ከመስጡ ጎን ለጎን በሞስኮ ላይ ማዕቀብ በመጣል ላይ ናቸው።

ይህ በዚህ እንዳለም አፍሪካን ጨምሮ ከሩሲያ ጋር ወዳጅነትን በሚመሰርቱ ሀገራት ላይ ግንኙነታቸውን እንዲያቋርጡ የተለያዩ ጫናዎችን በማድረግ ላይ ናቸው።

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ወደ ዋሸንግተን ተጉዘው በነጩ ቤተ መንግስት ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ተወያይተዋል።

ሩሲያ የየትኛውም የዓለማችን ባለጸጋ ሀገር ጋር የተለየ ግንኙነት የላትም ያሉት ፕሬዝዳንት ራማፎዛ አሜሪካም በአፍሪካ የተለየ ተጽዕኖ ማድረግ እንደሌለባት አክለዋል።

የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ተጽዕኖ ልታደርግ እንደማይገባ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ አፍሪካ ምን ማድረግ እንደሚገባት ማንም መናገር አይችልም ሲሉም አክለዋል።

አሜሪካ አፍሪካ ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንድታቋርጥ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረገች ሲሆን በአንድ ወር ውስጥ በተመድ የዋሸንግተን ተወካይ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ እና የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወደ አፍሪካ በመምጣት ስድስት ሀገራትን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

የመሪዎቹ ወደ አፍሪካ መምጣት ዋና አላማው ከሩሲያ ጋር ጠያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ጫና መፍጠር ሲሆን አፍሪካ ከሩሲያ ከአፈር ማዳበሪያ እና ስንዴ ውጪ ሌሎች ምርቶችን መግዛት እንደማይችሉ ተናግረውም ነበር።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በምዕራብ አፍሪካ ባደረጉት ጉብኝት አፍሪካ በሩሲያ ላይ የተለሳለሰ አቋም አሳይተዋል በሚልም ትችት ሰንዝረዋል።

News today, social life

ግብጽ በስዊዝ ካናል ላይ የ15 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ማድረጓን አስታወቀች

ግብጽ ከስዊዝ ካናል በዓመት ሰባት ቢሊዮን ዶላር ገቢ እያገኘች ነው

የዋጋ ጭማሪው ከመጭው ጥር ወር ጀምሮ የተገበራል ተብሏል

ግብጽ በስዊዝ ካናል ላይ የ15 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ማድረጓን አስታወቀች።

ሰሜን አፍሪካዊቷ ግብጽ ከቀጣዩ ጥር ወር ጀምሮ በስዊዝ ካናል በሚያልፉ መርከቦች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጓን አስታውቃለች።

ሮይተርስ የስዊዝ ካናል ሊቀመንበርን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ ግብጽ በእቃ ጫኝ መርከቦች ላይ የ15 በመቶ በትራንዚት እና በጎብኚዎች መርከቦች ላይ ደግሞ የ10 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ተጨምሯል።

የግብጽ ዋነኛ የገቢ ምንጭ የሆነው የስዊዝ ካናል በፈረንጆቹ 1869 ዓመት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት የሆነ ሲሆን ይህ የመርከቦች መጓጓዣ መስመር በቀን 50 መርከቦችን በማጓጓዝ ላይ ይገኛል።

ስዊዝ ካናል አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 153 ዓመት የሞላው ሲሆን ግብጽ ከስዊዝ ካናል ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ገልጻለች።

ስዊዝ ካናል ከ153 ዓመት በፊት ሜድትራኒያን ባህርን እና ህንድ ውቂያኖስን በማገኛኘት በአውሮፓ እና እስያ መካከል የሚደረገውን የባህር ላይ ጉዞ በማሳጠር ዘመናዊ የባህር ትራንስፖርት ያቀላጥፋል፡፡

በወቅቱ የግብጽ መሪ የነበሩት ካዲቭ እስማኤል ፓሻ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ የመርከቦች መተላለፊያ መስመር ግንባታው 10 ዓመታትን ፈጅቷል።

በዓመት 300 ሚሊዮን ቶን እቃዎች የሚተላለፉበት ስዊዝ ካናል የአገልግሎት መጠኑን ለማስፋት ግብጽ በየጊዜው የተለያዩ ማሻሻያዎችን አድርጋለች።

የአሁኑ የግብጽ ፕሬዝዳንት አልሲሲ በፈረንጆቹ 2014 ላይ በስዊዝ ካናል ላይ የተደረገውን የ8 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፋያ ግንባታ መመረቃቸው አይዘነጋም።

ስዊዝ ካናል በተሰራለት የማስፋፊያ ግንባታ መሰረት አሁን ላይ ስፋቱ 61 ሜትር በ312 ሜትር ላይ የደረሰ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት ከቻይና የመጣ ኮንቴይነሮችን የጫነች እቃ ጫኝ መርከብ መተላለፊያ መስመሩን ለአንድ ወር ዘግታ የ100 መርከቦችን እንቅስቃሴ በመግታት የዓለምን ንግድ ማስተጓጎሏ ይታወሳል።

News today, Technology

የጃፓን ተመራማሪዎች የሰዎች ቀለድ የሚያስቀው ሮቦት ሰርተዋል

ሮቦቱን ሳቅ ያስተማሩት የጃፓን ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ናቸው

የሚስቀው ሮቦት ፕሮጀክት ሮቦቶችን ከሰው ልጅ ጋር የማመሳሰል እቅድ አንዱ ካል ነው

የጃፓን ተመራማሪዎች ከዚህ በፊት ያልተመለደ “በሰዎች ቀልድ የሚስቅ ሮቦት” መስራታቸውን ከሰሞኑ አስታውቀዋል።

ሮቦቱን ሳቅ ያስተማሩት የጃፓን ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ሲሆኑ፤ ዋና አላማዉም ሮቦቶች የበለጠ ከሰው ልጆች ጋር ለማመሳሰል እንደሆነም ተነግሯል።

ክዮቶ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ሮቦቱ ትክክለኛ የሰው ልጆችን ሳቅ እንዲስቅ ለማለማመድም ሰው ሰራሽ ክህሎት (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ) መጠቀማቸውን አስታውቀዋል።

ተመራማሪዎቹ ኤሪካ የሚል ስያሜ ባለው ሮቦት ላይ ሳቅን የማስተማር ስራውን እየሰሩ ሲሆን፤ ይህ ስራም በሰዎች እና በሮቦቶች መካከል ያለው ንግግሮች የበለጠ ተፈጥሯዊ እንዲመስሉ እንደሚያደርግ ተስፋ ሰንቀዋል።

ርዝመታቸው ከሁለት እስከ ሶሰስተ ደቂቃ የሚቆዩ ንግግሮች በሰዎች እና በኤሪካ ሮቦት መካከል የተደረገ ሲሆን፤ ይህም አዲሱን ሲሰተም ለመመኮር እንደተካሄደ እና ስራውም በጎ ውጤት እንደተገኘበት አስታውቀዋል።

ሮቦቶቹ የበለጠ ከሰዎች ጋር እንዲግባቡ እና በቀልዶች የምር እንዲስቁ ለማስቻል አሁንም ቀሪ ስራች እንደሚቀሩ አስታውቀዋል።

በሰዎች እና በሮቦቶች መካከል ልክ ንደጓደኛ መደበኛ ንግግሮች እንዲኖሩ ለማስቻል እየሰሩ መሆኑን ያስታወቁት ተመራማሪዎቹ፤ ይህንን እውን ለማድረግ እን ከ10 እስከ 20 ዓመት ሊያስፈልገን ይችላል ብላዋል።

News today, social life

የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት ያልቻሉ ሊባኖሳዊያን ባንኮችን በጦር መሳሪያ እያስፈራሩ ነው

ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት ባንኮች ለደንበኞቻቸው ገንዘባቸውን መመለስ አልቻሉም

የሊባኖስ ባንኮች የፊታችን ሰኞ ጀምሮ በደህንነት ምክንያት ስራ ለማቆም ወስነዋል

የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት ያልቻሉ ሊባኖሳዊያን ባንኮችን በጦር መሳሪያ እያስፈራሩ ነው፡፡

የመካከለኛዋ ምስራቅ ሀገር ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት ዜጎች በባንክ የቆጠቡትን ገንዘብ ማግኘት አልቻሉም፡፡

ሊባኖስ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያጋጠማት ሲሆን የሀገሪቱ መገበያያ ገንዘብም የመግዛት አቅሙ መሽመድመዱን ተከትሎ ዜጎች ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል፡፡

አብዛኛው የሀገሪቱ ዜጎች ፍጆታ ከውጭ ሀገራት የሚገቡ በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ኢኮኖሚውን ወደ ከፋ አለመረጋጋት አስገብቶታል፡፡

በዚህም ምክንያት ባንኮች ከደንበኞቻቸው የተቆጠበ ገንዘብን መስጠት አለመቻላቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ ዜጎች የጦር መሳሪያ በድብቅ እያስገቡ የባንክ ሰራተኞችን እያስፈራሩ እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በየጊዜው የጦር መሳሪያ እየያዙ ወደ ባንኮች የሚያመሩ ዜጎች ቁጥር መጨመሩን ተከትሎ ባንኮች ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንደገጠማቸው ተጠቅሷል፡፡

ለአብነትም በትናንትናው ዕለት አንዲት እንስት የካንሰር ህክምናዋን በቱርክ እየተከታተለች ለምትገኝ እህቷ ገንዘብ መላክ በመፈለግ ወደ ባንክ ብትሄድም ባንኩ ሊያስተናግዳት ባለመቻሉ የጦር መሳሪያ ለመጠቀም መገደዷን ተናግራለች፡፡

በዛሬው ዕለትም በአምስት የሊባኖስ የተለያዩ ቦታዎች የባንክ ደንበኞች የጦር መሳሪያ ተጠቅመው ገንዘባቸውን ከባንኮች ለመውሰድ መሞከራቸው ተገልጿል፡፡

የደንበኞቻቸው የጦር መሳሪያ እየያዙ መምጣት ያሳሰባቸው የሀገሪቱ ባኮችም ከቀጣዩ ሰኞ ጀምሮ ለሶስት ቀናት አገልግሎት ላለመስጠት መወሰናቸውን አሳውቀዋል፡፡ 

News today, Politics

ጆ ባይደን፤ ቭላድሚር ፑቲን ታክቲካል ኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳይጠቀሙ አስጠነቀቁ

ባይደን፤ ፑቲን ኒውክሌር ከተጠቀመ “ጦርነቱን ከ2ኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ባልታየ ሁኔታ ይቀይረዋል” ሲሉ ተናግረዋል

ጆ ባይደን፤ “ፑቲን ቀይ መስመሩን ማለፍ የለበትም” ሲሉ አስጠንቅቀዋል

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፤ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳይጠቀሙ አስጠነቀቁ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ከሲቢኤስ ቴሌቪዥን ጋር ባረደጉት ቆይታ የታክቲካል የኒውክሌር መሳሪያ መጠቀም አደገኛ ሁኔታ ሊያስከትል ይችላል ብለዋል፡፡

ታክቲካል ኒውክሌር በመባል የሚታወቁት የአጭር ርቀት መሳሪያዎች ሲሆኑ፣ ስትራቴጂክ ኒውክሌር ደግሞ የረዥም ርቀት ተስወንጫፊ መሳሪያዎችን ያካትታሉ።

ፑቲን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ከተጠቀሙ “ጦርነቱን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ባልታየ ሁኔታ ይቀይረዋል” ያሉት ባይደን፤ “ፑቲን ቀይ መስመሩን ማለፍ የለባቸውም!” ሲሉም አስጠንቅቀዋል፡:

ፑቲን የኒውክሌር መሳሪያ በዩክሬን ለመጠቀም አስበው ከሆነ ምን መልዕክት ማስተላለፍ ይፈልጋሉ ተብለው በሲቢኤስ የተጠየቁት ባይደን ጋዜጠኛውን “ተው! ተው! ተው!” ሲሉ ታይተዋል።

ፕሬዝዳንት ጆ-ባይደን አሜሪካ የኒውክሌር ጥቃትን ተከትሎ ምን እርምጃ እንደምትወስድ በግልጽ ባይናገሩም “ዓለም ላይ ታይተው ከሚታወቁ ቀውሶች ሁሉ የባሰ ይሆናል፤ የሚከሰተውን ጉዳት ያህልም ምላሽ እንሰጣለን” ብለዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ይህን ይበሉ እንጅ፤ የክሬምሊን ባለስልጣናት የሶሞኑ መግለጫዎች የሚያመለለክቱት በተቃራኒው ነው፡፡

በዩክሬን ላለው ቀውስ አሜሪካን ጨመሮ ለኪቭ የጦር መሳሪያ ድጋፍ የሚያደርጉትን ምዕራባውያን ተጠያቂ የሚያደርጉት የሩሲያው መሪ ፑቲን፤ በዩክሬን ምድር ያሰብነውን ዓላማ ከማሳከት የሚገታን ኃይል የለም እያሉ ነው፡፡

በዚህም ዩክሬንን ሽፋን ደረገው የሩሲያ እና አሜሪካ ፍጥጫ አደገኛ ሁኔታ እንዳያስከትል ተሰግተዋል፡፡አሜሪካ በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ለኪቭ የሚያስፈለግ የጦር መሳሪያ በከፍተኛ ደረጃ ድጋፍ ከሚልኩ ሀገራት አንዷ መሆኗ ይታወቃል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ፤አሜሪካ 3 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የጦር መሳሪያ ድጋፍ ለዩክሬን እንደምትሰጥ በቅረቡ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

ድጋፉ ዩክሬን ፤በአየር መከላከያ እንዲሁም የመድፍ ስርዓቶችና ጥይቶችን እንድታጎለብት ብሎም ከረዠም ርቀት ጥቃቶች እራሷን መከላከል እንደምትችል ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸው ነበር፡፡

News today, Politics

አሜሪካ እና ሶማሊያ ሽብርተኝነት ለመዋጋት የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ

በሶማሊያ ፖለቲከኛች መካከል የነበረው ሽኩቻ “አልሻባብ እንዲያንሰራራ” እድል የፈጠረ መሆኑ ይነገራል

የሶማሊው ፕሬዝዳንት ፤ “አሜሪካ በሶማሊያ ዘላቂ ልማት እና እድገት ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋር ነች” ብለዋል

አሜሪካ እና ሶማሊያ ሽብርተኝነት ለመዋጋት የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ፡፡

ለይፋዊ ስራ ጉብኝት በአሜሪካ የሚገኙት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ሽብርተኝነትን መዋጋት፣ የሶማሊያ ድረቅ እና መልካም አስተዳደር ፕሬዝዳንቱ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በነበራቸው ቆይታ የመከሩባቸው አንኳር ጉዳዮች ናቸው፡፡

በውይይታቸው በተለይም ከሶማሊያ አልፎ የቀጠናው ስጋት የሆነውን ሽብርተኝነት ለመዋጋት ሀገራቱ የሚያደርጉት ትብብር አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በትዊተር ገጻቸው ያጋሩት መረጃ ያመለክታል፡፡

“አሜሪካ በሶማሊያ ዘላቂ ልማት እና እድገት ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋር ነች”ም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ፡፡

አሁን አሁን ከነበረበት ሁኔታ እያንሰራራ እየመጣ እንደሆነ የሚነገርለት አልሻባብን አደጋ ለመግታት በሚል፤ አሜሪካ በታጣቂ ቡድኑ ላይ የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኗ የሚታወቅ ነው፡፡

በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠናው ስጋት የሆነውን አልሻባብ ለመምታት 600 የሚሆኑ የሃገራቸውን ወታደሮች ወደ ሶማሊያ እንደሚልኩ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው።

የአሜሪካ ጦር በድጋሚ በሶማሊያ እንዲሰማራ የማድረግ ውሳኔ በየሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ተቀባይነት ማግኘቱም አይዘነጋም፡፡

ሶማሊያ አሁንም በአልሻባብ እየተፈተነች ነው። በተለይም ከምርጫ ጋር በተያያዘ በሃገሪቱ ፖሊተከኞች መካከል የነበረው ሽኩቻ ለሰላምና ጸጥታ ይሰጥ የነበረውን ትኩረት አላልቶት እንደነበር በርካቶች ያነሳሉ።

አሁኑ ላይ አሜሪካ በአልሻባብ ላይ የምትወስዳቸው እርምጃዎች አሜሪካ ቡድኑን ከማዳከም አንጻር ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል፡፡

የአሜሪካን ሚና እንደ ትልቅ የአጋርነት መገለጫ አድረጎ የሚወስደው የፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ አስተዳደር በቅረቡ “ለመረጋጋትና ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በምናደርገው ትግል አሜሪካ ወትሮም ቢሆን ታማኝ አጋራችን ናት” ሲል በትዊተር ገጹ ላይ ባወጣው ጽሁፍ ማጋራቱም የሚታወስ ነው፡፡

News today, Politics

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ከቻይና የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልእክተኛ ጋር በአስመራ ተነጋገሩ

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ፤ ጉብኝቱ በኤርትራ እና ቻይና መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የሚያጎለብት መሆኑ ተናግረዋል

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና ጉብኝት እንዲያደርጉ መጋበዛቸው ይታወሳል

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከቻይና የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሹ ቢንግን ጋር በአስመራ ተናገገሩ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ከልዩ መልዕክተኛው ጋር በነበራቸው ቆይታ በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዘለግ ያለ ውይይት ማድረጋቸው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል አስታውቀዋል፡፡

ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ “ሁለቱ ወገኖች በኤርትራ ቅድሚያ በሚሰጣቸው የልማት መስኮች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ተወያይተዋል” ብለዋል፡፡

ኤርትራ እና ቻይና በቀጣናዊ ትስስራቸው ማዕቀፍ ውስጥ የልማት ትብብር ለማካሄድ መስማማተቸውም ጭምር ተናግረዋል ፡፡

ጉብኝቱ በኤርትራ እና ቻይና መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት የበለጠ ለማጎልበት የሚያችል እንደሆነ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በውይይቱ መናገራቸውም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ኤርትራ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች በትብብር የሚሰሩ ሀገራት መሆናቸው ይታወቃል፡፡

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ በየካቲት በኤርትራ ባደረጉት ይፋወዊ የስራ ጉብኝት፤ በማዕድን ልማት፣ በምጽዋና አሰብ ወደቦች ልማት፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በመሰረተ ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራትም ከስምምነት መድረሳቸው የሚታወስ ነው፡፡

በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት ቻይና ለኤርትራ ተጨማሪ የ100 ሚሊየን ዩዋን ድጋፍ ማድረጓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋንግ ዪ በወቅቱ መግለጻቸው አይዘነጋም።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በበኩላቸው የቻይናን የ100 ዓመታት የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ጉዞ እና በዓለም ዐቀፍ ሕጎች ማዕቀፍ ውስጥ ሆና ዓለምን ሚዛናዊ ለማድረግ የምታደርውን ጥረት አድንቀዋል።

የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ፐሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና ጉብኝት እንዲያደርጉ ግብዣ እንደላኩላቸውም የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው አስፍረው ነበር፡፡

ኤርትራ፤ ቻይና በዓለም አቀፍ መድረክ የምታራምዳቸው አቋሞች በመደገፍ የምትታወቅ ሀገር መሆኗም ይታወቃል፡፡

News today, Politics

በአርመን እና አዘርቤጃን መካከል በተካሄደው ጦርነት ከ200 በላይ ወታደሮች ተገደሉ

አለምአቀፉ ማህበረሰብ ባለፈው ሀሙስ የተደረሰውን ተኩስ አቁም በአዎንታ ተቀብሎታል

አርመኒያ እና አዘርቤጃን ናጋርኖ ካራባክ በተባለው ተራራማ ግዛት ምክነያት ከፈረንጆቹ 1988 ጀምሮ ፍጥጫ ውስጥ ነበሩ

በቅርቡ በድጋሚ በተቀሰቀሰው የአርመን እና የአዘርቤጃን ጦርነት ከ200 በላይ ወታደሮች ተገደሉ፡፡

ሮይርስ እንደዘገበው የአርመንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሲኒያን በአርመን እና አዘርቤጃን መካከል በተቀሰቀሰው ጦርነት 135 ወታደሮች መገደላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

አሁን 135 ወታደሮች ህይወታቸው አልፏል፤ ብዙዎች ቆስለዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺኒያን “እንዳለመተል ሆኖ ይህ የመጨረሻ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሀለቱ ሀገራት በፈረንጆቹ 2020 ካደሩጉት ደምአፋሳሽ የስድስት ሳምንት ጦርነት ወዲህ በተቀሰቀሰው ጦርነት 71 ወታደሮች እንደተገደሉባት አዘርቤጃን ሪፖርት አድርጋለች፡፡

እስካሁን በሁለቱም ሀገራት የተገደሉ ወታደሮች ቁጥር ከ200 በላይ ሆኗል፡፡

አርመኒያ እና አዘርቤጃን ናጋርኖ ካራባክ በተባለው ተራራማ ግዛት ምክነያት ከፈረንጆቹ 1988 ጀምሮ ፍጥጫ ውስጥ ነበሩ፡፡ በፈረንጆቹ 1994 በተካሄድ የሰላም ድርድር ተኩስ አቁም የተፈራረሙ ቢሆንም ከዚያ ወዲህ አልፎ አልፎ ግጭት ውስጥ ሲገቡ ቆይተዋል፡፡

በቅርቡ የተጀመረውን ግጭት በሚመለከት ግን ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን በመጀመር እየተካሰሱ ይገኛሉ፡፡ አርመን፣ የአዘርቤጃን ሃይሎች ናጎርኖ ካራባክን አልፈውጥቃት በመክፈት አርመን ውስጥ ቦታ ይዘዋል የሚል ክስ ስታቀርብ፣አዘርቤጃን ደግሞ ለተፈጸመባት ትንኮሳ ምላሽ መስጠቷን ትገልጻለች፡፡

አለምአቀፉ ማህበረሰብ ባለፈው ሀሙስ የተደረሰውን ተኩስ አቁም በአዎንታ ተቀብሎታል፡፡

News today, Politics

ቱርክ፤ በሩሲያ እና ቻይና የሚመራው የጸጥታ ጥምረት አባል የመሆን አላማ እንዳላት ፕሬዝደንት ኤርዶጋን ተናገሩ

ኤስሲኦ በሩሲያ እና ቻይና የተመሰረተ የጸጥታ ጥምረት ነው

ፕሬዝደንቱ ይህን ያሉት በኡዝቤክስታን በተካሄደው የኤስሲኦ ስብሰባ ላይ ከተካፈሉ በኋላ ነው

የቱርኩ ፕሬዝደንት ኤርዶጋን የኔቶ አባል የሆነችውን ሀገራቸው የሻንጋይ ኮኦፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን(ኤስሲኦ) አባልጰየማድረግ አላማ እንዳላቸው ተናግረዋል።

ኤስሲኦ በሩሲያ እና ቻይና የተመሰረተ የጸጥታ ጥምረት ነው።

ፕሬዝደንቱ ይህን ያሉት በኡዝቤክስታን በተካሄደው የኤስሲኦ ስብሰባ ላይ ከተካፈሉ በኋላ መሆኑን ሮይተር ዘግቧል።

“በዚህ እርምጃ ከእነዚህ ሀገራት ጋር ያለን ግንኙነት ወደ ልዩ ቦታ ይደርሳል” ብሐዋል ፕሬዝደንት ኤርዶጋን።

ቱርክ በአሁኑ ወቅት ቻይና ሩሲያ ህንድ ፓኪስታን ኢራን ኪሪጊስታን ፓጃኪስታን ካዛኩስታን እና ኡዝቤኪስታን ያሉበት የጸጥታ ጥምረት የውይይት አጋር ነች።

በስብሰባው ላይ ከፕሬዝደንት ፒቲን ጋር የተነጋገሩት ኤርዶጋን በደቢብ ቱርክ በሚገኘው የኑክሌር ጣቢያ ጉዳይ የነበረውን ግጭት ለመፍታት ከስምምነት መድረሳቸውን ገልጸዋል።

በፈረንቹ 2001 የተቋቋመው በሩሲያ እና ቻይና የነበረ ሲሆን ከተመሰረተ ከአራት አመት በኋላ ህንድ እና ፓኪስታንን አካቷል፤ ይህም በቀጣናው ያለውን የምእራባውያን ጫና ለመቋቋም አላማ ያደረገ ነበር፡፡

News today, Technology

በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ላይ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር ገለፀ

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚጣለው የጉምሩክ ታሪፍ ዝቅተኛ እንደሚሆንም ሚኒስቴሩ አስታውቋል

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ ነፃ እንደሚደረጉ ተገለፀ

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኢንቨስትመንትንና አስመጪዎችን የሚያበረታታ እንዲሁም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም የታክስ ማሻሻያ ከውጭ የሚገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎች እና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው መሆኑን ከሚኒስቴሩ ማህበራዊ ገጽ ያኘነው መረጃ ያመለክታል።

እንዲሁም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ ነፃ እንደሚደረጉም ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በታክስ ማሻሻያው መሰረት የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን በተመለከተም ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ መደረጉን ሚኒስቴሩ ገልጿል

በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን በተመለከተም 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ ደግሞ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን፤ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ መወሰኑንም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ መኪናዎችን በኢትዮጵያ ጎዳናዎች ላይ መታየት ከጀመሩ ዋል አደር ያሉ ሲሆን፤ ግሪን ቴክ አፍሪካ የተባለ ኩባያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን በኢትዮጵያ መገጣጠም ሊጀምር መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚይ ኢንጅነር ቅደም ተስፋዬ ከወራ በፊት ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ አሁን ለይ ከ320 በላይ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት መቻሉን አስታውቀው ነበር።

የተሸከርካሪዎቹ ዋጋ በነዳጅ ከሚሰሩት መኪኖች ጋር ተቀራራቢና እኩል እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የጉምሩክ፣ ሱርታክስታና ተጨማሪ እሴት ታክስ ባይኖር ግን ዋጋቸው ከዚህ ይቀንስ እንደነበር መግለጻቸው ይታወሳል።

News today, Politics

አረብ ኤምሬትስን ጨምሮ 5 ተጨማሪ የዓለማችን ሀገራት የሻንጋይ ትብብር ድርጅትን ተቀላቀሉ

ግብጽ፣ አረብ ኢምሬትስ፣ ኳታር ፣ ባህሬን እና ኩዌት ድርጅቱን በአጋርነት ተቀላቅለዋል

የምስራቅ ሀገራት ስብስብ የሆነው የሻንጋያ ትብብር ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ በኡዝበኪስታን ተካሂዷል

በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት የሚመራውን የዓለም ተጽዕኖ ለመመከት የተቋቋመው የሻንጋይ ትብብር ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤውን በኡዝበኪስታን አካሂዷል።

በሳመርካንድ ከተማ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የቻይና፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ኢራን፣ ቱርክ እና ሌሎችም ሀገራት ፕሬዝዳንቶች እና ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተሳትፈውበታል።

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድርጅቱን በአጋርነት ተቀላቀሉት የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ ግብጽ፣ ኳታር ፣ ባህሬን እና ኩዌት እንኳን ደህና መጡ ብለዋል።

ቤላሩስን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ሀገራት ወደዚህ ድርጅት ለመቀላቀል ፍላጎት እያሳዩ ሲሆን ኢራን በይፋ ድርጅቱን መቀላቀሏም ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ፑቲን በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር የሻንጋይ ትብብር ድርጅት የዓለምን ችግር ለመፍታት የተቋቋመ እንጂ ቡድን የመመስረቻ መድረክ አይደለም ብለዋል።

ለዓብነትም ድርጅቱ የዓለም ምግብ ችግሮችን፣ ሽብርተኝነትን እና የህይል እጥረቶችን ለመፍታት ይሰራል ሲሉም ፕሬዝዳንት ፑቲን አክለዋል።

በአፍሪካ፣እስያ እና ደቡብ አሜሪካ ሀገራት መካከል በራሳቸው በብሄራዊ የመገበያያ ገንዘባቸው ሰፊ የንግድ ልውውጥ መፍጠር የድርጅቱ ዋነኛ አላማ እንደሆነም ተገልጿል።

ሞስኮ በዩክሬን በጀመረችው ጦርነት ምክንያት ማዕቀቦች እንደተጣሉባት የገለቱት ፕሬዝዳንት ፑቲን ከ300 ሺህ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ያለምንም ክፍያ ለታዳጊ ሀገራት እንደምታሰራጭም ተናግረዋል።

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ በበኩላቸው ቤጂንግ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩዋን እርዳታ ለታዳጊ ሀገራት የሰብዓዊ ድጋፎችን እንደምታደርግ በጉባኤው ላይ ገልቷል።

ሻንጋይ የትብብር ድርጅት በፈረንጆቹ 2001 ላይ በቻይናዋ ሻንጋይ የተቋቋመ ሲሆን ኡዝቤኪስታን፣ ቻይና፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ፓኪስታን፣ ታጂኪስታን፣ ኪርጊስታን፣ እና ካዛኪስታን ደግሞ መስራች ሀገራት ናቸው።

አፍጋኒስታን፣ ኢራን፣ ቤላሩስ እና ሞንጎሊያ በታዛቢነት ድርጅቱን የተቀላቀሉ ሲሆን አርመኒያ፣ አዛርባጂያ፣ ቱርክ፣ ስሪላንካ፣ ቻምቦዲያ እና ኔፓል ደግሞ ድርጅቱን ለመቀላቀል በሂደት ላይ እንደሆኑ ተገልጿል።

ከዓለማችን ህዝብ ቁጥር ውስጥ ግማሽ ገደማ የሖነው በዚህ ድርጅት ውስጥ በመደራጀት ላይ ሲሆኑ የድርጅቱ ሊቀመንበርነትን አባል ሀገራቱ በዙር እየመሩት ይገኛሉ።

የኡዝቤኪስታን ፕሬዝዳንት ሻቭካት ሚርዚቭ የወቅቱ የሻንጋይ የትብብር ድርጅትን በሊቀመንበርነት በመምራት ላይ ይገኛሉ።

News today, Politics, social life

ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ፤ “ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን ማቅረብ በሞራል ደረጃ ተቀባይነት ያለው ነው” አሉ

አባ ፍራንሲስ፤ እራስን መከላከል ህጋዊ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ “ለሀገሩ ያለውን ፍቅር መግለጫ ነው” መሆኑም ተናግረዋል

ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ፤ የዩክሬን ጦርነት ራስን ለመከላከል የሚደረግ “ፍትሃዊ ጦርነት” ነው ብለዋል

የዓለም ካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ፤ ራሷን በመከላከል ላይ ላለችው ዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን ማቅረብ “በሞራል ደረጃ ተቀባይነት ያለው ነው” አሉ።

ሊቀ ጳጳሱ ይህን ያሉት ከሶስት ቀን የካዛኪስታን ቆይታ ሲመለሱ በአውሮፕላን ውስጥ ሆነው በነበረቻው 45 ደቂቃ የፈጀ ቃለ ምልልስ ላይ ከአንድ ጋዜጠኞች “ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ መላካችው ትክክል ነው?” ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ነው።

አባ ፍራንሲስም “ይህ ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው ፤ ነገር ግን መርሆችን ባከበረ መልኩ የሚደረግ ከሆነ ከሞራል አኳያ ተቀባይነት ያለው ውሳኔ ነው” ብለዋል።

የዩክሬን ጦርነት ራስን ለመከላከል የሚደረግና በመርህ ደረጃም “ፍትሃዊ” የሚባል ጦርነት መሆኑ ለዚህም የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሃሳባቸው እንድትጋራ የሚያስችል ማብራሪያም መስጠታቸውም ሮይተርስ ዘግቧል።

“እራስን መከላከል ህጋዊ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር መግለጫ ነው” ሲሉም አክለዋል። ሊቀ ጳጳሱ የሩሲያ – ዩክሬን ጦርንት እንዲያበቃ ምኞታቸው መሆኑንም ገልጸዋል።

ጦርነቱ እንዲቆም “ዩክሬን ለውይይት ክፍት እንድትሆን” የጠየቁት ሊቀ ጳጳሱ፤ በቅርቡ ከዩክሬን ጋር ምንም ዓይነት የድርድር ተስፋ እንደማይኖር ስለገለጸችው ሩሲያ ግን ያሉት ነገር የለም።

ያም ሆኖ ሊቀ ጳጳስ ፍራሲስ፤ ከሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሞስኮ ተገናኝቶ ለመምከር ፍላጎት እንዳላቸው ባሰለፍነው ግንቦት ወር አስታውቀው እንደነበር አይዘነጋም።

ሊቀ ጳጳሱ፤ ከጣሊያኑ ኮሬ ዴላ ሴራ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ ወደ ሞስኮው መምጣት እፈልጋለሁ ሲሉ ለፑቲን መልዕክት መላካቸውንም ተናግረው ነበር።

መልዕክቱ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት በተጀመረ በ20ኛው ቀን የተላከ መሆኑንም ነበር ሊቃ ጳጳስ ፍራንሲስ የተናገሩት።

የዓለም ካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ጥያቄ ብያቀርቡም፤ በክሬምሊን ባለስልጣነት በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።

News today, social life

ደቡብ ሱዳን ነዳጅ ወደ ውጭ ለመላክ ጅቡቲ ወደብ ላይ ቦታ መግዛቷ አስታወቀች

የደቡብ ሱዳን መንግስት የነዳጅ ሚኒስትር ከፖርት ሱዳንና ሞምባሳ በተጨማሪ ጅቡቲን እንጠቀማለን ብለዋል

ደቡብ ሱዳን አሁን ላይ ነዳጅ የምትልከው “ፖርት ሱዳንን በመጠቀም ብቻ” መሆኑ ይታወቃል

ደቡብ ሱዳን ድፍድፍ ዘይትን ወደ ውጭ ለመላክ የጅቡቲ ወደብ እንደ አማራጭ መጠቀም እንደምርፈልግ አስታወቀች፡፡

የደቡብ ሱዳን መንግስት የነዳጅ ሚኒስትር ፉት ካንግ ኩል በነዳጅ ጉዳይ እየመከረ ባለውና የጅቡቲው የኢነርጂ እና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስትር ዩኑስ አሊ ጌዲ በተገኙበት የጁባው ኮንፈረንስ እንደተናገሩት ደቡብ ሱዳን ነዳጅን ወደ ውጭ ለመላክ እና እቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በጅቡቲ ወደብ ላይ 12 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ገዝታለች ብሏል፡፡

 “እኛ ፖርት ሱዳን እና ሞምባሳን ብቻ ስንጠቀም ቆይተናል ነገር ግን በቅርቡ ወደ ጅቡቲ ለመሄድ ወስነናል” ሲሉም አክለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጀምስ ሞርጋ ለአል ዐይን አማርኛ እንደናገሩት “በሞምባሳ በኩል ነዳጅ መላክ አንችልም፤ ስለዚህም ጅቡቲን መጠቀም ግድ ይለናል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን ነዳጅ ለመላክ መሰረተ ልማት ወሳኝ በመሆኑ በቅድሚያ “ከደቡብ ሱዳን-አትዮጵያ እስከ ጅቡቲ የሚያገናኘው መስመር መዘርጋት አለበት”ም ብለዋል አምባሳደሩ፡፡

ደቡብ ሱዳን፤ በሱዳን የተፈጠረውን የፖለቲካ አለመረጋጋት ተከትሎ ፖርት ሱዳንን በመጠቀም ነዳጅ ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ለማቆም ተገዳ የነበረ ቢሆንም፤ አንጻራዊ ሁኔታ መፈጠሩን ተከትሎ አሁን ፖርት ሱዳን ብቸኛ ነዳጅ የምትልክበት ወደብ አድርጋ በመጠቀም ላይ ትገኛለች፡፡

ደቡብ ሱዳን ኢኮኖሚዋ በነዳጅ ንግድ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ይታወቃል፡፡ 

News today, Politics

ጀርመን በአውሮፓ ግዙፍ ሆነ የታጠቀ ጦር ለመገንባት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

የጀርመኑ መሪ ኦላፍ ሾልዝ የአውሮፓ ሀገራት በኔቶ ጥላ ስር ሆነው ኃላፊነታቸው እንዲወጡ አሳስበዋል

የሩስያ-ዩክሬን ጦርነት ጀርመን የመከላከያ ፖሊሲዋን እንድትለውጥ አስገድዷል

የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው የአውሮፓን ጸጥታ ለመምራት የሚያችላት ግዙፍ ሆነ የታጠቀ ጦር ለመገንባት ዝግጁ ነች አሉ፡፡

ኦላፍ ሾልዝ፤ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ፊት ባደረጉት ንግግር “ጀርመን ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ያላትና በአህጉሪቱ መሃል ያለች ሀገር እንደመሆኗ፤ ሰራዊታችን በአውሮፓ ውስጥ የመደበኛ መከላከያ የማዕዘን ድንጋይ መሆን አለበት” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የሩስያ-ዩክሬን ጦርነት ፤ ጀርመን በመከላከያ ፖሊሲዋ ላይ ለውጥ በማድረግ ጦሯን ይበልጥ ለማጠናከር የ100 ቢሊዮን ዩሮ ልዩ ተጨማሪ ፈንድ ለማድረግ ያስገደደ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር ጀርመን በወዳጆቿ የተከበበች ሀገር ናት የሚል የተሳሳተ እምነት እንደነበራቸው ያነሱት ኦላፍ ሾልዝ፤ ጀርመን ከራሷ አልፎ የአውሮፓን ደህንነት የሚያረጋጋ ጦር የመገንባቷ ጉዳይ ግድ መሆኑም አንስተዋል፡፡

“ጀርመን ለአህጉራችን ደህንነት የመሪነት ሀላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን በግልጽ እና በታማኝነት እያሳየን ነው” ብለዋል ኦላፍ ሾልዝ።

ኦላፍ ሾልዝ፤ የአውሮፓ ሀገራት በሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ጥላ ስር ሆነው የበለጠ ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል።

“እኛ አውሮፓውያን በኔቶ ውስጥ የበለጠ ሀላፊነት መውሰድ አለብን፤ ዘመናዊ እና ብቃት ያለው ጦር ያሏቸው ሁለቱ የአውሮፓ ሀገራት ፊንላንድ እና ስዊድን በቅርቡ ወደ ኔቶ መቀላቀላቸው በጣም ጥሩ ነው” ማታቸውም ዩሮ ኒውስ ዘግቧል፡፡

 ኦላፍ ሾልዝ ባለፈው አመት በአፍጋኒስታን እንደነበረው እንደ ኢራቅ ፣ ማሊ እና ኒጀር በመሳሰሉና የአውሮፓ ምክር ወይም የስልጠና ተልእኮዎችን የሚያስፈልጋቸው ሀገራት ላይ ተልእኮዎችን ለመወጣት የሚያስችሉ “የአውሮፓ ዋና መስሪያ ቤቶች” ማቋቋም እንደሚደግፉም ተናግረዋል፡፡

ለዩክሬን ወታደራዊ ድጋፍ ለመላክ ዘግይተዋል ተብለው ሲተቹ የነበሩት የጀርመኑ መራሄ መንግስት፤ አሁን ላይ ለኪቭ የሚያደርጉት ድጋፍ አጠናክረው መቀጠላቸው የሚታወቅ ነው፡፡

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸውም ይታወሳል።

ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ መግለጻቸውም አይዘነጋም

News today, Technology

በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር የሚጓዘው በራሪ ሞተር ሳይክል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ አዲስ በራሪ ሞተር ሳይክል ይፋ አድርጓል

በራሪው ሞተር ሳይክል በቀጣዩ 2023 ለገበያ ይቀርባል ተብሏል

የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የዓለማችን የመጀመሪያው በራሪ ሞተር ሳይክል ከሰሞበኑ ይፋ አድርጓል።

በአሜሪካ ዴትሮይት እየተካሄደ ያለው አውቶሞቲቭ ሾው ላይ የቀረበው በራሪው ሞተር ሳይክል የበርካቶችን ቀልብ ይዟል።

በራሪ ሞተር ሳይክሉን የጃፓኑ ዚቱሪስሞ ኩባንያ የሰራው ሲሆን፤ ሞተር ሳይክሉ ለ40 ደቂቃ ያክል አየር ላይ መብረር ይችላል።

ዚቱሪስሞ በራሪ ሞተር ሳይክሉ በሰዓት እስከ 100 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መብረር የሚችል መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል።

የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ ኩባንያው ከበራሪ ሞተር ሳይክል በተጨማሪ ድሮኖች እና በራሪ መኪናዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ በጃፓን መሸጥ ጀምሯል ያሉት ስራ አስፈጻሚው፤ በአሜሪካ እና በሌሎች የዓለም ሀገራት ከ2023 ጀምሮ ለገበያ ይቀርባል ብለዋል።

አዲሱ በራሪ ሞተር ሳይክል አሁን ላይ የተገመተለት ዋጋም 777 ሸህ ዶላር ነው።

8የኩባንያው ስራ አስፈጻሚ ሹሄሂ ኮማስቱ፤ እስከ ፈረንጆቹ 2025 ባለው ጊዜ በኤሌክትሪ የሚሰራውን በራሪ ሞተር ሳይክል ዋጋ ወደ 55 ሺህ ዶላር የመቀነስ ተስፋ እንዳለ አስታውቀዋል።

News today, Politics

አራን፤ በሩሲያ እና ቻይና የሚመራውን የጸጥታ ጥምረት ልትቀላቀል ነው

ኤስሲኦ ተሰኘው የጸጥታ ቡድን የተመሰረተው በፈረንጆቹ 2011 ነበር

በአሜሪካ የሚደገፈው የአረብ-እስራኤል ጥምረት ኢራን ከሩሲያ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት እንድትመሰርት ገፋፍቷታል ተብሏል

የአሜሪካን የኢኮኖሚ ማእቀብ ለመቋቋም ጥረት እያደረገች ያለችው ኢራን በሩሲያ እና በቻይና የሚመራው የሴንትራል እሲያ የጸጥታ አካል ቋሚ አባል ለመሆን ቀርባለች፡፡

ባለፈው ሃሙስ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አሚርአብዶላሂያን ስብሰባውን በዚህ ሳምንት ያካሄደውን የሻንጋይ ኮኦፐሬሽን ድርጅት(ኤስሲኦ) ለመቀለቀል የሚያስችል መግባባቢያ ሰነድ መፈረማቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በፈረንቹ 2001 የተቋቋመው በሩሲያ እና ቻይና የነበረ ሲሆን ከተመሰረተ ከአራት አመት በኋላ ህንድ እና ፓኪስታንን አካቷል፤ ይህም በቀጣናው ያለውን የምእራባውያን ጫና ለመቋቋም አላማ ያደረገ ነበር፡፡

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢንስታግራም ገጻቸው እንደጻፉት ኢራን የኤስሲኦ ሙሉ አባል ለመሆን በመፈረም፣ ኢራን የኢኮኖሚ፤የንግድ እና የኢነርጅ ትብብር የምታደርግበት አዲስ ምእራፍ ውስጥ ገብታለች ሲሉ ጽፈዋል፡፡

የኢራን ፕሬዝደንት ኢብራሂም ሬኢሲ በኡዝቤክስታን የተካሄውን የተካፈሉ ሲሆን በወቅቱም ከሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን ጋር ተገናኝተው የነበሩ መሆኑን የኢራን ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡

አውዛጋቢ በሆነው የኢራን የኑክለር ጉዳይ ምእራባውያን የጣሉባትን መእቀብ የምትቋቋምበትን መንገድ የኤስሲኦ አባልት እንዲረዷት መጠየቋን ተከትሎ ነበር ወደ ቡድኑ እንድትገባ የተፈቀደላት፡፡

 ያእደገ የመጣው ማእቀብ እና በአሜሪካ የሚደገፈው የአረብ-እስራኤል ጥምረት የኢራኑን መሪ ከሩሲያ ጋር ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት እንድትመሰርት እንደገፋፋቸው ዘገባው ጠቅሷል፡፡

“ኢራን ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ከኢኮኖሚ እስከ ኤሮስፔስ እና የፖለቲካ ዘርፎች ለማሳደግ ቆርጣ ተነስታለች” ሲሉ ራይሲ ለፑቲን በስብሰባቸው ወቅት ተናግረዋል።

“በቴህራን እና በሞስኮ መካከል ያለው ትብብር በአገሮቻችን ላይ በዩኤስ ማዕቀቦች ላይ የተጣለውን ውስንነት በእጅጉ ያስወግዳል”ብለዋል።

News today, social life

ስደተኞችን በግል ጄት ጭነው አውሮፓ ያሻገሩ ተከሰሱ

የቤልጂየም ፖሊስ ሁለት ጄቶችን ይዟል።
የምስሉ መግለጫ,ስደተኞቹ ሐሰተኛ የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ታድለዋል

15 መስከረም 2022

የግል ጄት በመጠቀም ስደተኞችን ወደ ምዕራብ አውሮፓ ያሻገሩ አምስት ሰዎች ተከሰሱ።

አምስቱ ሰዎች የተከሰሱት በጣሊያን ፍርድ ቤት ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ስደተኞቹን ወደ አውሮፓ በግል አውሮፕላን ጭነው ያስገቡት ለሰዎቹ ሐሰተኛ የዲፕሎማት ፓስፖርት ካደሏቸው በኋላ ነው ተብሏል።

ፓስፖርቱ የካሪቢያን ደሴት የሆነችው ሴንት ኪተስ ኤንድ ኔቪሰ እንደሆነ ተመላክቷል።

የግል አውሮፕላኑ እነዚህን ስደተኞች ከቱርክ ከጫናቸው በኋላ በአንድ የአውሮፓ አገር አየር ማረፊያ አራግፈዋቸዋል።

በዚያም ግለሰቦቹ እውነተኛ ማንነታቸውን በመግለጽ የጥገኝነት ጥያቄን አቅርበዋል።

ፖሊስ እንደሚለው እነዚህን ግለሰቦች በግል ጄት ጭኖ አውሮፓ ለማስገባት ተጠርጣሪው ቡድን ከእያንዳንዳቸው 10ሺህ ዩሮ ሳይቀበል አልቀረም።

ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው ከተጠረጠሩት አምስት ግለሰቦች መሀል ሦስቱ በሮምና በብራስልስ ከተሞች ተይዘዋል።

ሁለቱ አሁንም በፍለጋ ላይ ናቸው።

 ከተጠርጣሪዎቹ አንዱ ጣሊያናዊ ሲሆን ሦስት የግብጽ ዜጎችና አንዲት ቱኒዚያዊት ሴት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፖሊስ ኃላፊ የሆኑት ኮስታንቲኖ ስኩዲየር ለሮይተርስ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ የሌላ ግዙፍ ሕገ ወጥ የስደተኛ አሸጋጋሪ ቡድን አባላት እንደሆኑ ግምት በመውሰድ ክስ ተመሥርቶባቸዋል።

ወንጀለኞቹን አድኖ በመያዙ ረገድ ቤልጅየም፣ ጀርመን፣ ኦስትሪያ፣ ፈረንሳይ እና የአሜሪካ የጸጥታና ደኅንነት አካላት እገዛ እንዳደረጉ ተነግሯል።

News today, Politics

ኪም ጆንግ ኡን የሰሜን ኮሪያን “የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር” ሲሉ አወጁ

የሀገሪቱ ፓርላማ በአደጋ ወቅት በጠላት ኢላማዎች ላይ የኒውክሌር ጥቃት እንድትፈጽም የሚፈቅ ህግ አጽድቋል

በኒውክሌር ጉዳይ ድርድር የለም ያሉት ኪም ጆንግ ኡን “ሰላም ሊገኝ የሚችለውም በኃይል ብቻ ነው” ብለዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸውን “የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር” ሆናለች ሲሉ አወጁ፡፡

ኪም ጆንግ ኡን ሊቀለበስ የማይችል ነው ባሉት ውሳኔያቸው፤ ሀገራቸው የኒውክሌር የታጠቀች ሀገር የሆነችበትን አዲስ ህግ ይፋ አድርገዋል።

” ሀገራችን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ሆናለች” ብለዋል ኪም ጆንግ ኡን።

“በአዲሱ ህግ መሰረት የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቻችን ጉዳይ መደራደር የማይታሰብ ነው፤ ሰላም ሊገኝ የሚችለውም በኃይል ብቻ ነው” ሲሉም አክለዋል፡፡

“ሀገራችንን ከኒውክሌር ነፃ ለማድረግ ምንም አይነት ድርድር አይኖርም” ሲሉም ነው የተደመጡት ኪም ጆንግ ኡን፡፡

የሀገሪቱ ፓርላማም ዛሬ ረፋድ ላይ ሀገሪቱ አደጋዎች በሚጋረጡባት ወቅት በጠላት ኢላማዎች ላይ የኒውክሌር ጥቃትን እንድትጀምር የሚፈቅደውን ህግ አጽድቋል፡፡

በዚህም ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መያዝን እንደ ህጋዊ ጉዳይ ፣አስፈላጊና መሰረታዊ መብት አድርጋ በመመልከት ባጸደቀችው አዲስ ህግ ራሷን “የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ያላት ሀገር” መሆኗ አውጃለች ሲል የኮሪያ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡

ነገር ግን በአዲሱ ህግ መሰረት የኒውክሌር ጦር መሳሪያን ከማንም ጋር እንደማትጋራ እንዲሁም የአቶሚክ ቴክኖሎጂ እና ቁሳቁስ እንደማታስተላልፍም አስታውቃለች።

ሰሜን ኮሪያ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኒውክሌር ሙከራ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።

እንደፈረንጆቹ በ2018 የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕና ሌሎች መሪዎች ሰሜን ኮሪያ ኒውክሌር ማበልጸጓን እንድትተው ኪም ጆንግ ኡንን ለማሳመን ያደረጉት ጥረት እንዳልተሳካ የሚታወስ ነው፡፡

News today, Politics

ከ80 በመቶ በላይ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በተሳሳተ መንገድ ላይ እንዳለች ያምናሉ ተባለ

እድሜያቸው 55 እና ከዛ በላይ የሆኑ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ ናት ብለው ያምናሉ ተብሏል

የአሜሪካው ሞንማውዝ የተሰኘው ዩንቨርስቲ በአሜሪካ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያጠናውን ጥናት ይፋ አድርጓል

ከ80 በመቶ በላይ አሜሪካዊያን ሀገራቸው በተሳሳተ መንገድ ላይ እንዳለች እንደሚያምኑ ጥናት አመለከተ።

የአሜሪካው ሞንማውዝ ዩንቨርስቲ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ አሜሪካዊያን አሁን ባለው አስተዳድር  ላይ ያላቸውን አመለካከት ለማወቅ ጥናት አካሂዷል

በዚህ ጥናት ላይ 978 ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን በጥናቱ ከተሳተፉ ሰዎች መካከል ከ80 በላይ ያህሉ አሜሪካ በተሳሳተ መንገድ እየተጓዘች እንደሆነ ያምናሉ።

በጥናቱ ከተሳተፉት ውስጥ እድሜያቸው 55 እና ከዛ በላይ ከሆናቸው ሰዎች ውስጥ 16 በመቶዎቹ ግን ሀገራቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ መሆኗን ያምናሉ ሲል ዘ ሂል የተሰኘው የአሜሪካው ሚዲያ ዘግቧል።

በዚህ ጥናት መሰረት አሜሪካ በታሪኳ በህዝቧ ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው የጥናት ውጤት አሳይታለች ተብሏል።

ዩንቨርሲቲው ግንቦት ወር ላይ ተመሳሳይ ጥናት ማካሄዱ የተገለጸ ሲሆን በሀምሌ ወር ላይ የተገኘው የጥናት ውጤት ግን ሀገራቸው በተሳሳተ ጎዳና ላይ እንደሆነች የሚያምኑ አሜሪካዊያን ቁጥር በ9 በመቶ ጨምረዋል።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንእና ካቢኔያቸው

የጥናቱ ተሳታፊዎች ከመላው የአሜሪካ ግዛቶች የተካተቱ ሲሆን በዚህ ጥናት መሰረት አሜሪካ በታሪኳ ከፍተኛው ችግር ላይ ትገኛለች ተብሏል።

በትናቱ ከተሳተፉ ሰዎች ውስጥ 92 በመቶ የሚሆኑት የሪፐብሊካን ፓርቲ ደጋፊዎች አሜሪካ በተሳሳተ መንገድ ላይ ነች ብለው ያምናሉም ተብሏል።

በጥናቱ ከተሳተፉ የሪፐብሊካን ፓርቲ ደጋፊዎች ውስጥ 6 በመቶዎቹ ብቻ ሀገራቸው በትክክለኛውም መንገድ ላይ ናት የሚል አመለካከት እንዳላቸው ተገልጿል።

በአሜሪካ የጋዝ ምርቶች ዋጋ ማሻቀብ፣ እና የኑሮ ውድነቱ የአሜሪካዊያን ዋነኛ የወቅቱ ችግር እንደሆነም በጥናቱ የተሳተፉ ሰዎች ተናግረዋል።

ይሄንንም ተከትሎ በጥናቱ ከተሳተፉ አሜሪካዊያን ውስጥ 38 በመቶ የሚሆኑ አሜሪካዊያን በቅርቡ የሚካሄደውን የኮንግረስ ምርጫ ዲሞክራቶች እንዲቆጣጠሩት ሲፈልጉ 36 በመቶዎቹ መላሾች ደግሞ ኮንግረሱን ሪፐብሊካኖች እንዲይዙት እንደሚፈልጉም ጥናቱ ያሳያል።

News today, Politics

ዶላርን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው-ፑቲን

ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ተስማምታለች

ከዓለም ዙሪያ

2022/9/12 13:28 GMT

ፕሬዝደንት ፑቱን

ሩሲያ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት መስማማቷ ይታወሳል

ዶላን ከገበያ የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ፕሬዝደንት ፑቲን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝደንት ፑቱን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ንግግር ባሰሙበት ወቅት ሩሲያ ከምእራባውያን የተሰነዘሩባትን መእቀቦች መቋቋም መቻሏን መግጻቸውን የሩሲያው አርቲ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ማእቀቦቹን የተቋቋመችው የተለያዩ የመከላከያ መንገዶችን በመጠቀም ነው ብለዋል ፑቲን፡፡

በቀጣይ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎች ላይ የተናገሩት ፑቲን ዶላርን ከመገበያያነት የማስወጣት እንቅስቃሴ የማይቀር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ላይ “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ አሜሪካን ጨምሮ ምእራባውያን በሺዎች የሚቆጠሩ ማእቀቦችን ጥለውባታል፡፡ ሩሲያ ከጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከበርካታ ሀገራት ጋር በሩብል ለመገበያየት ከስምምነት መድረሷ ይታወሳል፡፡

ሩሲያ ምእራባውያን ለሚገዙት ጋዝ በሩሲያ ገንዘብ ሩብል እንከፍሉ በማድረግ እና ከዚህም አለፍ ሲል የጋዝ ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዝጋት በምእራባውያን ሀገራት የአጸፋ እርምጃ ወስዳለች፡፡ በቅርቡ ለጥገና በሚል የዘጋችው ጋዝን ከሩሲያ ወደ ጀርመን የሚደውስደው ኖርድ ስትሪም 1 የተሰኘውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር እንደማትከፍት መግለጽ ይታወሳል፡፡

ጀርመን በሩሲያ ውሳኔ በእጅጉ አዝናለች፡፡

ሩሲያ እውቅና የሰጠቻቸው ሉሃንስክ ግዛት አሁን ሙሉበሙሉ ነጻ የወጣ ሲሆን የዶምባስ ግዛትን ሙሉ ለሙሉ ነጻ ለማውጣት ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡፡

ዩክሬን በቅርቡ በሩሲያ ሃይሎች ላይ ድል በመቀዳጀት የተወሰኑ ቦታዎች ማስለቀቋን እየገለጸች፤ ነገርግን ሩሲያ ቦታ የለቀቀችው ጦሯን በደንብ ለማደራጀት ነው ብላለች፡፡

News today, Technology

ሚሳዔልና ተተኳሽ ቦምቦችን ጭኖ በሰዓት ከ2 ሺህ ኪ.ሜ በላይ የሚበረው “ሚኮያን ሚግ-35” ጄት

ሚኮያን MIG-35 ሩሲያ ካሏት አደገኛ የጦር ጄቶች ውስጥ አንዱ ነው

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት

እስከ ከ300 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ የሚገኙ የባሀር ላይና የአየር ላይ ጠላት ኢላማዎችን መለየት ይችላል

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት ሩሲያ ካሏት ጦር የውጊያ ጄቶች ውስጥ በአደገኛነቱ እና በፈጣንነቱ ብዙ ይነገርለታል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት በፈረንጆቹ 2007 የተመረተ ሲሆን፤ ሩሲያ አሁን ላይ ከዩክሬን ጋር ከገጠመችው ጦርነትን ጨምሮ በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ እንተጠቀመችበት ኤር ፎርስ ቴክኖሎጂ ድረ ገጽ አስነብቧል።

ተዋጊ ጄቱ ክሊሞቭ አር ዲ 33 MK የሚል መጠሪያ ያለው ሁለት ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ከመሬት ለመነሳት 122 ሜትር የመንደርደሪያ፤ ለማረፍ ደግሞ 137 ሜትር ርዝመት ቦታ ያስፈልገዋል።

በሰዓት ከ2 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ አየር ላይ የሚከንፈው ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት፤ በአንድ ጊዜ በተሞላለት ነዳጅ ከ3 ሸህ ኪሎ ሜትሮች ባለይ፤ እዛው አየር ላይ ነዳጅ ተከሞላለት ደግሞ ከ5 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ መጓዝ እንደሚችል ታውቋል።

ተዋጊ ጄቱ ፀረ መርከብ እና ፀረ አውሮፕላን ሚሳዔሎችን ጨምሮ የተለያዩ ተተኳሽ ቦምቦችን የመታጠቅ አቅም ያለው እንደሆነ ይነገራል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት ከሚታጠቃቸው እና ከሚያስወነጭፋቸው መሳሪያዎች መካከልም ሚግ-35 Kh-29TE ሚሳኤል እና KAB-500Kr TV ቦምቦች ተጠቃሽ ናቸው።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት አየር ክልልን ጦሶ የገባን የጠላት አውሮፕላን ከ160 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መለየት እንደሚችልም ኤር ፎርስ ቴክኖሎጂ ድረ ገጽ መረጃ ያመለክታል።

ታዲያ ይህ የጦር ጄት የአየር ክልል ጥሶ የገባን የጠላት አውሮፕላን ሚግ-35 Kh-31P ፀረ-ራዳር ሚሳኤል በመጠቀም የሚያወድም መሆኑ ተነግሯል።

ሚኮያን MIG-35 ተዋጊ ጄት በተጨማሪም የሀገርን የውሃ ክልል ጥሶ የገባን መርከብ ከ300 ኪሎ ሜትር ላይ የመለየት ብቃት ያለው ሲሆን፤ አስፈላጊ ሆኖ ከገተኘ Kh-31A ፀረ-መርከብ ሚሳኤል በማስወንጨፍ መምታት ይችላል ተብሏል።

News today, Politics

ለንግሥት ኤልዛቤጥ ቀብር የቻይና መንግሥት መጋበዙ የምክር ቤት አባላትን አስቆጣ

በዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ ሥርዓተ ቀብር ላይ የቻይና መንግሥት ተወካዮች እንዲገኙ የቀረበው ግብዣ እንዲሰረዝ የዩናይትድ ኪንግደም ፖለቲከኞች እና የምክር ቤት አባላት ጠየቁ።

የቻይና መንግሥት ተወካዮች በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ በዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) መንግሥት መጋበዛቸው አሳስቦናል በማለት ለአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ደብዳቤ ከጻፉት መካከል የወግ አጥባቂው ፓርቲ ጉምቱ አባላት ይገኙበታል።

የምክር ቤት አባላቱ በቻእና አነሳ በሆኑት ዊገር ሙስሊም ማኅብረሰብ አባላት ላይ “የዘር ማጥፋት” ወንጀል የሚያስጽሙት ባለሥልጣንት መጋበዛቸው አሳሳቢ ነው ብለዋል።

የፊታችን ሰኞ መስከረም 09/2015 ዓ.ም. በሚከናወነው የንግሥቲቱ ሥርዓተ ቀብር ላይ እንዲገኙ ለቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ይፋዊ ጥሪ የቀረበ ቢሆንም ፕሬዝዳንቱ ግን ይገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም።

ፕሬዝዳንቱ በዚህ ሳምንት ከሁለት ዓመታት በኋላ በመጀመሪያቸው በሆነው የውጭ አገር የሥራ ጉብኝት ጉዟቸው ወደ ካዛኪስታን እና ኡዝቤኪስታን አቅንተዋል።

የቻይናው ‘ሳውዝ ቻይና ሞርኒን ፖስት’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ምክትል ፕሬዝዳንት ዋንግ ኪሻን ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በንግሥቷ ቀብር ላይ ማን ይገኛል?

በንግሥቲቱ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ወደ 500 የሚጠጉ ርዕሳነ ብሔራት እና የውጭ አገር ተወካዮች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አብዛኞቹ መሪዎች በንግድ አውሮፕላን በረራዎች እንዲመጡ የተጠየቁ ሲሆን፤ ምዕራብ ለንደን ከሚገኝ ቦታ በአውቶብስ እንደሚጓጓዙም ተነግሯቸዋል ተብሏል።

በዕለቱ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከሚገኙት መካከል ከመላው አውሮፓ የሚመጡ ንጉሣውያን ቤተሰብ አባላት ይገኙበታል።

የቤልጂየም፣ የኔዘርላንድስ፣ የስፔን ነገሥታት የሚገኙ ሲሆን፣ የኖርዌይ፣ የስዊድን፣ የዴንማርክ እና የሞናኮ ንጉሣውያን ቤተሰቦችም በቀብሩ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

ከአገራት መሪዎች መካከል የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከእነ ባለቤታቸው በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደሚገኙ ዋይት ሐውስ አረጋግጧል።

ከኮመንዌልዝ አገራት መሪዎች መካከል የአውስትራሊ፣ የካናዳ እና የኒው ዚላንድ ጠቅላይ ሚንስትሮች ጥሪውን ተቀብለዋል።

የጀርመን፣ የጣሊያን፣ የፈረንሳይ፣ የደቡብ ኮሪያ፣ የብራዚል እና የቱርክ ፕሬዝዳንቶችም እንደሚገኙ ይጠበቃል።

ያልተገባዙትስ እነማን ናቸው?

ከሩሲያ፣ ከቤላሩስ እና ከሚያንማር በዩናይትድ ኪንግደም ንግሥት የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ የተጋበዙ ባለሥልጣንት የሉም።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በንግሥቲቱ ቀብር ላይ የመገኘት ዕቅድ እንደሌላቸው ቃል አቀባያቸው ቀደም ሲል ተናግረው ነበር።

ዩናይትድ ኪንግደም ከሶሪያ፣ ከቬንዙዌላ እና ከአፍጋኒስታን ጋር ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ስለሌላት ከእነዚህ አገራት በሥነ ሥርዓቱ ላይ የሚገኝ አይኖርም።

ሰሜን ኮሪያ፣ ኢራን እና ኒካራጉዋ ደግሞ አምባሳደሮቻቸውን ብቻ እንዲልኩ ተጋብዘዋል።

News today, Politics

የቻይናና የሩሲያ የባህር ኃሎች በፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ የውጊያ ልምምድ አካሄዱ

በሩሲያና በቻይና መርከቦች መካከል የመረጃ ልውውጥ እና የኢላማ ተኩስ የልምምዱ አካል ናቸው

የቻይናና የሩሲያ የባህር ኃሎች

የጦር ልምምዱ በሩሲያና በቻይና ባህር ኃሎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ነው

የቻይና እና የሩሲያ ባህር ኃይሎች በፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ ታክቲካዊ የውጊያ ልምምድ ማድረጋቸው ተገለፀ።

በጦር ልምምዱ ላይ የሩሲያ ባህር ኃይል አባላት ከቻይና አቻቸው ጋር የኮሙዩኒኬሽን እና ሌሎችም ወታደራዊ ልምምዶችን ማድረጋቸውን አር.ቲ ዘግቧል።

በልምመዱም በቻይና እና በሩሲያ የጦር መርከቦች መካከል ግንኙነት እንዴት መለዋወጥ እንደሚችል፣ የባህር ላይ የተኩስ ልምምድ እና የጦር መርከብ ሄሊኮፕተር ድጋፍ አሰጣጥ ላይ ልምምድ አድርገዋል።

የውጊያ ልምምዱ በቤጂንግ እና በሞስኮ የባህር ኃይሎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏ።

በተጨማሪም ልምምዱ የእሲያ-ፓስፊክ ቀጠናን ሰላም እና መረጋጋት ለማስጠበቅ እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ እንቅቃሴዎችን ለመጠበቅ ያለመ ነው።

የቻይና እና የሩሲያ ወታደሮች ከሳምንታት በፊት ሩሲያ አስተናጋጅነት በተካሄደው የቮሶቶክ 2022 ወታደራዊ ልምምድ ላይ የጋራ ልምምድ አድርገው እንደነበረ ይታወሳል።

በዚሁ ልምምድ ላይ የቻይና እና የሩሲያ ወታደሮች በጋራ ወታደራዊ የኢላማ ተኩስ ልምምድ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በዚህም የሩሲያ የፓስፊክ የባህር ኃይል እና የቻይና ባህር ኃይል ከጦር መርከቦች ላይ በመሆን የምድር ላይ ኢላማዎችን የመምታት የተኩስ ልምምድ አካሂደዋል ነው የተባለው።

በወቅቱም ቻይን ቻይና የጦር ልምምዱ ከወቅቱ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር እንደማይገናኝ መግለጿ ይታወሳል።

News today, Politics

ለዩክሬን የረጅም ርቀት መሳሪያ ማስታጠቅ ቀይ መስመርን ማለፍ ነው ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች

ዩክሬን የረጅም ርቀት ተተኳሽ የጦር መሳሪያ እንዲሰጣት ለአሜሪካ ጥያቄ አቅርባለች

የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 206ኛ ቀኑ ላይ ይገኛል

ለዩክሬን የረጅም ርቀት መሳሪያ ማስታጠቅ ቀይ መስመርን ነው ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች፡፡

ከስድስት ወር በፊት የተጀመረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ሀያላን ሀገራት ጎራ ለይተው ድጋፍ በማሰባሰብ ላይ ይገኛሉ፡፡

በዚህ ጦርነት ሩሲያ እንድትሸነፍ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የተለያዩ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን በማስታጠቅ ላይ ናቸው፡፡

ዩክሬንም ከነዚህ ሀገራት የሚደረግላትን የጦር መሳሪያ በመጠቀም በሩሲያ ተይዘው የነበሩ ቦታዎችን መልሳ በማስለቀቅ ላይ ስትሆን አሜሪካ የረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ የጦር መሳሪያዎች እንዲሰጧት ጠይቃለች፡፡

ሩሲያ በበኩሏ ለዩክሬን የረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ የጦር መሳሪያ ማስታጠቅ ማለት ቀይ መስመርን ማለፍ ነው ስትል አስጠንቅቃለች፡፡

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እንዳሉት አሜሪካ ለዩክሬን የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያ ካስታጠቀች ሞስኮ ራሷን ለመከላከል ስትል እርምጃ ትወስዳለች ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የአሜሪካ መከላከያ ዋና አዛዥ ሊዮድ ኦስቲን ሀገራቸው ለዩክሬን ተጨማሪ የ675 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው የጦር መሳሪያዎች ልትሰጥ እንደምትችል ተናግረዋል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው ከአሜሪካ እና ምዕራባዊያን በሚደረግላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በሩሲያ ጦር ተይዘው የነበሩ አካባቢዎችን እያስለቀቁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሩሲያ የተያዙ ሌሎች የዩክሬን ግዛቶችን ለማስለቀቅም የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያዎች እና ሌሎች አጋዥ መሳሪያዎች ድጋፍ እንዲደረግላቸው ለአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት ሀገራት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ለሰባት ወራት በዘለቀው የሩሲያ ጦርነት ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ወታደሮች እና ንጹሃን የተገደሉ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሀገራት እንደተሰደዱ ተመድ ገልጿል፡፡ 

News today, Politics, social life

ግብፅና ኳታር በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች በትብብር ለመስራት ስምምነት ተፈራረሙ

የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ ከ4 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር ጉብኝት አድርገዋል

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም

ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አለሲሲ እና የኳታ ኢሚር ታሚም በሁለትሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል

የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አል ሲሲ በኳታር ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ተገልቷል።

ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ ከአራት ዓመታት ወዲህ በሳለፍነው ማክሰኞ ለመጀመሪያ ጊዜ ዶሃ ሲደርሱም በኳታር ኢሚር ታሚም አቀባባበል ተደርጎላቸዋል።

በትናትናው እለትም የግብጹ ፕሬዝዳት አብዱልፈታህ አልሲሲ እና የኳታሩ ኢሚር ታሚም በሀገራ የሆለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተመካክረዋል።

በዚህም የኳታሩ ኢሚር ታሚም ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እንዲያደግ እየሰሩት ላው ስራ ማማስገናቸውን የኳታር የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል።

የፕሬዝዳንት አል ሲሲ ግብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናከር እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት አል ሲሲ በበኩላቸው፤ ግብጽ ከኳታ ጋር በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ እና በደህንነት ዘርፎች ከኳታር ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ውይይቱን ተከትሎም ሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ ዘርፎች ስምምነት የተካሄደ ሲሆን፤ ከስምምነቶቹ ውስጥም ልማትና ኢንቨስምንት እንዲሁም የማህበራዊ ዘርፍ ይገኝበታል።

News today, Politics

የስዊድኗ ጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ማግዳሊና አንደርሰን የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ ለፓርላማው አስገብተዋል

ጠቅላይ ሚኒስትሯ መልቀቂያ ያስገቡት ፓርቲያቸው በምርጫ መሸነፉን ተከትሎ ነው

የስዊድኗ ጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ ፡፡

ባለፈው እሁድ በስዊድን የህግ አውጪ ምክር ቤት ምርጫ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን ሀገሪቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነት የሚመሩት አንደርሰን ፓርቲ በምርጫው ተሸንፏል፡፡

ይሄንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትር አንደርሰን የግድ መንግስታቸውን አፍርሰው በምርጫው ላሸነፈው ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች ስልጣን ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም ጠቅላይ ሚኒስትር አንደርሰን ለሀገሪቱ ህግ አውጪ ምክር ቤት የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

የስዊድን ግራ ዘመመም ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የነበረውን ምርጫ አሸንፈፈው ጠቅላይ ሚኒስትር ማግደሊና አንደርሰንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሾመው የነበረ ሲሆን አሁን በተካሄደው ምርጫ ደግሞ ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች በጠባብ ልዩነት አሸንፈዋል፡፡

ግራ ዘመም ፓርቲዎች ምርጫውን 173 ለ176 ድምጽ ልዩነት የተሸነፉ ሲሆን የሞደሬት ፓርቲ መሪ የሆኑት ኡልፍ ክሪሰትረሰን አዲስ መንግስት እንደሚመሰርቱ ይጠበቃልም ተብሏል፡፡

ላለፉት 11 ወራት ስዊድንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት አንደርሰን የኑሮ ውድነት፣ የስደተኞች አያያዝ እና የግድያ ወንጀሎች መበራከት በምርጫው እንዲሸነፉ ዋነኛ ምክንያቶች እንደሆኑ ተገልጿል፡፡

የስዊድን ቀኝ ዘመም ፓርቲዎች በሀገራቸው አጥፊዎች ረጅም ዓመት የሚቆይ እስር እንዲፈረድባቸው ማድረግ ፣ስደተኞች ለሀገራቸው ደህንነት አደጋ በማይሆኑበት መንገድ እንዲያዙ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የምረጡኝ ቅስቀሳቸው ዋነኛ አጀንዳዎች ነበሩ፡፡

News today, Politics

ፑቲን፤ “ዓለምን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረገውን ሙከራ” እንደማይቀበሉ ለቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ገለፁ

ፕሬዝዳንት ዢ፤ ቻይና ከሩሲያ ጋር ለመስራት እንደምትፈልግ ለፑቲን አረጋግጠውላቸዋል

2022/9/15 16:52 GMT

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ

ፑቲን፤ ለቻይናው ፕሬዝዳንት “በዩክሬን ጉዳይ ያንጸባረቁትን ሚዛናዊ አቋም አደንቃለሁ” ብለዋል

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ “ዓለምን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረገው ሙከራ” እንደማይቀበሉ ለቻይናው አቻቸው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ገለጹ።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ቻይናው ዢ ጂንፒንግ የዩክሬን-ሩሲያ ከተጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በኡዝቤኪስታን መዲና ሳማርካንድ ተገናኝተዋል

ሁለቱ መሪዎች የሻንጋይ የትብብር ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የጎንዮሽ ውይይት አድርገዋል።

በዚህም ፑቲን “አንድ የማይታወቅ ዓለም ለመፍጠር የተደረጉ ሙከራዎች በቅርብ ጊዜ በጣም አስቀያሚ ቅርጽ እየያዙ ነው፤ እናም ፈጽሞ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው” ሲሉ ነው ለቻይናው አቻቸው መናገራቸውን ነው ሮይተርስ የዘገበው፡፡

የፑቲንን ኃሳብ የሚጋሩትና “የቀድሞ ጓደኛዬን” በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ ያሉት ፕሬዝዳንት ዢ በበኩላቸው ቻይና ከሩሲያ ጋር ለመስራት እንደምትፈልግ ለፑቲን አረጋግጠውላቸዋል።

አክለውም ቻይና “በተመሰቃቀለ ዓለም ውስጥ መረጋጋት እና አዎንታዊ ጉልበት ለማስፋፋት ትፈልጋለች ” ብለዋል።

በሌላ በኩል መሪዎቹ የዩክሬን አሁናዊ ሁኔታን አንስተው የተወያዩ ሲሆን ፤የቻይናው ፕሬዝዳንት የዩክሬን ጉዳይ እንደሚስስባቸው ለፑቲን መናገራቸውን ሮይተረስ ዘግቧል።

ዢ በዩክሬን ጉዳይ የተለያዩ ስጋቶችና ጥያቄዎች እንደነበራቸው እረዳለሁ ያሉት ፑቲን፤ የቻይናው መሪ በዩክሬን ጉዳይ ያንጸባረቁትን “ሚዛናዊ አቋም” እንደሚያደንቁ ገልጸውላቸዋል።

“ከዩክሬን ቀውስ ጋር በተያያዘ የቻይና ወዳጆቻችንን ላሳዩት ሚዛናዊ አቋም ትልቅ ክብር አለን” ሲሉም ነው ፑቲን ለዢ የገለጹላቸው።

መልካም የሚባል ግንኙነት እንዳለቸው የሚነገርላቸው መሪዎቹ በኡዝቤኪስታን ፊት ለፊት ሲገናኙ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወታደራዊ ዘመቻ ከጀመረች ወዲህ የመጀመሪያ ነው ተብሏል፡፡

በተለይም በኮሮና ምክንያት ኩፉኛ የተፈተነችው ሀገር መሪ ለሆኑት ለቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ የመጀመሪያ የባህር ማዶ ጉዞ መሆኑ ነው።

የመሪዎቹ መገናኘት ፤ በዩክሬን ጦርነት ምክንያት ዓለም ፊቱን ላዞረባት ሞስኮ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው እየተገለጸ ነው።

ሞስኮ እና ቤጂንግ በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ባለቸው ግንኙነት የቅርብ አጋሮች ሆነው ብቅ ያሉበት አጋጣሚ ተፈጥረዋል።

News today, Politics

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ የመኪና አደጋ ደረሰባቸው

ፕሬዝደንት ዘሌሰንኪ ወታደሮቻቸው በመልሶ ማጥቃት 2 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱን ተናግረዋል

ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ ጦራቸው ከሩሲያ ያስለቀቃቸውን ስፍራዎች ጎብኝተው ሲመለሱ ነው አደጋው ያጋጠመው

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ የመኪና ግጭት አደጋ እንደደረሰባቸው ቃል አቀባያቸው ይፋ አድርገዋል።

ፕሬዚዳንቱ በኪቭ ከተማ ውስጥ በእጀባ በመጓዝ ላይ እያሉ ያሉበት መኪና ከመንገደኛ መኪና ጋር መጋጨቱን የፕሬዝዳቱ ቃል አቀባይ ሰርጉ ነይክሪፎቭ ባጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ከአደጋው በኋላ ፕሬዝዳንቱ በዶክተሮች እንደታዩ እና ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው መረጋገጡንም ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

ከፕሬዝዳንቱ መኪናጋር የተጋጨው አሽከርካሪ በስፍራው የህክምና ክትትል ከተደረገለት በኋላ በአምቡላንስ ወዳልታወቀ ስፍራ እንደተወሰደም ቢቢቢ ዘግቧል።

የመኪና አደጋው ሁኔታ በህግ አስከባሪ አካላት ምርመራ እየተደረገበት መሆኑን ሰርጉ ነይክሪፎቭ አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ ጦራቸው ከሩሲያ ነጻ በማውጣት የተቆጣጠራትን ኢዚየም ከተማን ጎብኘተው ሲለመሱ እንደሆነም ታውቋል።

ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ ባሳለፍነው ሳምንት በሰጡት መገለጫ፤ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “2 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።

የዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ፤ እየተገኙ ያሉ ድሎች የዩክሬን ኃሎች የሩሲያ ጦርን ማሸነፍ እንደሚችሉ አማላካች ናቸው ብለዋል።

ጦርነቱ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ምዕራባውያንና የዩክሬን አጋሮች የሚያደርጉት የጦር መሳሪያ ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉበት ሲሉም ተማጽነዋል።

News today, Politics

የብሪታኒያ ንጉስ ርእሰ ብሄር የሆኑባቸው ሀገራት የትኞቹ ናቸው…ʔ

የብሪታኒያ ንግስ በዓለማችን ላይ ላሉ 15 ሀገራት ርእሰ ብሄር ናቸው

ሀገራቱ ሉዓላዊ ቢሆኑም የብሪታኒያ ጉስ ግን እስካሁን ድረስ ርእሰ ብሄራቸው ናቸው

የብሪታኒያ ንግስት ኤልሳቤጥ ከ70 ዓመታት የንግስና ዘመን በኋላ በ96 ዓመታቸው ማረፋቸው ይታወሳል።

ንጉስ ቻርልስ

ይህንን ተከትሎ የንግስት ኤልሳቤጥ የመጀመሪያ ልጅ ንጉስ ቻርልስ የንግስና ዙፋኑን ተረክበዋል።

በዚህም ንጉስ ቻርልስ ንግስት ኤላሳቤጥ በግንስና ዘመናቸው ከሀገራቸው በተጨማሪ ርእሰ ብሄር በነበሩባቸው ሀገራት ላይም ርእሰ ብሄር በመሆን ይመራሉ።

ሀገራቱ ከዚህ ቀደም የእንግሊዝ ቀኝ ግዛት የነበሩ ሲሆን፤ ከቀኝ ግዛት ከተላቀቁ በኋላም ግን ሀገራቱ የብሪታኒያ ንጉሳውያንን በሀገራቸው ርእሰ ብሄር አድረገው ሾመዋል።

የብሪታኒያ ንጉስ ርእሰ ብሄር የሆኑባቸው 15 ሀገራት የትኞቹ ናቸው..ʔ

1. ካናዳ

2. ጃማይካ

3. አውስትራሊያ

4. ኒውዚላንድ

5. በሃማስ

6. ፓፑዋ ኒው ጊኒ

7. ሰለሞን ደሴቶች

8. በሊዝ

9. ሴንት ኪትስ እና ኔቪስ

10. ሴንት ሉሲያ እና ገራኒድስ

11. ቱቫሉ

12. አንቲጉዋ እና ባበርቡዳ

13. ግሬናዳ

14. ሰለሞን ደሴቶች እንዲሁም

15. ብሪታኒያ ናቸው

የንግስት ኤልሳቤጥን ህልፈት ተከትሎ በተለያዩ ሀገራት ውስጥ የቢሪታኒያ ንጉሳውያንን ከሀገራቸው ርእሰ ብሄርነት የማንሳት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል።

የብሪታኒያ ቅኝ ግዛት የነበረችው አንቲጓና ባርቡዳ ደሴት የብሪታኒያ ንጉሳውያንን ከርዕሰ በሄርነት በማንሳት ሪፐብሊክ ለመሆን የሚያስችላትን ህዝበ ውሳኔ ልታካሂድ መሆኑን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር ጋስቶን ብራዎን አስታውቀዋል።

አንቲጓና ባርቡዳ በፈረንጆቹ 1981 ከቅኝ ግዛት ነጻ ብትወጣም፤ የበሪታኒያ ንግስት ግን የሀገሪቱ ርዕሰ ብሄር ነበሩ።

ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ባርባዶስ ባሳለፍነው ዓመት ህዳር ወር ላይ የብሪታኒያ ንጉሰውያንን ከርዕሰ ብሄርነት በማንሳት ሪፐብሊክነቷን ማወጇ ይታወሳል።

News today, social life

ግብጽ ተንቀሳቃሽ የዳንስ ምስል በፌስቡክ ገጿ ላይ የለቀቀችን የዩንቨርሲቲ መምህር ከስራ አገደች

ከስራ የታገዱት ፕሮፌሰር ሞና አል ፕሪንስ የስዊዝ ልንል ዩንቨርስቲ መምህር ነበሩ

መምህሯ ለተማሪዎቿ አርአያ አልሆኑም በሚል ነው ከስራ የተባረሩት

ግብጽ የዳንስ ቪዲዮ በፌስቡክ ገጿ ላይ የፖሰተችን የዩንቨርሲቲ መምህር ከስራ አገደች።

ፕሮፌሰር ሞና አል ፕሪንስ በመባል የሚታወቁት እኝህ እንስት ከሰሞኑ በግላቸው የፌስቡክ ገጽ ላይ በሆድ የሚጨፈር የሰውነት እንቅስቃሴ ወይም ቤሊ ዳንስ ለተከታዮቻቸው አጋርተው ነበር።

እኝህ የስዊዝ ልንል ዩንቨርስቲ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህር ግብጻውያን ሴቶች እና ወጣቶች በነጻነትን የሚፈልጉትን እንዲያደርጉ በማበረታታትም ይታወቃሉ።

በቅርቡ በግል የፌስቡክ ገጻቸው ለተከታዮቻቸው ባጋሩት ተንቀሳቃሽ የዳንስ ምስል የግብጽን ባህል እና እምነት የሚጻረር ነው በሚል ክስ ቀርቦባቸው እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል።

የግብጽ አስተዳድራዊ ፍርድ ቤትም መምህሯ ለተማሪዎቻቸው አርዓያ ያልሆነ እንቅስቃሴ አድርገዋል በሚል ከስራ እንዲታገዱ መወሰኑ ተገልጿል።

መምህር ሞና ለወጣቶች አርአያ ያልሆነ ተማሪዎችን ወዳልተፈለገ ድርጊት የሚመራ ተግባር እንደፈጸሙ ፍርድ ቤቱ አስታውቋል ተብሏል።

መምህር ሞና ዳንስ ከፈለጉ መብታቸው ነው ያለው ፍርድ ቤቱ የግል ነጻነት ማለት ወጣቶች ልቅ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ መገፋፋት ግን ወንጀል ነው ብሏል ተብሏል ።

ፕሮፌሰር ሞና አል ፕሪንስ በፈረንጆቹ 2018 ላይ በተካሄደው የግብፅ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ብቸኛዋ ሴት እጩ ተወዳዳሪ እንደነበሩ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

News today, Politics

የጀርመን መራሄ መንግስት “ሩሲያ ከዩክሬን ምድር ሙሉ በሙሉ ለቃ እንድትወጣ” ፑቲንን ጠየቁ


ኦላፍ ሾልዝ፤ ፑቲን በተቻለ ፍጥነት ወደ “ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ” እንዲመጡ አሳስበዋል
የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ “ሩሲያ ከዩክሬን ምድር ሙሉ በሙሉ ለቃ እንድትወጣ” ፑቲንን ጠየቁ፡፡


ኦላፍ ሾልዝ ከፑቲን ጋር በነበራቸው 90 ደቂቃ በፈጀ የስልክ ቆይታ ፤ “ፑቲን በተቻለ ፍጥነት ተኩስ አቁመው ወደ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲመጡና ወታደራቸው ሙሉ በሙሉ ከዩክሬን ምድር በማውጣት የዩክሬን ግዛት ሉዓላዊነት እንዲያከብሩ” ማሳሰባቸው ቃል አቀባያቸው ስቴፈን ሃበስተሬት አስታውቋል፡፡


ኦላፍ ሾልዝ በተጨማሪም ሩሲያ በተደጋጋሚ የምትወቅሰውን እህል ከዩክሬን ወደ ውጭ የመላክ ጉዳይ የተደረሰውን የእህል ስምምነት እንድታከብር ፑቲንን መናገራቸውም ኤኤፍፒ ዘግቧል።


ፑቲን የእህል ስምምነቱን እንዳያጣጥሉ እና ሙሉ በሙሉ መተግበሩን እንዲቀጥሉም የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ተማጽነዋል፡፡


ኦላፍ ሾልዝ አሁን ላይ የጦርነቱ የስህበት ማዕከል ስለሆነው የዛፖሪዝሂያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደህንነት ጉዳይ በተመለከተም ለፑቲን ጥያቄ አንስተው ተወያይተዋል፡፡


በዚህም የጀርመኑ መሪ ፑቲን “ምንም አይነት መባባስ እንዲያስወግዱና በዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የተመከሩትን እርምጃዎች (ነጻ ቀጠና እንዲቋቋም) ሙሉ በሙሉ እንዲተገብሩ” ጠይቀዋል።


የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ከፑቲን ጋር ዘለግ ያለ ቆይታ ያደረጉት፤ ሞስኮ በርሊን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላክ ቀይ መስመር እየጣሰች ነው የሚል ማስጠንቀቅያ በሰጠቀችበት ማግስት መሆኑ ነው፡፡


በጀርመን የሩሲያ አምባሳደር ሰርጌይ ናቼቭ ፤ የዩክሬን መንግስት ጀርመን ስሪት አውዳሚ ጦር መሳሪያዎችን እየታጠቀ መሆኑ ሀቅ ነው ማለታቸው አይዘነጋም፡፡
የጦር መሳሪያዎች በሩሲያ ጦር ላይ ብቻ ሳይሆን በዶንባስ ክልል በሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ለማጥቃት እየዋሉ እንደሆነም ነበር የተናገሩት አምባሳደሩ፡፡


የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸው ይታወሳል።


ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በገልጸውላቸዋል።


ጀርመን ቀይ መስመር አልፋለች ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች
ጀርመንም ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ለማቅረብ በሚል ፖሊሲ እስከ ማሻሻል ደርሳ እንደነበረ ይታወሳል።


ሩሲያም በተለያዩ ጊዜያት ከምእራባውያን ለዩክሬን ያበረከቷቸው የረጅም ርቀት ሮኬትን ጨምሮ ይለያዩ የጦር መሳሪያዎችን አወደምኩ ማለቷ አይዘነጋም።

News today, Politics

ዢ ዢንፒንግ እና ፑቲን ስለ ዩክሬን ጦርነት እንደሚወያዩ ተገለጸ

የቻይናው መሪ ዢ ዢንፒንግ እና የሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ስላለው ጦርነት እና በሌሎች “ዓለም አቀፋዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች” ዙሪያ በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚወያዩ ክሬምሊን ገለጸ።

መሪዎቹ በኡዝቤኪስታን የሚወያዩ ሲሆን ለምዕራቡ ዓለም “አማራጭ” በሚያሳየው ስብሰባ ላይ ነው የሚገናኙት ብሏል ክሬምሊን።

ዢ ዢንፒንግ እና ቭላድሚር ፑቲን

ዢ ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት በኋላ የመጀመሪያውን የባሕር ማዶ ጉብኝታቸውን እያደረጉ ነው።

ጉብኝቱ ዢ ሦስተኛ የሥልጣን ዘመን ለማግኘት በሚጥሩበት እና ፑቲን ከምዕራቡ ዓለም ጋር ያላቸው ግንኙነት በዩክሬን ጦርነት ምክንያት ዝቅተኛ ደረጃ በደረሰበት ወቅት የሚካሄድ ነው።

ዢ የሦስት ቀን ጉብኝታቸውን በካዛኪስታን ረቡዕ ጀምረዋል።

ከዚያም ለሁለት ቀናት በሚቆየውና በሳምርካንድ በሚካሄደው የሻንጋይ የትብብር ድርጅት (ኤስሲኦ) ስብሰባ ላይ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ይገናኛሉ።

ፑቲን ከሕንድ፣ ከፓኪስታን፣ ከቱርክ እና ከኢራን መሪዎች ጋርም ይገናኛሉ።

ከቻይናው መሪ ጋር የሚያደርጉት ውይይት “በተለየ መልኩ ጠቃሚ ነው” ሲሉ የክሬምሊን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቃል አቀባይ ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል።

ጉባኤው እየተካሄደ ካለው “ትልቅ የፖለቲካ ለውጥ ጀርባ የሚደረግ ነው” ብለዋል።

ኤስሲኦ እአአ በ2001 ከቀድሞ የሶቪየት ማዕከላዊ እስያ አራት አገራት ጋር የተመሠረተ ነው።

ቻይና እና ሩሲያ ድርጅቱን ለምዕራባውያን ቡድኖች እንደ አማራጭ ለማቀረብ ደፋ ቀና ሲሉ ቆይተዋል።

የዢ ጉብኝት ዜሮ ኮቪድ የተባለው ፖሊሲ በቀጠለበት እና በቻይና በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም የእንቅስቃሴ ገደብ በተጣለበት ወቅት ነው።

የተቀረው ዓለም ከቫይረሱ ጋር አብሮ መኖርን በመማር ወደ ቀድሞ  ሕይወት ሲመለስ ቤጂንግ ድንገተኛ ሁኔታ በተፈጠረ ቁጥር ሁሉንም ከተሞቿን እና ግዛቶችን መዝጋቷን ቀጥላለች።

ዢ ለመጨረሻ ጊዜ ከአገር ውጭ ጉብኝት ያደረጉት እአአ ጥር 2020 ምያንማርን ለመጎብኘት ሲያቀኑ ነው።

ይህም የመጀመርያው የእንቅስቃሴ ገደብ በውሃን ከመጣሉ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ነበር።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቻይና ለመቆየት የተገደዱ ሲሆን ሐምሌ ላይ ከዋናው ቻይና ውጭ ወደ ሆንግ ኮንግ አቅንተዋል።

ፑቲንም በውጭ አገራት ያልተለመደ ጉዞ እያደረጉ ነው።

የሩሲያ ወታደሮች ዩክሬንን ከወረሩ በኋላ በሐምሌ ወር ቴህራን ላይ ከቱርክ እና ከኢራን መሪዎች ጋር ካደረጉት ስብሰባ ወዲህ ይህ ሁለተኛው የውጭ ጉብኝታቸው ነው።

ሁለቱ መሪዎች በዚህ ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ ነው የሚገናኙት። ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት በየካቲት ወር ቤጂንግ ባዘጋጀችው የክረምት ኦሊምፒክ ነው።

በየካቲት የተካሄደውን ስብሰባ ተከትሎ ሁለቱ መሪዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ በአገሮቻቸው መካከል ያለውን ወዳጅነት “ገደብ የለሽ” ብለውታል።

ሩሲያ ከቀናት በኋላ ዩክሬንን ወረረች። ቻይና ወረራውን ማውገዟንም ሆነ መደገፏን አልገለፀችም።

ቤጂንግ ለጦርነቱ ተጠያቂዎቹ ሁለቱም ወገኖች ናቸው ትላለች።

ቻይና በሩሲያ ላይ የተጣለው ዓለም አቀፍ ማዕቀብ አካል አይደለችም። በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥም እያደገ መሄዱን ቀጥሏል።

ከዩክሬን ወረራ በኋላ ሕንድ እና ቻይና ከሩሲያ የሚያስገቡት ነዳጅ ጨምሯል።

ቻይና ከምዕራቡ ዓለም እና በተለይም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት በቅርብ ወራት ወዲህ ውጥረት ነግሦበታል።

የታይዋን ጉዳይ ደግሞ ነገሩን አባብሶታል። ቻይና ደሴቱን የግዛቴ አካል ነው ትላለች።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ደሴቲቱን መጎብኘታቸውን ተከትሎ “ምላሽ ለመስጠት” በሚል ቤጂንግ በታይዋን ዙሪያ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ አድርጋለች።

የቻይናን ጉዳይ የሚከታተሉ ባለሙያዎች እንደሚሉት በእንቅስቃሴ ገደብ እና ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ምክንያት ተግዳሮቶች ቢኖርባቸውም፣ ዢ ከሁለት ዓመት በኋላ ቻይናን ለቀው ለመውጣት መወሰናቸው በአመራሩ ላይ ያላቸውን እምነት ያሳያል።

ተንታኞች እንደሚሉት በመጪው ጥቅምት በሚካሄደው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ኮንግረስ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ለሦስተኛ ጊዜ እንዲመረጡ ይጠብቃሉ።

የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ማነው?

ኤስሲኦ በቻይና፣ ሩሲያ፣ ካዛኪስታን፣ ኪርጊስታን፣ ታጃኪስታን እና ኡዝቤኪስታን የተመሠረተ የአውሮፓ እና እስያ አገራት የፖለቲካ ፣ የምጣኔ ሀብት እና የደኅንነት ድርጅት ነው።

ኢራን በ2001 የተቋቋመውን ድርጅት ለመቀላቀል ፍላጎት አላት።

ቻይና በቤልት ኤንድ ሮድ ፕሮጀክቶቿ በቀጠናው ትልቅ መዋዕለ ንዋይ የምታፈስ ሲሆን አባላቱ በንግድ ዙሪያ ይወያያሉ።

ቤጂንግ ከአውሮፓ ጋር ለምታደርገው የንግድ ልውውጥ አዳዲስ የባቡር መስመሮችን ለመዘርጋት የምትፈልግ ሲሆን የመካከለኛው እስያ አገራት ደግሞ ከቻይና ጋር የበለጠ ግንኙነት ለመፍጠር ጉጉት አላቸው።

ኪርጊስታን በ2023 ከቻይና እና ኡዝቤኪስታን ጋር የሚያገናኛትን አዲስ የባቡር መስመር ዝርጋታ እንደምትጀምር አስታውቃለች።

News today, Politics

ሩሲያ በሌሎች ሀገራት ፍላጎቷን ለማስጠበቅ 300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን አሜሪካ ገለጸች

ሩሲያ በአምስት አህጉራት ለሚገኙ ከ20 በላይ ሀገራት ገንዘብ ፈሰስ አድርጋለች ተብሏል

ሩሲያ እስካሁን በአሜሪካ ክስ ዙሪያ ምላሽ አልሰጠችም

ሩሲያ በሌሎች ሀገራት ፍላጎቷን ለማስጠበቅ 300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን አሜሪካ ገለጸች።

የአሜሪካ የደህንነት ተቋም ባወጣው መረጃ ሩሲያ በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት የፖለቲካ ፍላጎቷን ያስፈጽሙልኛል ያለቻቸውን እጩዎች እና ፓርቲዎች በገንዘብ እየረዳች ነው ብሏል።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ ሩሲያ በአምስት አህጉራት ለሚገኙ ከ20 በላይ ሀገራት ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ፈሰስ አድርጋለች ።

በተለይም ከፈረንጆቹ 2014 ጀምሮ ለአውሮፓ፣ እስያ፣ አፍሪካ እና ሁለቱ የአሜሪካ አህጉራት ስር ላሉ ሀገራት በተለያየ መንገድ ገንዘብ ሰጥታለች ተብሏል።

ሩሲያ ገንዘቡን ፈሰስ የምታደርገው በፋውንዴሽን ስም በተቋቀቋሙ ድርጅቶች እና ለይስሙላ በተቋቋሙ የንግድ ድርጅቶች ስም እንደሆነም አሜሪካ ገልጻለች።

አሜሪካ በሩሲያ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገላቸውን ሀገራት ለጊዜው ያልጠቀሰች ሲሆን ከአውሮፓ አልባኒያ፣ ቦስኒያ እና ሄርዜጎቪና፣ ሞንቴኔግሮ ሲሆኑ ከአፍሪካ ደግሞ ሜዳጋስካር አንዷ መሆኗን ኤኤፍፒ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጽህፈት ቤት ያገኘውን መረጃ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ሩሲያ ገንዘቡን ወደ ምትፈልጋቸው ሀገራት እና የፓርቲ እጩዎች ቤልጂየም እና ኢኳዶር ከሚገኙት የሩሲያ ኢምባሲዎች በኩል እንደሆነም ተጠቅሷል።

አሜሪካም የፓለቲካ ፍላጎቶቿን ለማስፈጸም በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት ላይ በሲአይኤ በኩል ጣልቃ በመግባት መፈንቅለ መንግስት እስከማስፈጸም የሚደርስ ሙከራ ታደርጋለች የሚል ክስ እንደሚነሳባት የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።

በተለይም በኢራን እና በቺሊ ሲአይኤ መፈንቅለ መንግስት እንዲፈጸም አድርጓል በሚል የሚቀርብባትን ክስ አሜሪካ ውድቅ አድርጋለችም ተብሏል።

የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳድር በሩሲያ ላይ ያቀረበውን ክስ ራሷ አሜሪካ በዲሞክራሲ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ስም ትፈጽማለች በሚል የቀረበበትን ክስ ውድቅ ማድረጉም ተገልጿል።ሩሲያ በአሜሪካ በቀረበባት ክስ ዙሪያ እስካሁን ምላሽ እንዳልሰጠች ተገልጿል።

News today, social life

በዓለም ላይ 50 ሚሊዮን ዜጎች አሁንም በባርነት ውስጥ እንደሚኖሩ ተመድ ገለጸ


በዓረብ ሀገራት ከፍተኛ የግዳጅ ስራዎች ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች እንዳሉ ተመድ ገልጿል

በዓለም ላይ 50 ሚሊዮን ዜጎች አሁንም በባርነት ውስጥ እንደሚኖሩ ተመድ ገለጸ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ባወጣው ሪፖርት 50 ሚሊዮን የዓለማችን ዜጎች አሁንም በባርነት ውስጥ እንደሚኖሩ ገልጿል።

በዓለማችን ከሚኖሩ 150 ሰዎች ውስጥ አንድ ሰው በግዳጅ ስራ ላይ ወይም ጋብቻ ውስጥ እንደሚኖሩ የድርጅቱ ሪፖርት ያስረዳል።

ከፍተኛ የእድሜ ጣራ ያስመዘገቡ 15 የአፍሪካ ሀገራት
ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ወይም አይኤልኦ እና የፍልሰተኞች ድርጅት በጋራ ባወጡት ዓመታዊ ሪፖርት 27 ሚሊዮን ዜጎች በግድ ስራ እንዲሰሩ እየተደረገ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 15 ሚሊዮን ያህሉ ሴቶች እና ህጻናት ናቸው ተብሏል፡፡

ተመድ በፈረንጆቹ 2017 ላይ ተመሳሳይ ሪፖርት ይፋ አድርጎ የነበር ሲሆን አሁን ላይ በባርነት የሚኖሩ ዜጎች ቁጥር ከአምስት ዓመት በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ህዝብ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል፡፡

በባርነት ተገደው ከሚሰሩ ዜጎች ውስጥ 22 ሚሊዮኑ በእስያ፣ 4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ያህሉ ደግሞ በአውሮፓ፣ 3 ነጥብ 8 ሚሊዮኑ በአፍሪካ፣ እንዲሁም 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን በአሜሪካ እና 900 ሺህ ያህሉ ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅ ይኖራሉ ተብሏል፡፡

በዓረብ ሀገራት ከአንድ ሺህ ሰዎች መካከል ስድስቱ ተገደው ስራ የሚሰሩ ሲሆን ይህ አሃዝ በሌሎች አህጉራት ካለው ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛው እንደሆነ ተገልጿል፡፡

6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ያህል ዜጎች ደግሞ ተገደው በሴተኛ አዳሪነት እንዲሰማሩ ተደርገዋል ያለው ተመድ በተለይም ስደተኞች የዚህ ድርጊት ሰለባ እንደሆኑ ተጠቅሷል፡፡

ተገደው በጋብቻ ውስጥ እየኖሩ ያሉት ዜጎች ቁጥር አሁን ላይ 22 ሚሊዮን ያህል ናቸው የተባለ ሲሆን ይህ አሃዝ ከአምስት ዓመት በፊት በጥናት ከተረጋገጠው ጋር ሲነጻጸር የ6 ነጥብ 6 ብልጫ ዓለው ተብሏል፡፡

እስያ እና ፓሲፊክ አካባቢዎች ከ14 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተገደው በትዳር ውስጥ ያኖራሉ ያለው ተመድ ቀሪው በአፍሪካ እና አውሮፓ እንደሚኖሩ ተገልጿል፡፡

ዝቅተኛ ኢኮኖሚ ባለባቸው ሀገራት ውስጥ ከአምስቱ ሰዎች መካከል ሶስቱ በግድ በትዳር ውስጥ እየኖሩ ሲሆን በበለጸጉ ሀገራት ደግሞ 26 በመቶዎቹ ሰዎች በተመሳሳይ የግዳጅ ጋብቻ ውስጥ ያሉ ናቸው ተብሏል

News today, Politics

ጀርመን ቀይ መስመር አልፋለች ስትል ሩሲያ አስጠነቀቀች

ጀርመን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላኳ ነው ከሩሲያ ማስጠንቀቂያ የደረሳት

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ

በበርሊን የሩሲያ አምባሳደር ጀርመን ለዩክሬን ያቀረበቻቸው የጦር መሳሪያዎች ነጹሃን እየተጎዱበት ነው ብለዋል

ጀርመን ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎችን በመላክ ቀይ መስመር እየጣሰች ነው ሲሉ በበርሊን የሩሲያ አምባሳደር አስጠነቀቁ።

በጀርመን የሩሲያ አምባሳደር ሰርጌይ ናቼቭ፤ የዩክሬን መንግስት ጀርመን ስሪት አውዳሚ ጦር መሳሪያዎችን እየታጠቀ መሆኑ ሀቅ ነው ብለዋል።

ነገር ግን በእነዚህ የጦር መሳሪያዎች በሩሲያ ጦር ላይ ብቻ ሳይሆን በዶንባስ ክልል በሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ለማጥቃት እየዋሉ ነው፤ ይህ ደግሞ ቀይ መስመርን መጣስ ነው ማለታቸውን አር.ቲ ዘግቧል።

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሀገራቸው ለዩክሬን አዲስ የጦር መሳሪያ ልታበረክት መሆኑን እና በቅርቡ እንደሚላክላት መናገራቸው ይታወሳል።

አዲሱ የጦር መሳሪያ “ሱፐር ሞዴል ዊፐን” በመባል እንደሚጠራም መራሄ መንግስቱ የተናገሩ ሲሆን፤ በተጨማሪም ትልቅ የአየር መከላከያ ስርዓት፤ ራዳር እና ድሮኖች ለዩክሬን እንደሚላኩ አረጋግጠዋል።

የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ሃምሌ ላይ በዩክሬን ጉብኝት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን ሀገራቸው ዩክሬንን ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ለፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በገልጸውላቸዋል።

ዩከሬን እና ሩሲያ ወደ ጦርነት መግባታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ጀርመንም ለዩክሬን ጦር መሳሪያ ለማቅረብ በሚል ፖሊሲ እስከ ማሻሻል ደርሳ እንደነበረ ይታወሳል።

ሩሲያም በተለያዩ ጊዜያት ከምእራባውያን ለዩክሬን ያበረከቷቸው የረጅም ርቀት ሮኬትን ጨምሮ ይለያዩ የጦር መሳሪያዎችን አወደምኩ ማለቷ አይዘነጋም።

News today, Politics

ለተመድ ጠቅላላ ጉባዔ የአሜሪካ ቪዛ ሲጠይቁ የቆዩት የሩሲያ ልዑካን ወደ ኒውዮርክ ለመሄድ የሚያስችል ቪዛ አገኙ

አንጋፋው ዲፕሎማት ሰርጌ ላቭሮቭ “በፑቲን ምትክ በጠቅላላ ጉባዔው ሩሲያን ወክለው በመሳተፍ ላይ ናቸው” ተብሏል
ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጉባዔ የአሜሪካ ቪዛ ሲጠይቁ የቆዩት የሩሲያ ልዑካን ወደ ኒውዮርክ ለመሳተፍ የሚያችላቸው ቪዛ አግኝተዋል፡፡


የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የሩሲያ ልዑካን ቡድን አባላት በኒውዮርኩ ስብሰባ ለመሳተፍ የሚያስችላቸው ቪዛ ማግኘታቸው የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡


ሩሲያ፤ 77 ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ለሚወክላት ልዑክ የቪዛ ጥያቄ ማቅረቧን ካቀረበች ብትቆይም አሁን ላይ የዘገየ ምላሽ ማግኘቷ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ሞስኮ፤ አሜሪካ በጠቅላላ ጉባኤው ሙሉ በሙሉ የሩሲያ ተሳትፎን ለመከላከል እየሞከረች ነው የሚል ክስ ስታሰማ መቆየቷም አይዘነጋም፡፡


“አሜሪካ ግዴታዎቿ እየጣሰች ነው” ሲሉም ነበር የከሬምሊን ሰዎች ዋሽንግተንን የወቀሱት፡፡
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዘንድሮ በሚካሄደው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እንደማይገኙ ቀድመው መግለጻቸው ይታወሳል።


በዚህ መሰረት በጉባዔው ሩሲያን የሚወክሉት ከፑቲን ቀጥሎ ወዳጆቻቸው “ጠንካራው ዲፕሎማት” የሚሏቸው፤ ምዕራባውያን ደግሞ “አደገኛው” የሚሏቸው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሩቁ ሰርጌ ላቭሮቭ ሆነዋል።


ሰርጌ ላቭሮቭ የሀገራቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት በአውሮፓውያኑ 2004 ነበር። የ77 ዓመቱ ሰርጌ ላቭሮቭ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከመሆናቸው በፊት ለ10 ዓመታት ማለትም ከአውሮፓውያኑ 1994 እስከ 2004 በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሩሲያ ቋሚ መልዕክተኛ ነበሩ።


ሩሲያን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 77 ኛው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የወከሉት ሰርጌ ላቭሮቭ በሀገራቸው ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መስራት የጀመሩት በ22 ዓመታቸው ሲሆን በድምሩ ለግማሽ ክፍለ ዘመን (ለ 50 ዓመታት) ያገለገሉም ናቸው።


77 ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ በፈረንጆቹ ከዛሬ መስከረም 13 እስከ 20 በኒውዮርክ እንደሚካሄድ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል።

News today, Politics

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃቶች እያደረስኩ ነው አለች

ሞስኮ የኪቭ ጦር በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች እየፈጸመ ነው ስትል ከሳለች

ፕሬዝደንት ዜለንስኪ በመልሶ ማጥቃት 6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ኃይሎች ነጻ ወጥቷል ብለዋል

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ “መጠነ ሰፊ ጥቃቶች” እያደረስኩ ነው አለች፡፡

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ጦር ላይ “የአየር፣ የሮኬት እና መድፍ የተቀናጀ ከፍተኛ ጥቃት እያደረሱ ነው” ብሏል፡፡

የክሬምሊን ባለስልጣናት የኪቭ ጦር መልሶ በያዘው ግዛት ውስጥ በሲቪሎች ላይ በደል ፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።

የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቃል አቀባይ በካርኪቭ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች መፈጸማቸው የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ መሆኑን ተናግረዋል።

https://facebook.com/KeAlemiZuriya

“ብዙ የቅጣት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው…ሰዎች እየተሰቃዩ ፣ እየተንገላቱ ነው “ሲሉም ነው ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።

ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች የወሰዱት እርምጃን ተከትሎ የሩሲያ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት ውስጥ ከሚገኙት ሁለት አካባቢዎች (ባላክሊያ እና ኢዚየም ) ለማፈግፈግ መገደዳቸው ሮይተርስ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡

በዚህም የዩክሬን ባለስልጣነት ወታደሮቻቸው ለሩሲያ ኃይሎች ወሳኝ አቅርቦት ማዕከል የሆነችውን ኩፒያንስክ መቆጣጠራቸው ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡

ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በሰጡት መገለጫ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።

የዩክሬን ባለስልጣነት ይህን ይበሉ እንጂ፤የተወሰደው የማፈግፈግ እርምጃ በምስራቅ ዩክሬን የመትገኘውን ዶንባስ ግዛት ነጻ ለማውጣት የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግ ያለመ መሆኑን የምትገለጸው ሩሲያ በዩክሬን ምድር ፈለገቸውን ዓለማ ከመፈጸም የሚያግዳት ኃይል እንደሌለ በመግለጽ ላይ ናት፡፡

ሩሲያ፤ “ዓላማዬን እስከማሳካ የሚቆም ወታደራዊ ዘመቻ የለም” ስትል በትናንትናው እለት መግለጿም አይዘነጋም፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻው መጀመሪያ ላይ የተቀመጡት አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ይቀጥላል” ብለዋል።

አሁን ላይ የሩሲያ አየር፣ ሮኬቶችና መድፍ ኃይሎች የኩፒያንስክ እና ኢዚዩም የከተማ ማዕከሎችን ጨምሮ በዩክሬን የጦር ኃይሎች ይዞታወች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በመሰንዘር ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ከኪቭ ጋር ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ንግግሮች ተጠይቀውም፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ኤኤፍፒ ዘግቧል።

News today, Politics, social life

የፌደራል መንግስት እና የህወሓት የድርድር ሂደት ይሳካ ይሆን…?


ምሁራኑ “ህወሓት አሁን ላይ ድርድሩን የጠየቀበት ምክንያት ተገዶ ይሆናል፤ ምክንያት ፈልጎ ሊያቋርጠው እንደሚችል ግምታቸውን አሰቀምጠዋል
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው ህወሓት በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ማጥቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው።


ይህ ጦርነት ላለፉት 23 ወራት የዘለቀ ሲሆን ጦርነቱን ለማስቆም አሊያም ለማሸማገል ራሱ የፌደራል መንግስትን ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት የአዉሮፓ ህብረት የተባሩት መንግስታት ድርጅት እና የተለያዩ አካላት ጥረት እያደረጉ ቢሆንም ድርድሩ እስካሁን ሳይሳካ ቀርቷል።


የፌደራል መንግስት እና ህወሓት ድርድር ተስፋ እና ስጋቶች
መንግስት ከህወሃት ጋር ድርድር የሚካሄድበትን ቦታ ለመወሰን ከአፍሪካ ህብረት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን አስታወቀ
አሁንም ጦርነት ለማስቆምና እልባት ለመፈለግ እየተደረገ ያለው ጥረት በህወሓት በኩል እንቅፋት እየገጠመው ነዉ ሲል መንግስት በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።


መንግስት የሰላም ድርድሩን በአስቸኳይ ለመጀመር የሚያስችል የሰላም ምክረ- ሃሳብን የያዘ ሰነድ ማዘጋጀቱን ይፋ ቢያደርግም፣ ህውሓት በተቃራኒው ከፌደራል መንግስት ጥቃት እንደተከፈተበት በመግለጽ የተኩስ አቁም ስምምነቱ መፍረሱን ገልጾ ነበር።


የፌደራል መንግስትም ህወሓት ከነሀሴ 18 2014 አ.ም ጀምሮ በራያ፣ ወልቃይት ፣ ሰቆጣ እና አፋር ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።


ከተጠቀሰው ዕለት ጀምሮም በበትግራይ ክልል እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች እንዲሁም በኢትዮ ሱዳን ድንበር አካባቢዎች ላይ ጦርነቱ መቀጠሉ የተገለጸ ሲሆን፤ ህወሓት የዘመን መለወጫ ዕለት ማለትም መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለመወያየት እና ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መዘጋጀቱን አስታውቋል።


ፃድቃን ገብረተንሳይና ጌታቸው ረዳን ያካተተ ከፌደራል መንግስት ጋር ለሚደረገው ድርድር የሚወክሉትን ቡድን ያፈ ያደረገው ህወሓት አለማቀፉ ማኅበረሰብ በታዛቢነትና ድጋፍ በማድረግ እንዲሳተፉ እንደሚፈልግም ገልጿል።


የህወሃትን የእደራደራለሁ መግለጫን ተከትሎ ብዙዎች ተስፋ እና ስጋትን እንደተሰማቸው በተለያዩ መንገዶች ሃሳባቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።
አል ዐይን አማርኛ የህወሓት ለመደራደር ዝግጁ ነኝ ማለቱን ተከትሎ ስለጉዳዩ ምሁራንን አነጋግሯል።


አቶ አበበ ይርጋ በባህር ዳር ዩንቨርሲቲ ስር ባለው የብሉናይል ውሀ ኢንስቲትዩት የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ጥናት መምህር ናቸው፤ የህወሃትን በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ከፌደራል መንግስት ጋር እደራደራለሁ ማለቱን እንዴት ያዩታል? በሚል ላነሳንላቸው ጥያቄ፤
“ህወሀት ወደ ድርድር እንዲመጣ ለረጅም ጊዜ ሲለመን ነበር፣ ነገር ግን ቅድመ ሁኔታ ሲደርድር እና ሰላም እንዳይፈጠር የቻለውን ሁሉ ሲያደርግ ቆይቷል።

በድንገት ያለ ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ቦታ እደራደራለሁ ማለቱ ከልቡ አይመስለኝም፣ ይሄንን መግለጫም ያወጣው በሎጅስቲክስ እና ፕሮፓጋንዳ ሲያግዙት የቆዩት አካላት አዘውት ነው” ብዬ አስባለሁ ብለዋል።


“በኢትዮጵያ የተለየ ፍላጎት ያላቸው ሀገራት ቁጥራቸው እየጨመረ ነው” የሚሉት መምህር አበበ “ህወሓት እየተሸነፈ ሲመስላቸው እና ተጨማሪ ድጋፍ ለማሰባሰብ እንዲያመቻቸው” ለድርድር ዝግጁ መሆኑን እንዲያሳውቅ ሳያደርገው እንዳልቀረ ግምት እንዳላቸውም ጠቅሰዋል።


“ህወሓት እደራደራለሁ ማለቱ በፌደራል መንግስት ላይ በሚደረግ ጫና ምክንያት መከላከያ ሰራዊት ማጥቃቱን ትቶ አሁን ባለበት ቦታ እንዲቆም ቀስ በቀስም ለአራተኛ ዙር ጦርነት የመዘጋጃ ጊዜ እንደሚያገኝ በማሰቡ ሊሆን ይችላል” ሲሉም ተናግረዋል።


“ድርድሩ የውጭ ጣልቃ ገብነት የተጫነው ይመስላል” የሚሉት መምህር አበበ “ለኢትዮጵያ ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጣላት ከድርድሩ ጎን ለጎን በህወሀት ጥቃት እየደረሰበት ያለውን የትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች ህዝብን መታደግ ሲቻል እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን መጀመር ብቻ” እንደሆነ ጠቁመዋል።


ሌላኛው በድርድሩ ዙሪያ አል ዐይን አማርኛ ያናገራቸው በጅግጅጋ ዩንቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ህግ መምህሩ ሰለሞን ጓዴ ናቸው።


እሳቸው እንዳሉት “በእኔ አመለካከት “ህወሓት አሁን ላይ ድርድሩን የጠየቀበት ምክንያት ተገዶ ይሆናል የሚል እሳቤ አለኝ ምክንያቱም ይፈልጉት የነበረዉ ስትራቴጂካዊ ቦታ ተይዞባቸዋል በዚህም ጫናዉ ሲበዛባቸዉና የጦርነት የበላይነትን ሲያጡ መጀመሪያ አጎንብሶ ከዛም አፈር ልሶ ለመነሳት የሚደረግ ሙከራ ነዉ ብዬ ነዉ የማምነዉ በአንድ ሳምንት ዉስጥ ሽንፈት ካልሆነ በስተቀር ሊፈጠር የሚችል አሳማኝ ምክንያት የለም” ሲሉ ገልጸዋል፡፡


“ህወሓት እንዳለው ወደ ድርድር ከመጣ የታጣቂዎቹ ትጥቅ መፍታት ጉዳይ የድርድሩ ዋነኛ ጉዳይ ይሆናል” የሚሉት መምህር ሰለሞን “ሰላም እንዲመጣ ከተፈለገ መተማመንን የሚያጎለብት ስራ መሰራት አለበት” ብለዋል፡፡


ድርድሩ ፍሬያማ እንዲሆን ከተፈለገ መጀመሪያ ሰላማዊ የሆነ አየር ያስፈልጋል፤ ሉዓላዊነት መከበር አለበት፣ ይህ የሚሆነው ደግሞ የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ ሲፈቱ እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀገሪቱን ዳር ድንበር መቆጣጠር በሚያስችለው መንገድ ሲሰማራ ብቻ እንደሆነም መምህር ሰለሞን አክለዋል።


መምህር ሰለሞን አክለውም የህወሓት የእስካሁኑ የፖለቲካ ባህል ምን ጊዜም እራሱን ብቻ የሚያስቀድም በመሆኑ እደራደራለሁ ማለቱ ከልቡ ሊሆን እንደማይችል ተናግረዋል።


በመንግስትና ህወሓት መካከል የሚደረገው ድርድር ሁሉንም ያሳተፈ ኢንዲሆን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት ጠየቀ
“ህወሓት እኔ ያልመራሁት ነገር አይደረግም የሚል ድርቅ ያለ መንገድን የሚከተል ድርጅት ነው” የሚሉት መምህር ሰለሞን ድርድር በባህሪው ሰጥቶ መቀበልን እና ሰላማዊ ሁኔታዎችን የሚፈልግ በመሆኑ ድርድሩ የመሳካት እድሉ ጠባብ መሆኑን ጠቁመዋል።


ህወሓት ድርድሩን ቢጀምረው እንኳን ምክንያት ፈልጎ ሊያቋርጠው እንደሚችል ግምታቸውን ያስቀመጡት መምህር ሰለሞን የፌደራል መንግስት በህወሀት ወጥመድ ሊገባ እንደማይገባም አሳስበዋል።


የፌደራል መንግስት ከዚህ በፊት ባወጣው መግለጫ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ከህወሃት ጋር በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ እንደሚደራደር ማሳወቁ ይታወሳል።


ለዚህ ድርድርም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራ አብይ ኮሚቴ መቋቋሙን እና ሌሎች ንዑስ ኮሚቴዎችም ተቋቁመው ስራ መጀመራቸው መገለጹ አይዘነጋም።

News today, social life

የሴኔጋል ፓርላማ አባላት እርስበርሳቸው ተደባደቡ

ሴኔጋል ከአንድ ወር በፊት ነበር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደችው።

ገዥው ፓርቲ አብዛኛውን መቀመጫ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በተነጠቀበት በዚህ ምርጫ ተመራጭ የሆኑ የምክር ቤት አባላት ዛሬ ስራቸው ጀምረዋል።

አባላቱ በዛሬው ስብሰባቸው የምክር ቤቱን ተጠሪ ፕሬዝዳንት መምረጥ የነበረባቸው ቢሆንም ወደ ስምምነት መምጣት አልቻሉም።

የምክር ቤቱ አባላት አለመስማማታቸው ተከትሎ በተፈጠረ አለመግባባት በወንበር እና ውሀ መያዣ ፕላስቲኮችን እርስ በርስ በመወራወር እንደተደባደቡ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል።

በምክር ቤቱ አባላት የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎም የሀገሪቱ ፖሊስ ገብቶ ተደባዳቢዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ክስተቱን ተቆጣጥሯል ተብሏል።

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya

News today, Politics

የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት ከ40 ዓመት ገደማ በኋላ ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ


የዋሸንግተን መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት ዝቅ ያለው በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ በመናሩ ነው


የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ከ40 ዓመት በኋላ ቅናሽ ማሳየቱ  ተገለጸ።
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስድስት ወራት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ በዓለም ምግብ እና ነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ እንዲመዘገብ ምክንያት ሆኗል።


 ጦርነቱ በዓለም ዲፕሎማሲ ላይ የተለያዩ መፋለሶችን ያስከተለ ሲሆን ሀገራት ከትብብር ይልቅ ጎራ ለይተው እንዲሰለፉ እያደረገም ይገኛል።
ባለፈው ሳምንት ብቻ 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ከመጠባበቂያዋ በማውጣት ለዜጎቿ እንዲሸጥ አድርጋለች።


አሜሪካ ከአንድ ዓመት በፊት በመጠባበቂያ ክፍሏ ያስቀመጠችው ነዳጅ 621 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ነበር።


ይሁንና በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መከሰትን ተከትሎ ባጋጠመ የነዳጅ ዋጋ መናር ምክንያት ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት በሚል ከመጠባበቂያ ክፍሏ እያወጣች በመሸጥ ላይ እንደምትገኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።
አሁን ላይ የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት መጠን 434 ሚሊዮን በርሜል ላይ ደርሷልም ተብሏል።


ከፈረንጆቹ 1984 ዓመት ጀምሮ የአሜሪካ መጠባበቂያ ነዳጅ ክምችት መጠን አሁን ካለበት መጠን ዝቅ ብሎ እንደማያውቅ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።


የአሜሪካ የነዳጅ አጠቃቀም መጠን በዚሁ ከቁጠለ ብሄራዊ የነዳጅ አጠቃቀም መጠን ወደ 358 ሚሊዮን በርሜል ዝቅ ይላል ተብሏል።


የዓለም ቀዳሚ ሰባት የበለጸጉ ሀገራት ስብስብ የሆነው የቡድን ሰባት ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ የዋጋ ተመን ማውጣታቸው ይታወሳል
ሩሲያ በበኩሏ ነዳጇን በሚያዋጣት ዋጋ ብቻ እንደምትሸጥ ገልጻ ወደ አውሮፓ የምትልከውን ነዳጅ ሙሉ ለሙሉ ማቋረጧ አይዘነጋም። 

የከዓለም ዙሪያ ቤተሰብ ይሁኑ
ቴሌግራም፡ https://t.me/KeAlemiZuriya
ዩቲዩብ: https://youtube.com/c/Kealemizuriya
ድረገፅ: https://kealemizuriya.data.blog
ትዊተር: https://twitter.com/KeAlemiZuriya
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/KeAlemiZuriya
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/Kealemizuriya

News today, Politics

ሩሲያ በዩክሬን የውጊያ ግንባሮች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃቶች እያደረስኩ ነው አለች


የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሩሲያ ኃይሎች በዩክሬን ጦር ላይ “የአየር፣ የሮኬት እና መድፍ የተቀናጀ ከፍተኛ ጥቃት እያደረሱ ነው” ብሏል፡፡


የክሬምሊን ባለስልጣናት የኪቭ ጦር መልሶ በያዘው ግዛት ውስጥ በሲቪሎች ላይ በደል ፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።


የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቃል አቀባይ በካርኪቭ ክልል በሰላማዊ ሰዎች ላይ “አስከፊ” የሚሉ በደሎች መፈጸማቸው የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ መሆኑን ተናግረዋል።


“ብዙ የቅጣት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው…ሰዎች እየተሰቃዩ ፣ እየተንገላቱ ነው “ሲሉም ነው ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች የተናገሩት።


ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ኃይሎች የወሰዱት እርምጃን ተከትሎ የሩሲያ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ግዛት ውስጥ ከሚገኙት ሁለት አካባቢዎች (ባላክሊያ እና ኢዚየም ) ለማፈግፈግ መገደዳቸው ሮይተርስ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡


በዚህም የዩክሬን ባለስልጣነት ወታደሮቻቸው ለሩሲያ ኃይሎች ወሳኝ አቅርቦት ማዕከል የሆነችውን ኩፒያንስክ መቆጣጠራቸው ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡
ፕሬዝደንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በሰጡት መገለጫ ወታደሮቻቸው በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ “6 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታ ከሩሲያ ነጻ መውጣቱ” ተናግረዋል።


የዩክሬን ባለስልጣነት ይህን ይበሉ እንጂ፤የተወሰደው የማፈግፈግ እርምጃ በምስራቅ ዩክሬን የመትገኘውን ዶንባስ ግዛት ነጻ ለማውጣት የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግ ያለመ መሆኑን የምትገለጸው ሩሲያ በዩክሬን ምድር ፈለገቸውን ዓለማ ከመፈጸም የሚያግዳት ኃይል እንደሌለ በመግለጽ ላይ ናት፡፡


ሩሲያ፤ “ዓላማዬን እስከማሳካ የሚቆም ወታደራዊ ዘመቻ የለም” ስትል በትናንትናው እለት መግለጿም አይዘነጋም፡፡


የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻው መጀመሪያ ላይ የተቀመጡት አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ይቀጥላል” ብለዋል።


አሁን ላይ የሩሲያ አየር፣ ሮኬቶችና መድፍ ኃይሎች የኩፒያንስክ እና ኢዚዩም የከተማ ማዕከሎችን ጨምሮ በዩክሬን የጦር ኃይሎች ይዞታወች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በመሰንዘር ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል።


ቃል አቀባዩ ከኪቭ ጋር ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ንግግሮች ተጠይቀውም፤ በሞስኮ እና በኪቭ መካከል የሚደረጉ “የድርድር ተስፋዎች የሉም” የሚል ምላሽ መስጠታቸው ኤኤፍፒ ዘግቧል።

News today, Politics

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ

በአርመን እና በአዘርባጃን መካከል ጦርነት ተቀስቅሶ 49 ወታደሮች ተገደሉ
አርመን እና አዘርባጃን ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው


የአርመኒያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኒኮል ፓሺኒያን በትናንትናው እለት ከአዘርባጃን ጋር በነበረው ጦርነት 49 የአርመን ወታደሮች ተገድለዋል ሲሉ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።


በአርመን ፖርላማ ቀርበው ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዘርባጃን የአርመንን ይዞታዎች ማጥቃቷን እና ጦርነቱ አሁንም መቀጠሉን ተናግረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ግጭቱ ወደ ጦርነት እንዲያመራ በማድረግ እርስበርሳቸው እየተካሰሱ ነው።


በአርመን እና አዘርባጃን መካከል ለአስርት አመታ ያሰቆጠረው አለመግባባት ኒጋርኖ ካራባክ በተባለ ቦታ መጀመሩ ይታወሳል።


በኒጋርኖ ካራባክ የተመረው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ቆሞ የነበረ ቢሆንም በድጋሚጨሊቀሰቀስ ችሏል።
ሪሲያ እና አሜሪካ ሁለቱም ሀገራት ግጭቱን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

News today, Politics

አፍሪካ ህብረት፣ ተመድ ፣አውሮፓ፣አሜሪካ እና ኢጋድ ህወሓት ባወጣው መግለጫ ዙሪያ ምን አሉ?

አፍሪካ ህብረት “ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ ተኩስ ለማቆም እንዲሰሩና የፊት ለፊት ንግግር እንዲያካሄዱ” ጥሪ አቅርቧል

የኢትዮጵያ መንግስት ጦርነቱ በድጋሚ ከመቀስቀሱ በፊት ከህወሓት ጋር ያለቅደመ ሁኔታ በየትኛውም ቦታ እንደሚደራደር መግለጹ ይታወሳል

ህወሓት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚካሄደው የሰላም ድርድር ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ትናንት ባውጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

 ህወሓት አቶ ጌታቸው ረዳን እና ጀነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ያከተተ ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

    ህወሐት ትናንት ማምሻው በትግራይ የውጭ ግንኙነት ጸ/ቤቱ በኩል ባወጣው መግለጫ ፤ የተሰየመው ተዳራዳሪ ቡድን ወደፊት በሚደረገው ድርድር “የትግራይን መንግስት” የሚወከል ስልጣን ተሰጥቶታለል ብሏል፡፡

    ህወሓት የተሰየመው ተደራዳሪ ቡድን “ሳይዘገይ ወደ ድርድር እንደሚገባ”ም ጠቁሟል፡፡

    የአፍሪካ ህብረት በትግራይ ለተፈጠረው ችግር መፍትሔ “አያመጣም” ሲል የነበረው ህወሓት፤ በትናንትናው መግለጫው ግን በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚደረግ ድርድር ላይ እንደሚሳተፍ ገልጿል፡፡

    ጦርነቱን በድርድር ለመፍታት ሲያደርግ የነበረው የአፍሪካ ህብረት የህወሓት መግለጫ በአወንታ እንደሚመለከው አስታውቋል፡፡

    የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ፤የትግራይ ክልል መንግስት ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትና በአፍሪካ ህብረት በሚመራ የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ፍቃደኝነት ማሳየቱን በበጎ እንደሚቀበሉት አስታውቀዋል፡፡

    እርመጃው በኢትዮጵያ ሰላም ለማስፈን ጥሩ እድል የሚፈጥር ነው ያሉት ሙሳ ፋኪ፤ “ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ ተኩስ ለማቆም እንዲሰሩና በአፍሪካ ህብረት መሪነት የፊት ለፊት ንግግር እንዲያካሄዱ” ጥሪ አቅርበዋል።

    ፊት ለፊት የሚደረገው ድርድር በሁለቱም ወገኖች ተቀባይነት ያላቸው “ዓለም አቀፍ አጋሮችን ያካተተ” እንደሚሆንም ፍንጭ ሰጥተዋል የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበሩ ሙሳ ፋኪ፡፡

    የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ህወሓት በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚደረገው የሰላም ሂደት ላይ ለመሳተፍ ባሳየው ፍላጎት ደሰተኛ መሆኑን ገልጿል፡፡

    የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፤ ሁለቱም ወገኖች ይህንን የሰላም እድል በመጠቀም ግጭትን በማቆም ለውይይት እንዲመርጡ ጠይቀዋል።

    ሁለቱም ወገኖች፤ “በቅን ልቦና እና ሳይዘገዩ በአፍሪካ ህብረት የሚመራውን ሂደት በንቃት እንዲሳተፉና ውይይቱ እንዲካሄድ ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ እናበረታታለን” ብለዋል ዋና ጸሃፊው፡፡

    ተመድ በአፍሪካ ህብረት የሚመራውን የሰላም ሂደት ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት በድጋሚ አረጋግጠዋል፡፡

    የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭትን በተመለከተ ተደጋጋሚ መግለጫዎች ስያወጣ የነበረው አውሮፓ ህብረት በበኩሉ የትግራይ ክልል መንግስት ጦርነቱ ባስቸኳይ እንዲቆምና በአፍሪካ ህብረት በሚመራው የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን መግለጹ በበጎ እንደሚመለከተው ገልጿል፡፡

    የአውሮፓ ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፕ ቦሬል በትዊተር ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ “እድሉ ሁሉም ሊጠቀሙበት ይገባል” ብለዋል፡፡

    ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ባወጣው መግለጫ ውጊያ ለማቆምና ያልተፈቱ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን ማስታወቁን “እናበረታታለን” ያሉት ደግሞ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒ ብሊንከን ናቸው፡፡

     “ኤርትራና ሌሎችም ግጭቱን ከማቀጣጠል ሊቆጠቡ ይገባል” ሲሉም አክለዋል፡፡

    አሜሪካ የኢትዮጵያን አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ትደግፋለች ያሉት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ አሜሪካ ከሀገሪቱ ጋር ወደነበራት “ጠንካራ አጋርነት” መመለስ እንደምትሻ ም አስታውቀዋል።

    ሌላው የትግራይ ክልል መንግስት ለውይይት ያወጣው መግለጫ ሚበረታታ መሆኑ የገለጸው ደግሞ፤ የኢትዮጵያ ሁኔታን በቅርበት ሲከታታል እንደነበር የገለጸው የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት /ኢጋድ/ ነው፡፡

    የኢጋድ ዋና ጸሃፊው ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በግጭት ውስጥ ያሉት ኃይሎች በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለሚደረግ የሰላም ንግግር ለመመለስ ባሳዩት ፈቃደኝነት መደሰታቸው ገልጸዋል፡፡

    “ኢጋድ ሁለቱም ወገኖች ለተኩስ ማቆምና ለሽምግልና ያሳዩት ቁርጠኝነት ይቀበላል”ም ነውም ያሉት ዋና ጸሃፊው፡፡

    በፌደራል መንግስቱ እና በህወሓት መካከል የነበረው ጦርነት ለወራት ጋብ ብሎ የነበረ ቢሆንም ጦርነቱ በድጋሚ ሊቀሰቀስ ችሏል፤ ጦርነቱን በመጀመር አንደኛቸው ሌላኛቸውን በመክሰስ ላይ ናቸው፡፡

    የኢትዮጵያ መንግስት በድጋሚ ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በየትኛው ቦታ ከህወሓት ጋር እንደሚደራደር መግለጹም ይታወሳል፡፡

    ህወሓትም በተመሳሳይ ለድርድር ዝግጁ መሆኑን ቢገልጽም ህወሓት በአፍሪካ ህብረት ላይ እምነት እንደሌላው ሲገልጽ ቆይቶ ነበር፡፡

    News today, Politics

    በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አሜሪካን እያዋረዷት እንደሆነ ትራምፕ ተናግረዋል

    አሜሪካ በአፍጋኒስታን 87 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸው ንብረቶችን ጥላ መውጣቷ ተገለጸ።

    የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዩ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ለመወዳደር ድጋፍ በማሰባሰብ ላይ ይገኛሉ።

      የቀድሞው ፕሬዝዳንት በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች እያካሄዱት ባለው በዚህ ቅስቀሳ ላይ እንዳሉት አሜሪካ በአፍጋኒስታን ጥላው የወጣችው ባግራም የተሰኘው ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ እጅግ ጠቃሚ እንደነበር ለጋፊዎቻቸው ተናግረዋል ሲል ራሺያን ቱዳይ ዘግቧል።

      ይህ ወታደራዊ ማዘዣ በተለይም አሜሪካ ከቻይና ጋር እያደረገች ላለው ወታደራዊ እና የንግድ የበላይነት ውድድር አስፈላጊ እንደነበር ጠቁመዋል።

      አሜሪካ ከፍተኛ በጀት ያፈሰሰችበት እና የቻይናን ኑክሌር መሰረተ ልማቶችን ለማጥቃት አመቺ ከሆነው ከባግራም ወታደራዊ ማዘዣ መውጣቷ ስህተት እንደሆነም የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጠቁመዋል።

      የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አመራር አሜሪካንን በዓለም መድረክ እያሳነሰ መሆኑን የጠቀሱት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ እና የአሜሪካ ወዳጆች ማሳዘኑንም ተናግረዋል።

      ኣሜሪካ ከአፍጋኒስታን መውጣቷ የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ትልቁ ስህተት መሆኑንም ዶናልድ ትራምፕ ገልጸዋል።

      አሜሪካ በአፍጋኒስታን 85 ቢሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸው ንብረቶችን ለታሊባን ጥላ መውጣቷን የቀድሞው ፕሬዝዳንት አክለዋል።

      አሜሪካ ከ20 ዓመት የአፍጋኒስታን ቆይታ በኋላ ለታሊባን ጥላ የወጣች ሲሆን አፍጋኒስታንን እያስተዳደረ የሚገኘው ታሊባን አንደኛ ዓመቱን ከሁለት ወራት በፊት ማክበሩ ይታወሳል።

      News today, Politics, social life

      የንግስት ኤልሳቤጥ ለ70 ዓመት የብሪታኒያ ንግስት ነበሩ

      የብሪታንያ ንግስት ኤልሳቤጥ በ96 ዓመታቸው ማረፋቸው ተገለፀ።

      ንግስቲቱ በስኮትላንድ ቤኪንግሀም ቤተ መንግሥት ማረፋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

      የንግስቲቱ የቀብር ስነ ስርዓት ከ10 ቀን በኋላ ክብራቸውን በጠበቀ መንገድ እንደሚከናወንም ተገልጿል።

      የንግስት ኤልሳቤትን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ ልዑል ቻርልስ የብሪታንያ በነገው ዕለት ንጉስ ሆነው እንደሚሾሙም ይጠበቃል።

      ላለፉት 70 ዓመታት የብሪታንያ ንግስት የነበሩት ንግስት ኤልሳቤት በ96 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል።

      ንግስቲቱ በኮሮና ቫይረስ እንዳይጠቁ የእንግሊዝ መንግሥት ልዩ ጥበቃ ሲያደርግላቸው ቆይቶ ነበር።

      ከትናንት በስቲያ የብሪታንያ አዲሷን ጠቅላይ ሚንስትር ሊዝ ትሩስን ሹመት ያጸደቁት ንግስቲቱ ዛሬ ከሰዓት መጠነኛ ህመም ከተሰማቸው በኋላ ምሽት ላይ ህይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል።

      በመላው ብሪታንያ ሀዘን ላይ የወደቁ ሲሆን የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላም ዝቅ ብሎ ከመውለብለቡ ባለፈ የብሪታንያ ብዙሀን መገናኛዎች ሌሎች ጉዳዮችን መዘገብ አቁመዋል።

      News today, social life

      በኮንጎ ሪባን በመቁረጥ ሰነ-ስርዓት ወቅት ድልድይ መደርመሱ አነጋገረ

      በኮንጎ ሪባን በመቁረጥ ሰነ-ስርዓት ወቅት ድልድይ መደርመሱ አነጋገረ
      September 7, 2022
      በኮንጎ ሪባን በመቁረጥ ሰነ-ስርዓት ወቅት የተደረመሰው ድልድይ አነጋጋሪ ሆኗል


      ድልድዩን ሊመርቁ የተገኙ የክብር እንዶች ድልድዩ ላይ ቆመው ሪባን በሚቆርጡበት ወቅት ድልድዩ ተደርምሷል፡፡ ሮይተርስ አረጋግጫለሁ ባለው ተንቀሳቃሽ ምስል ድልድዩ የሚመረቀው በኮንዶ ዋና ከተማ ሲሆን የምርቃት ሪባን የሚቆርጡ ሰዎች በድልድዩ ላይ በቆሙበት ወቅት ድልድዩ ሊደረመስ ችሏል፡፡


      ተንቀሳቃሽ ምስሉ በቦታው የተገኙት ሰዎች በግርምት ሲመለከቱ ይታያሉ፡፡
      ድልድዩ የእጅ መያዣዎቹን ጨምሮ ማእከላዊ አካሉ ተደርምሶ ከሁለት ሜትር ርቀት ላይ ማረፉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡


       ለምርቃቱ የመጡት የክብር እንግዶች ከአደጋው ለማምለጥ ሲታገሉ በቦተው የነበሩ ተመልካቾች ሲስዉ ታይተዋል፡፡ በአደጋው የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል፡፡
      ተንቀሳቃሽ ምስሉ በሰፊው የተሰራጨ ሲሆን ክስተቱ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡

      News today

      በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ኡሙሩ ወረዳ በታጠቁ ቡድኖች ከ60 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለፀ

      ከ20 ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ወደ ኦቦራ ከተማ መፈናቀላቸውንም ኮሚሽኑ አስታውቋል

      ኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ኡሙሩ ወረዳ በታጠቁ ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለፀ።

      ኢሰመኮ ዛሬ ባወጣው መግለጫው በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ስር በሚገኘው ኡሙሩ ወረዳ ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸሙ ጥቃቶች በርካታ ነዋሪዎች መገደላቸውን፣ መቁሰላቸውን እና መፈናቀላቸውን አስታውቋል።

      በዚህም በነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ አገምሳ ቀበሌ “ኦነግ ሸኔ” ተብሎ የሚጠራ ታጣቂዎች ኦቦራ ከተማን ለመያዝ ባደረጉት እንቅስቃሴ ሦስት የአማራ ብሔር ተወላጆች መግደላቸውን አሰታውቋል።

      ይህንን ተከትሎ ከኡሙሩ ወረዳ፣ ሀሮ አዲስ ዓለም ከተባለ ቀበሌ እና አጎራባች ከሚገኘው የአማራ ክልል፣ ቡሬ ወረዳ የተውጣጡ ታጣቂዎች በኡሙሩ ወረዳ በሚገኙና አገምሳ፣ ጆግ ምግር፣ ታም ኢላሙ፣ ጀቦ ዶባን፣ ጦምቤ ዳነጋበ፣ ጃዋጅ፣ ኛሬ፣ ለገ ሚቻ፣ ሉቁማ ዋሌ በሚባሉ ቀበሌዎች የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ነዋሪዎች ላይ ነሐሴ 24 እና 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ጥቃት ተፈጽሟል ብሏል።

      በእነዚህ ሁለት ቀናት በተደረጉ ጥቃቶች ከ60 በላይ ሰዎች መገደላቸውን፤ ከ70 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን፣ የነዋሪዎች የቤት ንብረቶች እና የቀንድ ከብቶች መዘረፋቸውን ኮሚሽኑ ካነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች እና የመንግሥት ኃላፊዎች ለመረዳት መቻሉን አመላክቷል።

      ጥቃት ከተፈጸመባቸው ቀበሌዎች መካከል አሁንም ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች መኖራቸውን እና በጥቃቱ ምክንያትም ከ20 ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ተፈናቅለው በኦቦራ ከተማ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

      በተጨማሪም በጥቃቶቹ ምክንያት የተፈጠረው የደኅንነት ስጋት ያልተቀረፈ መሆኑን እና በዞኑ ውስጥ ካሉት ወረዳዎች መካከል በጃርደጋ ጃርቴ፣ ኪረሙ እና በአቤ ዶንጎሮ ወረዳዎች ተመሳሳይ ጥቃቶች ሊፈጸሙ እንደሚችሉ ስጋቶች መኖራቸውን ኮሚሽኑ ከነዋሪዎች ያሰባሰባቸው መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል፡፡

      በሲቪል ሰዎች ላይ ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው ተሰማርቶ የነበረ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ወደ ሌላ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ መሆኑን ኮሚሽኑ በመግለጫው አክሏል።

      ኮሚሽኑ ጥቃት በተፈጸመባቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ እና ሰላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ ነዋሪዎችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት የመመለስና ተገቢውን ምርመራ አድርጎ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ ሥራ እንዲሠራ አሳስቧል።

      የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ኮሚሽኑ ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል መሆኑንና በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸመው አሳዛኝ ጥቃት ያሳሰበው መሆኑን ገልጸው፤ በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ስጋት ካለባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ወደ ሌላ ቦታ በሚዘዋወሩበት ወቅት የነዋሪዎች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነት እና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ ተገቢ የሆኑ ጥንቃቄዎች ሊደረጉ እንደሚገባ በድጋሚ አስታውሰዋል።

      News today, social life

      በቻይና በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 ደረሰ

      በቻይና ሲቹዋን ግዛት በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል

      በቻይና በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 ደርሷል፡፡

      ከፈረንጆቹ 2017ወዲህ በቻይና ደቡብ ምእራብ በምትገኘው ሲቹዋን ግዛት በተከሰተው ጠንካራ ነው በተባለው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 65 መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

      የነፍስ አድን ሰራተኞች በአስቸካሩ ሆኔታ ውሰት ሉ ሰዎችን ለማውጣት እና መሰረታዊ አገልግቶችን ለለመረስ እየሰሩ መሆናቸውንም ሀገባው ጠቅሷል፡፡

      በአደጋው ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው 250 ሰዎች ህክም እየተደረገላቸው ይገኛል፤ ከተጎጅዎች መካል 10 የሚሆኑት ከባድ አደጋ የደረሰባቸው ናቸው ተብሏል፡፡

      የነፍስ አድን ሰራተኞች ህይወታቸው ለአደጋ የተጋለጡ 200 ሰዎች ለማውጣት፣ ቴለኬኮሙኒኬሽንን፣ መብራት እና የውሃ አገልግሎቶችን ለመመለስ በመጣደፍ ላይ ናቸው፡፡

      ሮይተርስ የቻይና ሚዲያዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው የነፍስ አድን ሰራተኞቹ በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 በሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ለተጎዱ ሰዎች የምግብ አቅርቦት እያደረሱ ነው፡፡

      በሲቹያን ግዛት የተከሰተው ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እስከ ግዛቷ ተራራ ቦታዎች ድርስ ንዝረቱ መሰማቱን ዘገባው ገልጿል፡፡

      News today, Politics

      ሩሲያ የተጣሉባት ማዕቀቦች ካልተነሱ ወደ አውሮፓ ነዳጅ እንደማትልክ ገለጸች

      የቡድን ሰባት አባል ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ የዋጋ ተመን ማውጣታቸው ይታወሳል

      ሩሲያ የተጣሉባት ማዕቀቦች የማይነሱ ከሆነ ወደ አውሮፓ ነዳጅ እንደማትልክ ገልጻለች።

      የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስድስት ወራት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ በዓለም ምግብ እና ነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ እንዲመዘገብ ምክንያት ሆኗል።

       ጦርነቱ በዓለም ዲፕሎማሲ ላይ የተለያዩ መፋለሶችን ያስከተለ ሲሆን ሀገራት ከትብብር ይልቅ ጎራ ለይተው እንዲሰለፉ እያደረገም ይገኛል።

      አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ላይ በተለያየ መንገድ በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ በሩሲያ ላይ ከስድስት ሺህ በላይ ማዕቀቦችን ጥለዋል።

      ሩሲያም የአጸፋ እርምጃ በመውሰድ ላይ ስትሆን ማዕቀቡ ለአውሮፓ ሀገራት የምታቀርበውን ጋዝ ሽያጭ እክል አስከትሏል።

      ይሄንን ተከትሎም 40 በመቶ ለሚሆኑ የአውሮፓ ሀገራት ነዳጅ ስታቀርብ የነበረችው ሩሲያ በማዕቀቡ ምክንያት ለአውሮፓውያን ነዳጅ መላክ አለመቻሏን በተደጋጋሚ ገልጻለች።

      በነዳጅ ዕጥረት እየተፈተነ ያለው የአውሮፓ ህብረትም በሩሲያ ላይ የጣለውን ማእቀብ እስከማላላት ቢደርስም በሩሲያ ላይ የተጣሉት ሁሉም ማዕቀቦች እስካልተነሱ ድረስ ሩሲያ ምንም አይነት ነዳጅ እንደማትልክ ራሺያ ቱዴይ ዘግቧል።

      የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የአውሮፓ ሀገራት እና ኩባንያዎች በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ሳይነሳ አንዲት ጠብታ ነዳጅ አንልክም ሲሉ ተናግረዋል።

      የአውሮፓ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆኑት ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ብሪታንያ፣ ቤልጂየም እና ሌሎች ሀገራት በነዳጅ ዕጥረት እየተፈተኑ ናቸው ተብሏል።

      እነዚህ ሀገራት ሩሲያ ነዳጇን እንደጦር መሳሪያ እየተጠቀመችበት ነው ሲሉም ሞስኮን ከሰዋል።

      የዓለማችን ሰባቱ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆኑት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ከሰሞኑ  በሩሲያ ነዳጅ ላይ የዋጋ ተመን ማውጣታቸው ይታወሳል።

      እነዚህ ሀገራት ሩሲያ ነዳጇን በተተመነላት ዋጋ መሰረት ለአውሮፓ ሀገራት እንድትሸጥ የወሰኑ ቢሆንም ሩሲያ በበኩሏ ምንም አይነት ነዳጅ ወደ አውሮፓ አልሸጥም የሚል ውሳኔ አሳልፋለች።

      News today, Technology

      አሜሪካ ቲክቶክን ጨምሮ በሌሎች የቻይና ኩባንያዎች ላይ እገዳ ልትጥል እንደምትችል ተገለጸ

      እገዳዎቹ የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በአሜሪካ እንዳይሰሩ ማድረግንም ይጨምራል

      አሜሪካ ቲክቶክን ጨምሮ በሌሎች የቻይና ኩባንያዎች ላይ እገዳ ልትጥል እንደምትችል ተገለጸ።

      ሁለቱ የዓለማችን ባለ ብዙ ሀገራት አሜሪካ እና ቻይና የማይግባቡባቸው አጀንዳዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል።

      ሁለቱ ሀገራት በተለይም በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአስተዳድር ጊዜ ከቻይና ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ ገብተው የነበረ ሲሆን ሁለቱም ወገኖች ወደ ሀገራቸው በሚገቡ ምርቶች ላይ እገዳዎችን ሲጥሉ ነበር።

      በታይዋን ጉዳይ እንደ አዲስ መካረር ውስጥ የገቡት ቻይና እና አሜሪካ አሁን ደግሞ ከምርት እገዳ ወደ ተቋማት እገዳ እየገቡ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።

      አሜሪካ በተለይም በፍጥነት እያደጉ የመጡ የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ስጋት ላይ የጣሏት ሲሆን ቲክቶክ ደግሞ ዋነኛው ነው።አሜሪካ አጫጭር ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በመልቀቅ ተወዳጅ የሆነው የቻይናው ቲክቶክ በአሜሪካ እገዳ ሊጣልበት እንደሚችል ዘገባው ጠቅሷል።

      የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና ቲክቶክን ለአሜሪካ ኩባንያዎች ካልሸጠች እገዳ እንጥላለን ማለታቸው ይታወሳል።የአሁኑ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳድርም ቲክቶክ ኩባንያን ጨምሮ ሎሎች የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በአሜሪካ እንዳይሰሩ እገዳ እንደሚጥል ተገልጿል።

      እገዳው የሚጣልባቸው የቻይና ኩባንያዎች ማንነት፣ የእገዳው መጠን እና አይነትን በሚመለከት ኋይት ኃውስ መንግስት እና የአሜሪካ ኮንግረስ በውይይት ላይ እንደሆኑ ተገልጿል።

      አሜሪካ ከአንድ ሳምንት በፊት መነሻቸውን ከቻይና ያደረጉ 44 በረራዎች ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ እገዳ መጣሏ ይታወሳል።

      News today, Technology

      ቻይና “አሜሪካ 10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ፈጽማብኛለች” አለች

      ቻይና የተፈፀመባት የመረጃ ጠለፋ በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም የተመራ ነው ብላለች

      የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ተቋም በቅርብ ዓመታት ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃቶቸን እንደፈጸመባት ቻይና ገለጸች።

      በአሜሪካ የሳይበር ጥቃቶችም 140 ጊጋ ባይት ጠቃሚ መረጃዎች መሰረቃቸው እንዳልቀረ የቻይና ብሄራዊ የኮምፒውተር ቫይረስ ግብረ መልስ ኃይል እና ኪሆ የተባለው የኢንተርኔት ደህንነት ተቋም ባጋራ ባካሄዱት ምርመራ አስታውቀዋል።

      ተቋማቱ ምርመራውን ማካሄድ የጀመሩት የቻይና ሰሜናዊ የፖሊ ቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር ላይ የሳይበር ጥቃት እንደተፈፀመበት ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

      ተቋማቱ ጥቃቱን የፈፀመውን ኔትዎርክት ዱካ ተከትለው ባደረጉት ምርመራም ጠላፊው በአሜሪካው ብሄራዊ ደህንነት ተቋም አካል በሆነው ትሮይድ አክሰስ ኦፕሬሽን ቢሮ እንደተፈጸመ ደርሰንበታል ብለዋል።

      በዩኒቨርሲቲ ላይ በተፈፀመው የሳይበር ጥቃት በቀጥታ 13 ሰዎች መሳተፋቸው እና የመረጃ ጠላፊዎ የዩኒቨርሲቲዉን የመረጃ ደህንነት መጠበቂያ (ፋየርዎል) ለማለፍ ከ41 በላይ መሳሪያዎችን መጠቀማቸው ተነግሯል።

      ጠላፊዎቹ ማንነታቸውን ለመሸፈን ኢራን፣ ደቡብ ኮሪ እና ጃፓንን ጨምሮ በ17 ሀገራት አይ.ፒ እቀያየሩ ሲጠቀሙ ነበርም ብሏል ተቋማቱ ባወጡት መረጃ።

      ምርመራውያን ያካሄዱት ተቋማት ወደፊት የአሜሪካ የመረጃ ጠለፋ እና የስለላ ዘዴቆች እና መሰሳሪያዎችን ዝርዝር ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

      የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርመራ ውጤቱን ተከትሎ ምለሽ ሰጠ ሲሆን፤ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ፤ ቻይና ኢንዲህ አይነት ተጋባራትን በጽኑ ታወግዛለች ብለዋል።

      አሜሪካ ከሳይበር ጥቃት ተግበሯ ልትታቀብ ይገባል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ቻይና የኔትዎርክ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከዓለም አቀፉ ማህበረስበ ጋር ትሰራለች ሲሉም ተናግረዋል።

      News today, Politics

      ሩሲያ የከባድ መሳሪያ ተተኳሾችን ከሰሜን ኮሪያ እየገዛች ነው ተባለ

      ሩሲያ በበኩሏ ኢኮኖሚዋ በመሻሻል ላይ መሆኑን አስታውቃለች

      ሩሲያ የከባድ መሳሪያ ተተኳሾችን ከሰሜን ኮሪያ እየገዛች ነው ተባለ፡፡

      ኒዮርክ ታይምስ የአሜሪካ የስለላ ተቋም መረጃን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከሆነ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገች ባለው ጦርነት ምክንያት የጦር መሳሪያ እጥረት አጋጥሟታል፡፡

      ሩሲያ የየከባድ ጦር መሳሪያ ተተኳሽ እጥረት ያጋጠማት በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት በተጣለባት ማዕቀብ እንደሆነ የጠቀሰው ዘገባው እጥረቱን ለማስታገስ ስትልም ከሰሜን ኮሪያ በመግዛት ላይ መሆኗንም ጠቅሷል፡፡

      አሁን ላይ ሩሲያ ሮኬቶች እና ሌሎች የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያዎችን ለመግዛት ተገዳለች ያለው ዘገባው ጦርነቱ በቀጠለ ቁጥር የጦር መሳሪያውም የበለጠ እያጠራት እንደሚሄድ አመላክቷል፡፡

      ባሳለፍነው ሳምንት ሩሲያ ኢራን ሰራሽ ድሮኖችን ከቴህራን መግዛቷን የገለጸው ዘገባው ሩሲያ በአሜሪካ ማዕቀብ ከተጣለባቸው ሀገራት ጋር ግንኙነቷን እያጠበቀች መጥታለችም ብሏል፡፡

      የሰሜን ኮሪያ ፕሬዝዳንት ኪም ጆንግ ኡን በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መጀመር ዋነኛዋ ተጠያቂ አሜሪካ እንደሆነች ከዚህ በፊት ተናግረው ነበር፡፡

      ፕሬዝዳንቱ ከዩክሬን ወደ ሩሲያ ለተጠቃለሉ ዶምባስ እና ሉሃንስክ ግዛቶች ሉዓላዊነት ቀድመው እውቅና ከሰጡ ሀገራት መካከል ሰሜን ኮሪያ አንዷ ስትሆን ሶሪያ ደግሞ ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡

      ሩሲያ በበኩሏ በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት ከስድስት ሺህ በላይ ማዕቀቦች ቢጣሉብኝም ማዕቀቦቹ በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ ያደረሱት ተጽዕኖ ሁለት በመቶ ብቻ መሆኑን አስታውቃለች፡፡

      የሞስኮ መገበያያ የሆነው ሩብል ከአሜሪካው ዶላር ጋር ሲነጻጸር ከዚህ በፊት ከነበረው ልዩነት መቀነሱን እና የሩሲያ የወጪ ንግድም ጉድለት አለማሳየቱ ተገልጿል፡፡

      የፊንላንዱ የምሁራን ስብስብ ተቋም ባወጣው ጥናት ምዕራባዊያን በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ጥቂት ጉዳት ብቻ ማድረሱን ጠቅሶ ሩሲያ በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ 136 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን አስታውቋል፡፡

      News today, Politics

      ፑቲን የቻይና ጦር የተሳተፈበትን “ቮስቶክ 2022” የጦር ልምምድ ላይ መገኘታቸው ተገለጸ

      በቮስቶክ 2022 የጦር ልምምድ ከ14 ሀገራት የተውጣጡ 50 ሺህ ወታደሮች ተሳታፊ ሆነዋል

      ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ቻይናን ጨምሮ በርካታ ሀገራት በሚሳተፉበት በግዙፉ የ“ቮስቶክ 2022” የጦር ልምምድ በሚካሄድበት ካቦራቭስክ ወታደራዊ ስፍራ መገኘተቻው የክሬምሊን ቃል አቀባይ ደሚትሪ ፔስኮቭ ገለጹ፡፡

      ፕሬዝዳንት ፑቲን በልምምድ ስፍራው የተገኙት ከመከላከያ ሚኒስትሩ ሰርጌይ ሾይጉ እና ከወታደራዊው አዛዥ ቫለሪ ገራሲሞቭ ጋር መሆኑን ቃል አቀባዩ፤ አስታውቀዋል።

      ፕሬዝዳንቱ ለሳምንት የዘለቀውን ልምምድ የመጨረሻ ምዕራፍ እንደሚከታተሉ መገለጻቸውም ዘ-ጋርዲያን ዘግቧል፡፡

      በሩሲያ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ግዙፉ ቮስቶክ 2022 የጦር ልምምድ ባሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ እንደተጀመረ ሚታወስ ነው፡፡

      ቮስቶክ 2022 የሚል መጠሪያ የተሰጠውና በሩቅ ምስራቅ ሩሲያ እና በጃፓን ባህር ላይ ሲካሄድ የቆው ወታደራዊ ልምምድ በነገው እለት እንደሚጠናቀቅም ነው የተገለጸው፡፡

      በወታደራዊ ልምምዱ አዘጋጇ ሩሲያን ጨምሮ ቻይና፣ ቤላሩስ፣ ታጃኪስታን፣ ህንድ እና ሞንጎሊያን ጨምሮ በድምሩ 14 ሀገራት ተሳትፈዋል።

      በልምምዱ ከሀገራቱ የተውጣጡ 50 ሺህ ወታደሮች የተሳተፉ ሲሆን፤ የረጅም ርቀት ቦምብ ጣይ ጄቶ እንዲሁም የጦር ካርጎ አውሮፕላኖኖች የተካተቱባቸው ከ5 ሺህ በላይ የተለያዩ አይነት የጦር መሳሪያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

      ከጦር መሳሪያዎቹ መካከልም 140 የጦር አውሮፕላኖች እና 60 የጦር መርከቦች እንደሚገኙበትም ነው የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር መረጃ የሚያመለክተው፡፡

      በዚህ የጦር ልምምድ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ቻይና ፤ የጦር ልምምዱ ከወቅቱ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር እንደማይገናኝ መግለጿ ይታወሳል።

      መሰል ወታደራዊ ልምምድ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ የመጀመሪው የጦር ልምምድ እንደፈረንጆቹ 2018 መካሄዱ አይዘነጋም፡፡

      News today, Technology

      ሁዋዌይ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሳተላይት የሚሰራ ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ አደረገ

      ሁዋዌይ ሜት 40 ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ይፋ የተደረገው

      የቻይናው የቴክኖሎጂ ቁሶች አምራች ሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልኩን በዛሬው እለት ይፋ ማድረጉ ተነግሯል።

      አዲሱ የህዋዌይ ስማርት ስልክ ከዚህ በፊት በስማርት ስልኮች ላይ ያልተለመደ የሳተላይት ኮሙዩኒኬሽን የተገጠመለት መሆኑን ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል።

      በዚህም ስማርት ስልኩ ከጂ.ፒ.ኤስ ተመሳሳይነት ባለው በቻይናው ቤይ-ዶው ናቪጌሽን ሳተላይት ሲስትም (BDS) ኔትዎርክ አማኝነት በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚባይል ኔትዎርክ ባይኖርም መስራት ይችላል።

       በተጨማሪም አዲሱ ሜት 50 ስማርት ስልክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአሜሪካው የጎግል አንድሮይድ ስማርት ስልክ በመላቀቅ ቻይና በራሷ ባመረተችው አዲስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ለገበያ የሚቀርብ ይሆናል ነው የተባለው።

      ይህም ባትሪው ሊዘጋ 1 ፐርሰት እየቀረው 3 ሰዓት እንደቆይ ማድረግ እንደሚያስችልም ኩባያው አስታውቋል።

      አዲሱ የሁዋዌይ ሜት 50 ስማርት ስልክ የባትሪ አቅም 4460 mAh መሆኑን ኩባያው አስታውቋል።

      ስማርት ስልኩ ከጀርባው 4 የካሜራ ሌንሶች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሌንሶቹም 50 ሜጋ ፒክስል፣ 13 ሜጋ ፒክሰል እና 12 ሚክስል ናቸው።

      ከፊትለፊት አሊያም ሰለፊ ካሜራው ደግሞ 1 ሲሆን፤ የሌንሱ ምስል የማንሳት ጥራትም 13 ሜጋ ፒከስል ነው ተብሏል።

      ሁዋዌይ ሜት 40 የተባለ ስማርት ስልክን ከለቀቀ ከ2 ዓመት በኋላ ነው ሜት 50 ስማርት ስልክ ይፋ የተደረገው።

      በርካቶቸ ሁዋዌይ ስማርት ስልኩን ይፋ ሳያደርግ ይህን ያክል የቆየው አሜሪካ በኩንያው ላይ በጣለችው ማእቀብ ሳቢያ ሳይሆን እንዳልቀረ ያምናሉ።

      News today

      #Update የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ተመረጡ። የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሊዝ ትረስ አዲሷ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመርጠዋል። ትረስ እድሜያቸው 47 ሲሆን የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ሆነዋል። ሶስተኛዋ የሀገሪቱ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትርም እንደሆኑ ተገልጿል። ትረስ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ሪሺ ሱናክን ሲሆኑ ያሸነፉት 57.4% ድምፅ በማግኘት እንደሆነ ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

      #Update

የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ተመረጡ።

የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሊዝ ትረስ አዲሷ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመርጠዋል።
 
ትረስ እድሜያቸው 47 ሲሆን የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ሆነዋል።

ሶስተኛዋ የሀገሪቱ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትርም እንደሆኑ ተገልጿል።

ትረስ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ሪሺ ሱናክን ሲሆኑ ያሸነፉት 57.4% ድምፅ በማግኘት እንደሆነ ዶቼ ቨለ ዘግቧል።
      News today, social life

      ሱዳን በጎርፍ ተጥለቀለቀች

      በመስከረም ወር ተጨማሪ ዜጎች ለጎርፍ አደጋ ሊጋለጡ እንደሚችሉ ተገልጿል

      በሱዳን በጎርፍ የተወሰዱ ሰዎች 112 ደርሷል።

      በሱዳን ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 112 ማሻቀቡን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

      የዓባይ ወንዝ የውሃ መጠን በመጪዎቹ ቀናት የበለጠ ሊጨምር እንደሚችልም የገለፁት የሃገሪቱ የአደጋ መከላከል ባለስልጣናት አስጠንቅቀዋል።

      በሱዳን በጎርፍ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 100 ደረሰ
      ባለስልጣናቱ በዚህ ወር ብቻ ባጋጠመ አደጋ 112 ሱዳናውያን መሞታቸውንና 115 ሰዎች ደግሞ መጎዳታቸውን አስታውቀዋል።በድምሩ 84 ሺ 40 ቤቶች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መውደማቸው እና መጎዳታቸውንም ተናግረዋል ባለስልጣናቱ።

      መሠል የጎርፍ አደጋዎች ለሱዳን አዲስ አይደሉም። ክረምት በመጣ ቁጥርም ያጋጥማል። ሆኖም ዘንድሮ በ1940ዎቹ ካጋጠመውና የከፋ ነበር ከተባለለት የበለጠ የጎርፍ አደጋ ማጋጠሙ ነው የተነገረው።

      አደጋው ካለፉት ሁለት የክረምት ወራት ይልቅ በነሐሴ እና መስከረም ወራት ይከፋል መባሉም ብዙዎችን አስግቷል።

      የጎርፍ አደጋው በስድስት ግዛቶች እየከፋ የመጣ ሲሆን የሀገሪቱ ወታደራዊ መንግስትም በነዚህ ግዛቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል።

      ናይል፣ ዋይት ናይል፣ ኮርዶፋን፣ ዳርፉር እና ካሳላ ግዛቶች በጎርፍ አደጋው ክፉኛ ተጎድተዋል ተብሏል፡፡

      እስካሁን ባለው የጎርፍ አደጋ ከ250 ሺህ በላይ ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን በቀጣዮቹ ሳምንታት ተጨማሪ ጉዳት ሊከሰት እንደሚችል ተጠቅሷል።

      News today, Politics

      ሰሜን ኮሪያ ጥላትን ለማሳሳት በማለት 8 አንድ አይነት ቤተመንግሥት ሰራች


      2022/8/29 11:38 GMT

      ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን

      ቤተ መንግስቶቹ ተመሳስለው የተገነቡት ፕሬዝዳንቱ ያሉበት እንዳይታወቅ እንደሆነ ተገልጿል

      ከምዕራባዊያን ጋር እሰጣ አገባ ውስጥ ያለችው ሰሜን ኮሪያ ጠላትን ለማሳሳት በሚል ስምንት ተመሳሳይ ቤተ መንግስቶችን መገንባቷ ተገልጿል።

      እንደ ዴይሊ ሜይል ዘገባ ከሆነ ሰሜን ኮሪያ የፕሬዝዳንት ኪም ጆን ኡን ደህንነትን ለመጠበቅ ሲባል በሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ ተመሳሳይ ቅርጽ ያላቸው ቤተመግስቶችን ገንብታለች።

      ሰሜን ኮሪያ በጎረቤቷ ደቡብ ኮሪያ አማካኝነት እና በምዕራባዊያን የተቀናጀ ጥረት በፕሬዝዳንቱ ላይ ግድያ ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት አላት።

      ይሄንን ስጋቷን ለማስወገድ እና ፕሬዝዳንቷን ለመጠበቅ ተመሳሳይ ቅርጽ፣ የቀለም ቅብ፣ መሰረተ ልማት እና ሌሎች ሚስጢራዊ ግንባታዎችን የያዘ ቤተ መንግስት መገንባቷን ዴይሊ ሜጠይል የሳተላይት ምስሎችን ዋቢ አድርጓል።

      እነዚህ ቅንጡ ስምንት ቤተ መንግስቶች በመሃል ፒዮንግያንግ ቻንግ ክዋንግሳን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሀገሪቱ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት መገንባቱ ተገልጿል።

      ቤተ መንግስቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች ለሌሎች የሀገሪቱ ዜጎች ዝግ መሆኑን ተከትሎ አካባቢው “የተከለከለ ከተማ” ወይም ፎርቢድን ሲሰቲ የሚል ስምም ተሰጥቶታል ተብሏል።

      የሰሜን ኮሪያ ሀገራዊ ሚስጢራት እና ወታደራዊ እቅዶች በነዚህ ቤተመንግስቶች ውስጥ እንደሚረቀቁም ተገልጿል።

      ፕሬዝዳንት ኪም እና አስተዳድራቸው በሰሜን ኮሪያ ዋነኛ ስጋቷ ከሀገሬው ህዝብ ወይም ፖለቲከኞች ሳይሆን ከውጭ ሀገራት የሚሰነዘር እንደሚሆን እርግጠኛ ናቸው።

      ይሄንንም ስጋት ለመቀልበስ ጥቃቱ በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እና ወታደራዊ ተቋማቸው ላይ ስለሚሆን ጠላቶችን ለማሳሳት አጠቃላይ እንቅስቃሴያቸውን ገድበው በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው ተብሏል።

      ፕሬዝዳንት ኪም ራሳቸውን እና ሀገራቸውን ከአደጋ ለመጠበቅ በጠዋት እና በምድር ውስጥ የተዘጋጁ መጓጓዣዎችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

      ፕሬዝዳንት ኪም ከሀገሪቱ መዲና ፒዮንግያንግ ከተማ በተጨማሪ በመላው የሀገሪቱ ክፍል 13 ቤተ መንግስቶች አሏቸው የተባለ ሲሆን እነዚህ ቤተመንግስቶች በወዳጆቻቸው እና ዘመዶቻቸው ይጠበቃሉም ተብሏል።

      News today, Politics

      ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ ነው

      ጀርመን ወደ ሞስኮው ልኡክ የምትልከው ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከሩሲያ ጋር ለመምከር ነው
      ጀርመን የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ወደ ሩሲያ ልትልክ መሆኑ ተሰምቷል።

      ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦርን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲጠያ ጋር በተቀሰቀሰው ጦርነት የዓለም ነዳጅ ዋጋ አሻቅቧል።
      40 በመቶ የነዳጅ ፍጆታቸውን ከሩሲያ የሚሸምቱት አውሮፓዊያን በዩክሬን ጉዳይ አጣብቂኝ ውስጥ ወድቀዋል።

      ከአውሮፓ ሀገራት መካከል ጀርመን ደግሞ የሩሲያ ነዳጅ ጥገኛ ከሆኑ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነዳጅ እንደበፊቱ ማግኘት አልቻለችም።

      በዚህም ምክንያት የፕሬዝዳንት ፑቲን ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የቀድሞቀው የጀርመን ፕሬዝዳንት በጌራልድ ሽሮደር የሚመራ ልኡክ ወደ ሞስኮ ልትልክ መሆኑን አስታውቃለች።

      የወቅቱ የጀርመን ፕሬዝዳንት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ወደ ጀርመን የምትልከውን ነዳጅ መጠን እንዳትቀንስ የሚያግባባ ልኡክ ወደ ሞስኮ እንደሚልኩ ሮይተርስ ዘግቧል።

      ይህን በነዳጅ ግብይት ዙሪያ ለመምከር ወደ ሞስኮ የሚያቀናውን ልኡክ የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሾልደር ሊመሩት እንደሚችሉ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

      ወደ ሞስኮ የሚያቀናው የጀርመን ልኡክም በዋናነት ተልዕኮው ሩሲያ በኖርድ ስትሪም አንድ ተብሎ በሚጠራው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ነዳጅ በበቂ መጠን እንድትልክ ማግባባት እንደሚሆን ተገልጿል።

      የቀድሞው የጀርመን ፕሬዝዳንት ጌራልድ ሽሮደር ወደ ሞስኮ አቅንተው ፕሬዝዳንት ፑቲንን ያገኙ ሲሆን የጀርመን መንግስት ከዚህ በፊት ነዳጅ ከሩሲያ የሚያገኝበት ኖርድ ስትሪም አንድን ትቶ ወደ ሁለት እንዲያተኩር አሳስበው ነበር።

      ጌራልድ ሽሩደር ጀርመንን ከፈረንጆቹ 1998 ጀምሮ እስከ 2005 ድረስ በፕሬዝዳንትነት ማገልገላቸው አይዘነጋም።

      የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 170ኛ ቀኑ ላይ ሲሆን እስካሁን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ሀገራቸውን ጥለው ወደ ጎረቡት ሀገራት መሰደዳቸውን ተመድ ከሰሞኑ ገልጿል።

      News today, Politics

      ጀርመን በማሊ ያሰማራችውን ሰላም አስከባሪ ጦር ልታስወጣ መሆኗን አስታወቀች

      ጀርመን በባማኮ የነበራትን ሰላም ማስከበር ስራ ያቋረጠችው ማሊ ከሩሲያ ጋር መስራቷን ተከትሎ ነው
      ጀርመን በማሊ ያሰማራችውን ሰላም አስከባሪ ጦር ልታስወጣ መሆኗን አስታወቀች።

      የአውሮፓ ሀገራት ከዘጠኝ ዓመት በፊት በምዕራብ አፍሪካ የሽብርተኞችን ጥቃት ለመከላከል በሚል በፈረንሳይ አስተባባሪነት ለሚመራው የተመድ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ጦራቸው አዋጥተው ነበር።

       ማሊ፣ቡርኪና ፋሶ፣ኒጀር እና ቻድ ደግሞ ከአምስት ሺህ በላይ የአውሮፓ ሀገራት ጦር የሰፈረባቸው ሀገራት ናቸው፡፡
      ይሁንና በማሊ በኮለኔል አስሚ ጎይታ የሚመራው ወታደራዊ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ምዕራባውያን ሀገራት ደስተኛ ሊሆኑ አልቻሉም።

      ጀርመንም ከነዚህ ሀገራት መካከል ወነኛዋ ስትሆን የሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች በማሊ መታየታቸውን ተከትሎ ወታደሮቿን ከማሊ ለማስወጣት መወሰኗን የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።

      የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ክሪስቲን ላምምበርችት እንዳሉት ከምንም በላይ የወታደሮቻችን ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል ።

      ጀርመን ከአንድ ወር በፊት 60 ወታደሮቿን ከማሊ ያስወጣች ሲሆን የማሊ ወታደራዊ መንግሥት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ስጋት እንደደቀነባቸውም ተገልጿል።

      የማሊ ወታደራዊ መንግሥት ከዚህ በፊት የምዕራባውያን ሀገራት በሰላም ማስከበር ስም በርካታ ሰራዊት መስፈራቸውን እና የማሊን ሉዓላዊነት ሊጥሱ እንደማይገባ ገልጾ ነበር
      ለተመሳሳይ ተልዕኮ በሚል በማሊ በሶስት ካምፖች ሰፍሮ የነበረው የፈረንሳይ ጦር ከወራት በፊት ለቆ መውጣቱ ይታወሳል።

      የፈረንሳይ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እስካለፈው ሰኔ ወር ድረስ በምእራብ አፍሪካ አገራት ያለውን አብዛኛውን ጦር ወደ ፓሪስ የመመለስ እቅድ መያዙን ከዚህ በፊት መናገራቸውም አይዘነጋም፡፡
      የአውሮፓ አገራት ሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሳህል ቀጠና የሚሰማራው ከምዕራብ አፍሪካ አገራት ወደ አውሮፓ በመሻገር የሽብር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ያለመ ነበር ተብሏል፡፡

      የማሊ እና ቡርኪናፋሶ ዜጎች ከዚህ በፊት በተለያዩ ከተሞች የፈርንሳይ ጦር አገራቸውን ለቀው እንዲወጡ የሚጠይቁ ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄዳቸው ይታወሳል፡፡ 

      News today, social life

      ደቡብ ኮሪያ ለሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ዋና አስተዳዳሪ ምህረት አደረገች


      አስተዳዳሪው ፈጽመውታል በተባለው ሙስና ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል

      ደቡብ ኮሪያ ለቢሊየነሩ የሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ወራሽ እና ዋና አስተዳዳሪ ሊ ጄ ያንግን ምህረት አደረገች።

      የግዙፉ የዓለማችን ኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ባለቤት ሊ ጄ ያንግ ከፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል ነው ምህረቱን ያገኙት።

      በቀድሞዋ የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ፓርክ ጊዩን ሃይ የስልጣን ዘመን ፈጽመውታል በተባለው የሙስና ቅሌት ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል።

      አንዱን ዓመት በእስር ያሳለፉም ሲሆን ባለፈው ዓመት ነሐሴ ላይ ለመታረም ቃል በመግባት ከእስር ቤት ወጥተው ነበር። የተፈረደባቸው የእስር ጊዜም ከሳምንት በፊት ተጠናቋል። ሆኖም የክስ መዝገባቸው ሙሉ በሙሉ አልተዘጋም። በክሱ ያጡትን ሙሉ መብት እና ነጻነት መልሶ ለማግኘት ምህረትን ማግኘት የግድ ይላቸው ነበር።

      ይህን ተከትሎም ከፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል ምህረት ተሰጥቷቸዋል። ፕሬዝዳንታዊ ምህረቱ

      ከሶስት ቀናት በኋላ የሚከበረውን የሃገሪቱን የነጻነት በዓል አስመልክቶ የተሰጠ ነው።ሌሎች 1 ሺ 691 ገደማ እስረኞችም የፕሬዝዳንት ዮል ምህረት አግኝተዋል።

      ሊ ጄ ኩባንያቸው የቻይናን ጨምሮ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ ኩባንያዎች ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ነው ምህረቱን ያገኙት።

      በጥሩ ተወዳዳሪነቱ ለመቀጠል የሚያስችል አመራርን ሊሰጡ ይችላሉ በሚል ምህረቱን ስለማግኘታቸውም ተነግሯል።

      ሃገሪቱ የገጠማትን ምጣኔ ሐብታዊ ጫና ለማቅለልና በተሻለ ሁኔታ ለመገንባት የሚያስችሉ ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱም ስለመታዘዛቸውም የሃገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

      ደቡብ ኮሪያ ለሃገሪቱ ምጣኔ ሃብታዊ ግንባታ የጎላጰአበርክቶ ላላቸው የቢዝነስ ሰዎች በእንዲህ ዐይነት መንገድ ምህረት የማድረግ ልምድ እንዳላትም ተነግሯል።

      News today, social life

      ቤይሩት ውስጥ በመሳሪያ አስገድዶ ገንዘቡን ከባንክ የወሰደው ጀግና ተባለ

      መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው ግለሰብ ጀግና ተብሏል።
      የምስሉ መግለጫ,መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው ግለሰብ ጀግና ተብሏል

      ከ 3 ሰአት በፊት

      መሳሪያ ታጥቆ ከቁጠባ ሂሳቡ ገንዘቡ እንዲሰጠው ያስገደደው የሊባኖስ ዜጋ በሕዝቡ ጀግና ተብሎ ተወደሰ።

      ሊባኖስ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ባንኮች ደንበኞቻቸው ወጪ በሚያደርጉት ገንዘብ ላይ ገደብ ጥላለች።

      ይህ ግለሰብ ግን መሳሪያ ታጥቆና ባንክ ውስጥ ነዳጅ አርከፍክፎ ለሆስፒታል ክፍያ ለመፈጸም የሚያስፈልገው ገንዘቡ እንዲሰጠው በኃይል መጠየቁን ኤኤፍፒ ዘግቧል።

      በግለሰቡ እና በባንኩ መካከል ለስድስት ሰዓታት ከቆየ ፍጥጫ በኋላ ግለሰቡ የጠየቀውን ገንዘብ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስ ማግኘት ችሏል።

      ይህ በስም ያልተጠቀው ግለሰብ ተግባርም በሕዝቡ ዘንድ አድናቆትን አስገኝቶለታል። ከባንኩ ውጪ ተሰብስበው የነበሩ ሰዎች “ጀግና ነህ” እያሉ ጠርተውታል።

      የግለሰቡ ወንድም ለጋዜጠኞች ሲናገር፤ “ወንድሜ በባንክ ሂሳቡ 210ሺህ ዶላር አለው። የሆስፒታል ወጪውን ለመሸፈን 5ሺህ 500 ዶላር ፈልጎ ነበር” ብሏል።

      ከባንኩ ውጪ የነበሩት የግለሰቡ ወንድም እና ባለቤት፤ “ሁሉም ሰው ሊያደርገው የሚገባው ይሄን ነው። የራሳቸው የሆነውን ማግኘት አለባቸው” ብለዋል።

      ኤልቢሲ የተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ የግለሰቡ ቤተሰብ አባላት በሆስፒታል እንደሚገኙ እና ገንዘብ እጅጉን ያስፈልጋቸው እንደነበር ዘግቧል።

      የቴሌቪዥን ጣቢያው ጨምሮ እንደዘገበው ወደ ባንኩ በኃይል ከገባው ግለሰብ ጋር ድርድር ከተደረገ በኋላ ከቁጠባ ሂሳቡ 35ሺህ ዶላር ተሰጥቶታል።

      ፖሊስ ግለሰቡን እና በእገታ ስር የቆዩ የባንክ ሠራተኞችን ከአካባቢው ይዞ የወጣ ሲሆን በግለሰቡ ላይ ክስ ይመሰረት እንደሆነ እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

      እአአ 2019 ላይ ሊባኖስ የገጠማትን ምጣኔ ሃብታዊ ቀውስ ለመቋቋም ያስችለኛል ብላ ተግባራዊ ካደረገቻቸው ውሳኔዎች መካከል ሰዎች ከቁጠባ ሂሳባቸው ወጪ በሚያደርጉት የገንዘብ መጠን ላይ ገደብ መጣል ነው።

      ከዚህ በተጨማሪም ከአገር ውጪ በሚላክ የገንዘብ መጠን ላይም ገደብ ተጥሏል። ይሁን እንጂ እነዚህ ክልከላዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።

      በሊባኖስ የተከሰተው ምጣሄ ሃብታዊ ቀውስ የአገሪቱ ገንዘብ ዋጋውን ከ90 በመቶ በላይ እንዲያጣ አድርጎታል።

      የዋጋ ግሽበት ጣሪያ ነክቷል፤ እንደ መድሃኒት እና ስንዴ ባሉ ምርቶች ላይ እጥረት አጋጥሟል። የተባበሩት መንግሥታት ከአምስት ሊባኖሳዊያን አራቱ በድኅነት ውስጥ ይኖራሉ ይላል።

      News today, Politics

      የኬንያ የምርጫ አፈጻጸም በሁሉም መመዘኛዎች ጥሩ የሚባል ነው – የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን


      ዶ/ር ሙላቱ ፤ አልፎ አልፎ የታዩት መስተጓጎል ለማስቀረት የምርጫ ቁሳቁስ አቅርቦትን በትክክል መፈጸሙን ማረጋገጥ እንደሚያሰፈልግ ተናግረዋል

      ኬንያ ያካሄደችው ምርጫ ከዝግጅቱ ጀምሮ ጠንካራ የሚባልና የምርጫ አስተዳደር አፈጻጸሙ በሁሉም መመዘኛዎች የሚበረታታ ነው ሲል የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ቡድን ገለጸ፡፡

      ባለፈው ማክሰኞ ናይሮቢ የደረሰውና በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን የኬንያ ምርጫን ቅድመ ዝግጅትና የምርጫ ሂደቱን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡
      የታዛቢ ቡድኑ መሪ ዶ/ር ሙላት ተሾመ፤ የኬንያ የምርጫ እና የድንበር ጉዳዮች በሁሉም መመዘኛዎች ጥሩ ነው የሚባል የምርጫ ዝግጅት ማድረጉንና ምርጫ ማካሄዱን ተናግረዋል፡፡

      ዶ/ር ሙላቱ፤ ኬንያ ቀደም ሲል ባካሄደቻቸው ምርጫዎች፤ ከመራጮች ማንነት ማወቅና እና የውጤት ስርጭት ጋር በተያያዘ ይነሱ ነበሩ ችግሮች የሚቀርፍ ቴክኖሎጂ በዚህ ምርጫ ላይ ተግባራዊ መደረጉ እንዲሁም የሴቶችና ወጣቶች የምርጫ አስፈታሚዎች ውክልና መሻሻሉ በምርጫው ከታዘብናቸው በጎ እርምጃዎች ውስጥ ናቸውም ብለዋል፡፡

      “የምርጫ ጣቢያዎችን አደረጃጀት እና የዳስ አቀማመጥ ፣ የድምጽ መስጫ ሚስጥራዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉና በየምርጫ ጣቢያው የሚኖሩ ረጃጅም ሰልፎች የሚያስቀሩ በቂ የዳስ ቤቶች መኖራቸው ታዛቢ ቡድኑ ከተመለከታቸውና ከተሻሻሉ ወሳኝ የምርጫ ዝግጅቶች መካከል ናቸው” ሲሉም አክለዋል፡፡

      ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፤ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የታየውን አይነት መስተጓጎል ለማስቀረት የምርጫ ቁሳቁስ አቅርቦትን በትክክል መፈጸሙን በማረጋገጥ ረገድ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡

      ከምርጫ አስተዳደር ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በማስተናገድ እና የህዝብን እምነት በማሳደግ እስከ ምርጫው ቀን ድረስ የፍትህ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደነበርም ገልጸዋል የኢጋድ ታዛቢ ቡድን መሪው ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ።

      ከተመለከትናቸው ጉዳዮች አንዱ በእጅ መመዝገቢያ አጠቃቀምን በተመለከተ የፍተህ አካላት የነበራቸው ሚና ነው ያሉት ዶ/ር ሙላቱ፤ በኬንያ ዲሞክራሲን ከማጠናከር አንጻር የኬንያ የፍትህ አካላት በህዝብ ያላቸውን ተአማኒነት እንደ ተጨባጭ ስኬት እንቆጥረዋለንም ብለዋል።

      በመጨረሻም የኬንያ ህዝብ ምርጫው ሰላማዊ፣ ግልጽ እና ስርዓት ባለው መንገድ ለመሳተፍ ላሳየው ትዕግስት እና ቁርጠኝነት አመስግነዋል።

      የኢጋድ ታዛቢ ቡድኑ ከቀጣናዊው ተቋም ስድስት አባል ሃገራት ማለትም ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከሱዳን፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ እና ከኡጋንዳ የተውጣጡ ሰባት ዋና እና 24 ጊዜያዊ አባላት የተዋቀረ መሆኑ ይታወቃል፡፡

      News today, Politics

      ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ የአፍሪካ ህብረትን የሚደግፉ የአፍሪካ ታዋቂ ሰዎች ቢካተቱ እንደማይቃወም መንግስት አስታወቀ


      መንግሥት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎት ለማስጀመር በቅድመ ሁኔታነት እንደማያስቀምጥ ገለጸ

      የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

      ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የፌደራል መንግሥት ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ የመሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማስጀመር በቅድመ ሁኔታነት እንደማያስቀምጥ ተናግረዋል።

      የፌደራል መንግስት እና ህወሓት ድርድር ተስፋ እና ስጋቶች
      “አገልግሎቶችን ለማስጀመር ዋናው መሰረታዊ ነገር ቅድመ ሁኔታ ሳይሆን ምክክር እና ዝርዝር ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል” ብለዋል።

      ከዚህ በፊት ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሌሎች የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች አገልግሎቱን ማስጀመር የሚያስችል አስተማማኝ ሰላም እና መተማመን መፈጠር እንደሚያስፈልግ አምባሳደር መለስ ገልጸዋል።

      ቃል አቀባዩ አክለውም የፌደራል መንግስት ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ላይ በቦታ እና ጊዜ እንደማይወሰን ገልጸው በድርድሩ ላይ የአፍሪካ ህብረትን አቋም የሚደግፉ ታዋቂ አፍሪካዊያን ቢሳተፉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞ እንደሌለው አክለዋል።

      መንግሥት ከህወሃት ጋር ያደርገዋል የተባለው ንግግር የሚመራው በአፍሪካ ሕብረት ብቻ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል።

      ህወሓት በበኩሉ በቃል አቀባዩ በኩል በሰጠው መግለጫ፤ የአፍሪካ ሕብረት ከኦባሳንጆ ይልቅ፤ ኡሁሩ ኬንያታን ወይም ታቦ ኢንቤኬን ወይም ሌላ ሰው ከሰየመ ችግር እንደሌለበት ገልጿል።

      ህወሓት በኬንያ ድርድር ለማድረግ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን በሊቀ መንበሩ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ማስታወቁ ይታወሳል።

      የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ በመግለጫቸው አክለውም፤ እስካሁን ባለው ጊዜ በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ 70 ሺህ የውጭ ሀገራት ዜጎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

      በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የውጭ ሀገራት ዜጎችን የመመዝገብ ስራው እስከ ነሀሴ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ መራዘሙ ተገልጿል።

      ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ስለ “ድርድር” ምን አሉ?
      ምዝገባው የተራዘመበት ምክንያት በቀነ ገደብ በተለያዩ ምክንያቶች ያልተመዘገቡ የዉጭ ሀገራት ዜገች ዕድሉን ለመስጠት እንደሆነም ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

      የውጭ ሀገራት ዜጎችን መመዝገብ ያስፈለገው ምን ያህል የውጭ ሀገራት ዜጎች በኢትዮጵያ እንዳሉ ለማወቅ እና ከተመዘገቡ በኋላ ወደ ህጋዊ መስመር ለማምጣት በማስፈለጉ ነው ተብሏል።

      እስካሁን ባለው ምዝገባ ከካናዳ፣ አሜሪካ፣ ኮንጎ፣ ናይጄሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቻይና፣ ኤርትራ፣ ቡሩንዲ ፣ ጋና፣ ባንግላዲሽ፣ ሕንድ፣ ላይቤሪያ፣ ካሜሮን እና ጣሊያን የመጡ ህገወጥ ዜጎች ተመዝግበዋል።

      News today, Politics

      ላቲቪያ ሩሲያን በሽብርተኝነት ፈረጀች

      ሌላኛዋ የሩሲያ ጎረቤት ኢስቶኒያ ድንበሯን ለሞስኮ ዝግ አድርጋለች

      የላቲቪያ ፓርላማ

      ላቲቪያ ሌሎች የአውቶፓ ሀገራት ሩሲያ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቃለች

      የቀድሞ የሶቪየት ህብረት አንድ አካል የነበረችው እና የምስራቅ አውሮፓዋ ላቲቪያ ሩሲያን በሽብርተኝነት ፈርጃለች።

      የሀገሪቱ ፓርላማ ዛሬ እንደወሰነው ከሆነ በፕሬዝዳንት ፑቲን የሚመራው የሩሲያ መንግስትን በሽብርተኝነት ፈርጇል።

      ከሁለት ሚሊዮን ያልበለጠ ህዝብ ብዛት ያላት ላቲቪያ የሩሲያ እና ቤላሩስ ዜግነት ያላቸው መንገደኞች በአውሮፓ ሀገራት እንዲዘዋወሩ የሚፈቅደው የሸንገን ቪዛን እንዳይጠቀሙም እገዳ መጣሏን ሮይተርስ ዘግቧል።

      ሩሲያ በዩክሬን ዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እያደረሰች ነው በሚል የምትከሰው ላቲቪያ ሁሉም የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ላይ ተመሳሳይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ጥሪ አቅርባለች።

      ሌላኛዋ የቀድሞ የሶቪየት ህብረት አንድ አካል የነበረችው ኢስቶኒያ ድንበሯን ለሩሲያ ዜጎች የዘጋች ሲሆን ምክንያቷ ደግሞ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወረራ እና በዜጎቿ ላይ ስቃይ እያደረሰች ነው በሚል ነው።

      ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ከስድስት ወራት በፊት ከሩሲያ ጋር ወደ ጦርነት የገቡት።

      በዚህ ጦርነት ምክንያት የዓለም የምግብ እና ነዳጅ ዋጋ ያሻቀበ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ደግሞ ወደ ጎረቤት ሀገራት መሰደዳቸውን ተመድ ከሰሞኑ ሪፖርት ማድረጉ ይታወሳል።

      News today, Politics

      ቭላድሚር ፑቲን፤ ከማሊ የሽግግር መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር መወያየታቸውን ገለጹ


      ምዕራባውያን፤ ሩሲያ በማሊ የምታደርገው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው ሲገልጹ ነበር
      የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከማሊ የሽግግር መንግስት ፕሬዝዳንት ጋር መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ።


      ቭላድሚር ፑቲንና የማሊው መሪ አሲሚ ጎይታ፤ በሁለትዮሽ ትብብር ማለትም በንግድ፣ በኢኮኖሚና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው ተገልጿል።
      የማሊው መሪ አሲሚ ጎይታ፤ ሩሲያ ላደረገችላቸው ድጋፍ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ማመስገናቸውም ተሰምቷል።


      መሪዎቹ፤ የሩስያ የምግብ፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ምርቶች ወደ ማሊ መድረስ በሚችሉባቸው ነጥቦች ላይም መነጋገራቸው ተሰምቷል።
      የሚመለከታቸው የሩሲያ እና የማሊ ተቋማት የሥራ ክፍሎች የሁለቱን ሀገራት ትብብር እንዲያጠናክሩ ስምምነት ተደርጓል ተብሏል።


      መሪዎቹ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጭምር ያለው የሩሲያ እና የማሊ የውጭ ግንኙነት ትብብር እንዳስደሰታቸውም ገልጸጸዋል ተብሏል።
      የማሊው የሽግግር መንግስት መሪ አሲሚ ጎይታ በማሊ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለማረጋጋትና በአሸባሪ ቡድኖች እርምጃ ለመውሰድ የታቀደውን ዕቅድ ጨምሮ፤ በማሊ ውስጥ የተከናወኑ ስራዎችን ለፕሬዝዳንት ፑቲን ገልጸውላቸዋል ተብሏል።


      ቭላድሚር ፑቲን ፤ እ.ኤ.አ. በ 2023 በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሊካሄድ የታቀደው የሩሲያ አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ከመላው አፍሪካ ሀገራት ጋር ያለውን ወዳጅነት ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልጸዋል።


      ምዕራባውያን ሀገራት፤ ሩሲያ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በነበረችው ማሊ ውስጥ የምታደርገው ተሳትፎ እያደገ መምጣቱም እንዳሳሰባቸው ሲገለጽ ቆይቷል።
      በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ምክንያት 40 ሚሊየን አፍሪካዊያን ለምግብ እጥረት እንደሚጋለጡ አሜሪካ ገለጸች


      የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጂን ይቭስ ሊ ድሪያን የካቲት ወር ላይ፤ በማሊ መፈንቅለ መንግሥት ያካሄደው ወታደራዊ ኃይል “ሕገ ወጥ እና ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ነው” ማለታቸው ይታወሳል።
      ይህንን ተከትሎም የማሊ ወታደራዊ መሪዎች፤ በማሊ የነበሩት የፈረንሳይ አምባሳደር ጆል ሜየር በ 72 ሰዓት ውስጥ ከማሊ እንዲወጡ ማድረጋቸው ይታወሳል።

      News today, Politics

      ቻይና በዩክሬን ለተፈጠረው ቀውስ “ዋና ቀስቃሽ” አሜሪካ ናት አለች



      ቻይና እና ሩሲያ በመካከላቸው “ገደብ የለሽ አጋርነት” እንዲኖር በመስማማት በጋራ እየሰሩ ያሉ ሀገራት ናቸው
      በታይዋን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር መካረር ውስጥ የገባችው ቻይና፤ በዩክሬን ለተፈጠረው ዩክሬን ቀውስ “ዋና ቀስቃሽ” አሜሪካ ናት አለች፡፡


      በሞስኮ የቻይና አምባሳደር ዣንግ ሃንሁዊ ረቡዕ ታትሞ ከወጣው የሩስያ መንግስት የዜና ወኪል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፤ ዋሽንግተን በኔቶ የመከላከያ ህብረት ተደጋጋሚ መስፋፋት በማድረግና እና ዩክሬንን ከአውሮፓ ህብረት ጋር ለማስማማት ለሚፈልጉ ሃይሎች ድጋፍ በመስጠት ሩሲያን ወደ ጥግ እየገፋቸው ነው በማለት ከሰዋል። 


      አምባሳደር ዣንግ “ዋሽንግተን የዩክሬን ቀውስ ዋና አነሳሽ እና ቀስቃሽ ናት፤ አሁንም በሩሲያ ላይ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ አጠቃላይ ማዕቀብ መጣልንና ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እና ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ማቅረብ ቀጥላበታለች” ሲሉ መናገራቸውም ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡
      “የእነሱ (አሜሪካውያን) የመጨረሻ ግባቸው ሩሲያን በተራዘመ ጦርነት እና በማዕቀብ ማዳከም ነው”ም ብለዋል፡፡


      የሩስያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በየካቲት ወር ወደ ቤጂንግ ተጉዘው ከቻይናው አቻቸው ዢ ጂንፒንግ ጋር ባደረጉት ምክክር በሀገራቱ መካካል “ገደብ የለሽ አጋርነት” እንዲኖር መስማማታቸው የሚታወስ ነው፡፡
      የሀገራቱን ወቅታዊ ግንኙነት በተመለከተ የተጠየቁት አምባሳደር ዣንግም የሲኖ-ሩሲያ ግንኙነት “በታሪክ ውስጥ እጅግ በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል” ብለዋል፡፡


      የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሀገራቸው የሩሲያን ሉዓላዊነት እና ደህንነትን እንደምትደግፍ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት በቅረቡ መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡
      ቤጂንግ “በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር ፈቃደኛ ነች”ም ነበር ያሉት ዢ፡፡


      የሩሲያ እና የቻይና ወዳጅነት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የትብብር ምሳሌ መሆኑን ፕሬዘዳንት ፑቲን ከወራት በፊት ከቻይናው አቻቻው ጋር በነበራቸው የበይነ መረብ ውይይት መናገራቸውም የሚታወስ ነው።
      ሀገራቱ በወታደራዊ፣ በቴክኖሎጂ፣ በጠፈር ሳይንስ፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ጨምሮ በሌሎች ሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ ይታወቃል፡፡ 

      News today, social life

      የሕዳሴ ግድበ 2ኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት ጀመረ

      ዛሬ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው
      ሲጠናቀቅ ከአፍሪካ ትልቅ ግድብ እንደሚሆን የሚጠበቀው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ 2ኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።


      ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።


      የሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ
      የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው ን ዛሬ በይፋ ጀምሯል።


      ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
      ባሳለፍነው ጥር 25 2014 ዓ.ም በዚህም ግድቡ ካሉት ተርባይኖች ውስጥ አንዱ የሆነው እና ዩኒት 10 የሚል መጠሪያ ያለው ተርባይን 375 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል።


      ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ግድብ ለመገንባት የመረሰት ድንጋይ ካስቀመጠች አንድ አመት በኋላ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግብጽና ሱደን በግድቡ ላይ ስጋት እንዳላቸው ጥያቄ አንስተዋል፡፡
      ኢትዮጵያ፣ሱዳንና ግብጽ በግድቡ አስተዳደር ጉዳይ የሶስትዮች ንግግር እና ድርድር ከመጀሩ ቆይተዋል፤ ነገርግን እስካን ከስምምነት አልደረሱም፡፡


      የኢትዮጵያ መንግስት ግድቡን እየገነባ ያለው ለልማት አላማ ብቻ መሆኑን እና በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ላይ የጎላ ተጽእኖ እንደማያደርስ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ ግብጽና ሱዳን ግን በግድቡ ዙሪያ የየራሳቸው አቋም አላቸው፡፡


      በተለይም ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን የተፈረመ ስምምነትን ጭምር በመጥቀስ፤ ታሪካዊ የሆነ የውሃ ድርሻዋ ላይ ተጽእኖ እንሚያሳድር እና ግድቡ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድርባት ትገልጻለች፡፡


      በ2013 ዓ.ም በአሜሪካ ዋሽንግተን ሲደረግ የነበረው የሶስትዮሽ ድርድር ከፈረስ በኋላ ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት አመቻችነት እንዲካሄድ ተስማምተዋል፡፡


      ድርድርሩ ወደ አፍሪካ ህብረት የመጣው ኢትዮጵያ፤ ድርድሩ ሳይጀመር የታዛቢነት ሚና የነበራቸው አሜሪካና የአለም ባንክ ሚናቸውን ወደ አደራዳሪነትና ወደ የስምምነት ሰነድ አርቃቂነት ከፍ በማድረጋቸው እና ኢትዮጵያም ይህን አልቀበልም በማለቷ ነው።


      ኢትዮጵያ የግድቡ ጉዳይ የልማት ጉዳይ ነው ብትልም ፤ግብጽና ሱዳን የግድቡን ጉዳይ የጸጥታ ጉዳይ ነው በማለት ለተመድ የጸጥታው ም/ቤት በማቅረብ ም/ቤቱ ወይይት አድርጎበት ያውቃል።

      News today, social life

      ሲም ካርድ ያለው ሁሉ ገንዘብ መበደር የሚችልበትን ዕድል ለመፍጠር ያቀደው ቴሌብር

      የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ

      ከአስራ አራት ወራት በፊት ወደ አገልግሎት የገባው ቴሌብር የተሰኘው የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለፈው ሳምንት አርብ ከቁጠባ እና ብድር ጋር የተያያዙ አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት ጀምሯል።

      ከቢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶች በፋይናንስ ሥርዓት ያልተሸፈነውን 60 በመቶ የሚሆን የኅብተረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል።

      የነዳጅ ድጎማ እና የግብር ክፍያን ጨምሮ ባለፉት 14 ወራት ገንዘብ ለመላላክ፣ የግብይትና የአገልግሎት ክፍያን ለመፈጸም እንዲሁም ከውጭ አገራት ገንዘብ ለመቀበል ሲውል የነበረው ቴሌብር አሁን ደግሞ  ‘መላ’፣ ‘እንደኪሴ’ እና ‘ሰንዱቅ’ የተሰኙ አገልግሎቶችን ይፋ አድርጓል።

      ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌብር ደንበኞች ገንዘብ እንዲቆጥቡ፣ ሲያስፈልጋቸው እንዲበደሩ የሚረዱት አዳዲሶቹን አገልግሎቶች ለማስጀመር አስራ አራት ወራት በላይ ዘግይቷል።

      ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቴሌኮም እነዚህን አገልግሎቶች ለማስጀመር ከአንድ ዓመት በላይ የዘገየበትን ምክንያት ሲያስረዱ “የተሰጠን ፍቃድ እሱን አልፈቀደልንም ነበር። ስለዚህ በቴሌ ብር ሌሎቹን አገልግሎቶች እየሰጠን ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ለማግኘት ሥራዎችን ስንሰራ ቆይተናል” ብለዋል። 

      ለመሆኑ አገልግሎቶቹ ምንድን ናቸው?

      የቴሌብር ቁጠባና ብድር

      በቴሌብር አማካኝነት በቅርቡ የተጀመሩት ሦስት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ያለዋስትና/ማስያዣ እንዲበደሩ ወይም እንዲቆጥቡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

      • ሳንዱቅ

      ይህ የቴሌብር አገልግሎት ደንበኞች ገንዘብ የሚቆጥቡበት ሲሆን፣ ለተቀማጭ ገንዘብ ወለድ የሚከፈልበትን እና ከወለድ ነጻ የሆነ አመራጮችን አካቷል።

      እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገለጻ፣ ወለድ የሚከፈልበት ቁጠባ በየቀኑ የሚሰላ እና ደንበኞች በቀን ያገኙትን መጠን የሚያመላክት ነው።

      • እንደ ኪሴ

      የቴሌብር ደንበኞች ግብይት እየፈጸሙ ገንዘብ በሚያንሳቸው ጊዜ ቀሪውን ገንዘብ የሚያገኙት ሥርዓት ደግሞ እንደኪሴ ይሰኛል። 

      እንደኪሴ ደንበኞች ለግብይት ከሚያጥራቸው ገንዘብ በተጨማሪ እንደ የኤሌክትሪክ እና ውሃ ያሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመፈጸምም ያስችላል።

      ይህ አሰራር ደንበኞች ለክፍያ የጎደላቸውን እስከ 2 ሺህ ብር የሚሸፍንም ነው።  

      • መላ

      ቴሌብር መላ፣ ደንበኞች የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት መንገድ ሲሆን ግለሰቦችን እና የንግድ ተቋማትን የሚያካትት ነው።

      በቴሌብር መላ ግለሰቦች በወር እስከ 10 ሺህ ብር፣ የንግድ ተቋማት ደግሞ እስከ 100 ሺህ መበደር እንደሚችሉ የሚያስረዱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ግለሰቦች የተበደሩትን በቀን፣ በሳምንት እና በወር መመለስ የሚችሉበትን አሰራር ማቀፉን ጠቅሰዋል።

      ለንግድ ተቋማት ደግሞ ለግለሰቦች ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ በተጨማሪ የ3፣ የ6 እና የ9 ወር የሚመልሱበትን አሰራር አካትቷል።

      ቴሌብር መላ “ለሥራ ማስኬጃ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳብ ኖሯቸው ወደ ንግድ መግባት ለሚፈልጉ ሰዎችን ታሳቢ አድርጎ የቀረበ ነው። ለዚያ ነው በፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነውን ማኅበረሰብ፣ ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይሆናል ብለን ያሰብነው” ሲሉም አክለዋል።   

      መላ፣ እንደ ኪሴ እና ሰንዱቅ በተሰኙት የቴሌብር አገልግሎቶች በመጀመሪያ ዓመት ውስጥ በየወሩ በአማካኝ ከ3 እስከ 4 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል እና ከ19.5 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለማንቀሳቀስ ማቀዱን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል።

      ከዚህም ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የብድር አገልግሎቱ ወይም ቴሌብር መላ ሲሆን 9.8 ቢሊዮን ብር ይሸፍናል።

      6.4 ቢሊዮን ብር ክፍያን ለማጠናቀቅ ወይም እንደ ኪሴ ለተባለው አገልግሎት እንዲሁም 3.3 ቢሊዮን ብር ደግሞ በቁጠባ ወይም ሳንዱቅ በተሰኘው አገልግሎት የሚጠቃለል ነው።

      ደጋግመው ብድር የሚወስዱ ደንበኞችን ጨምሮ በዓመት 108 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማገልገል ማታቀዱንም አስረድተዋል።

      አገልግሎቶቹ በተጀመሩ በቀናት ውስጥ የዕለት ብድር ወስደው የሚመልሱ እንዲሁም የሚቆጥቡ ደንበኞች መኖራቸውን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተስፋ ሰጪ እና “አስገራሚ” ሁኔታዎች መኖራቸው ገልጸዋል።

      በቴሌብር መላ የሚሰጠው ብድር በሙሉ ዋስትና ወይም ማስያዣ እንደማይጠየቅበትም ጨምረው አስረድተዋል።

      News today, social life

      የኦሮሚያ ክልል ባህልና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኦንላይን ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ ተከፈተ

      የኦሮሚያ ክልል ባህልና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኦንላይን ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ ተከፈተ
      የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ያዘጋጀው “የቱሪዝምና ቴክኖሎጂ” ሳምንት ዛሬ ተከፈተ
      በፎቶግራፍና በተንቀሳቃሽ ምስል የተደገፈው ኤግዚቢሽኑ “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ መታየት ጀምሯል

      የኦሮሚያ ክልል ባህል እና እሴትን የሚያሳይ ቋሚ የኢንተርኔት (ኦንላይን) ኤግዚቢሽን በጎግል ላይ በይፋ ተከፍቷል።

      በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን አዘጋጅነት የተሰናዳው ይህ የኢንተርኔት (ኦንላይን) ኤግዚቢሽን “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” መተግበሪያ ላይ የሚገኝ መሆኑ ተነግሯል።

      በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው ወንጪ ሐይቅ ምርጥ የቱሪዝም መንደር ሆኖ በተመድ ተመረጠ
      የኦንላይን ኤግዚቢሽኑ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረው “የቱሪዝምና ቴክኖሎጂ” ሳምንት ላይ በይፋ የተከፈተ ሲሆን፤ ኤግዚቢሽኑንም የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አስጀምረውታል።

      በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ነጋ ዱፌራ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ 21 የተለያዩ የክልሉን ባህል እና እሴት የሚያሳዩ ይዘቶች መጫናቸውን አስታውቀዋል።
      “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” ላይ የተጫኑት 21 ይዘቶች በክልሉ ባህላዊ መገልገያዎች፣ ምግቦች እና አለባበሶች ላይ ያተኮሩ መሆኑን አቶ ነጋ ዱፌራ አስታውቀዋል።

      ሁሉም ይዘቶች “በጎግል አርት ኤንድ ካልቸር” መተግበሪያ ላይ መቀመጡን እና ማንኛውም ሰው መተግበሪያውን በማውረድ፤ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ አሊያም ቪዚት ኦሮሚያ ሲል እነዚህ በምስል እና በጽሁፍ የተደገፉ ይዘቶች ማይት ይችላል ብለዋል።

      “ጥምቀት በውኃ ላይ” በደምበል (ዝዋይ) ኃይቅ ላይ የተከበረው የከተራና ጥምቀት በዓል
      እነዚህ ይዘቶች በቋሚነት እንደ ዲጂታል ሙዚየም በመተግበሪያው ላይ የሚቀመጡ መሆኑን እና በየትኛውም የዓለም ክፍል ያለ ሰው በማንኛውም ሰዓት ከፍቶ ሊመለከት የሚችለው እንደሆነ አቶ ነጋ ለአል ዐይን ገልጸዋል።

      በተያያዘ የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ያዘጋጀው የቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ ሳምንት በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ ተከፍቷል።