News today, Politics

አሜሪካዊቷ ከፍተኛ ዲፕሎማት፤ የአፍሪካ ሃገራት “ሊያልፉት የማይገባ ቀይ መስመር አለ” ማለታቸው እያነጋገረ ነው

አሜሪካዊቷ ከፍተኛ ዲፕሎማት፤ የአፍሪካ ሃገራት “ሊያልፉት የማይገባ ቀይ መስመር አለ” ማለታቸው እያነጋገረ ነው
ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ፤ የአፍሪካ ሃገራት ከስንዴ እና ማዳበሪያ ውጭ ከሩሲያ ምንም ነገር እንዳይገዙ አስጠንቅቀዋል
አምባሳደር ሊንዳ ከሰሞኑ ሶስት የአፍሪካ ሃገራትን መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው

አፍሮ አሜሪካዊቷ የአሜሪካ ከፍተኛ ዲፕሎማት፤ የአፍሪካ ሃገራት ከስንዴ እና ማዳበሪያ ውጭ ከሩሲያ ምንም ነገር እንዳይገዙ ማስጠንቀቃቸው እያነጋገረ ነው፡፡

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ የአፍሪካ ሃገራት ሊያልፉት የማይገባ ቀይ መስመር እንዳለ ተናግረዋል፡፡

ግሪንፊልድ ከሰሞኑ ኡጋንዳን፣ ጋናን እና ኬፕቨርዴን ጎብኝተዋል፡፡ ጉብኝታቸው የሩሲያውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሰርጌ ላቭሮቭን የአፍሪካ ጉብኝት ተከትሎ የተደረገ ነው፡፡ ዲፕሎማቷ ግን ከሩሲያ እና ቻይና ጋር ለመፎካከር በሚል ወደ አፍሪካ እንዳልመጡ ተናግረዋል፡፡

በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ምክንያት ለከፋ የምግብ ዋስትና ችግር ለተዳረገችው አፍሪካ መፍትሔ ለማፈላለግ በማሰብ እንደሚጎበኟትም ነበር ከጉዞው በፊት የተናገሩት፡፡

ሆኖም ኡጋንዳ ከደረሱ በኋላ የአፍሪካ ሃገራት ሊያልፉት የማይገባ ቀይ መስመር እንዳለ መናገራቸው እያነጋገረ ነው፡፡

“የአፍሪካ ሃገራት እህልን ጨምሮ የሩሲያን የግብርና ምርቶች እና የአፈር ማዳበሪያን ሊገዙ ይችላሉ” ሲሉ ለአሶሼትድ ፕሬስ የተናገሩት አምባሳደር ሊንዳ ነገር ግን ነዳጅንና የነዳጅ ምርቶችን ሊገበያዩ እንደማይችሉ ገልጸዋል፡፡

የሚገበያዩ ከሆነ በሩሲያ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን መጣስ እንደሚሆን ነው አምባሳደሯ የተናገሩት፡፡ በመሆኑም “ማዕቀቡን እንዳይጥሱ እናሳስባለን” ብለዋል ይህ ካልሆነ ተመሳሳይ እጣ ፋንታ ሊጠብቃቸው እንደሚችል በማስጠንቀቅ፡፡

ብዙዎቹ የአፍሪካ ሃገራት በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ገለልተኛ አቋምን መርጠዋል፡፡ ሩሲያን አውግዘው ከምዕራባውያን ጎን እንዲሰለፉ ቢፈለግም ከኬንያ በስተቀር አቋማቸውን በአደባባይ ለማንጸባረቅ የደፈሩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ሆኖም ይህ የጦርነቱን ዳፋ ከመቅመስ አላዳናቸውም፡፡ በተለይም ብዙዎቹ በሩሲያ እና ዩክሬን የስንዴና ሌሎች የግብርና ምርቶች እንዲሁም የአፈር ማዳበሪያ ላይ ጥገኛ መሆናቸው ለከፋ ጉዳት ዳርጓቸዋል፡፡ ለከፋ የምግብ ዋስትና ችግር እና ኑሮ ውድነት የተዳረጉም ጥቂት አይደሉም፡፡

በዚህ መካከል ነው የአፍሮ አሜሪካዊቷ የአምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ማስጠንቀቂያ የመጣው፡፡ ምን ያህል ውጤት ሊያመጣ እንደሚችል አልታወቀም፡፡ ነዳጅን ጨምሮ በከፋ የሸቀጦች ዋጋ ንረት እየተጠበሱ መሆኑን ተከትሎ የመጣውን እንቀበላለን በሚል የሩሲያን ነዳጅ ሊገዙ የሚችሉ አንዳንድ የአፍሪካ ሃገራት እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡

ከአምባሳደር ሊንዳ ጉብኝት በፊት “ምን ማድረግ እንዳለብን ማንም ሊነግረን አይችልም” በሚል የተናገሩት የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ ከጉብኝቱ በኋላ “አፍሪካን ከአንጀት መርዳት ከፈለጉ ባልተሳተፍንበት ጦርነት ከጣሉት ማዕቀብ ሊለዩን ይገባል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

News today, Politics

የቡድን ሰባት አባል ሀገራት፤ ሩሲያ ዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን ለዩክሬን ልትሰጥ ይገባል አሉ

የቡድን ሰባት አባል ሀገራት፤ ሩሲያ ዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን ለዩክሬን ልትሰጥ ይገባል አሉ
ሩሲያ፤ በዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያ ዙሪያ የጸጥታው ም/ቤት እንዲሰበሰብ ጠየቀች
ሞስኮ፤ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጣትም ጠይቃለች

ሩሲያ፤ የዛፖሪዥያ ኒውክለር ጣቢያን፤ ለዩክሬን አሳልፋ ልትሰጥ እንደሚገባ የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ጠየቁ።

የሀገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ በዛፖሪዥያ ያለውን የኒውክለር ጣቢያ መያዝና መቆጣጠር ያለባት ዩክሬን ናት ብለዋል።

ሩሲያ፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ “ዛፖሪዥያ ኒውክሌር ጣቢያ” ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰች
ሚኒስትሮቹ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ፤ የኒውክለር መሳሪያዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ለሚያደርገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

ምንም እንኳን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሞስኮ በዛፖሮዝሂ ያለውን የኒውክለር ጣቢያ እንዳትቆጣጠርና ለዩክሬን አሳልፋ እንዲሰጥ ቢጠይቁም ሩሲያም ሌላ ቅሬታ አሰምታለች።

ሞስኮ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት፤ በኒውክለር ጣቢያው ዙሪያ ስብሰባ እንዲያደርግ ጠርታለች።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሩሲያ ቋሚ መልዕከተኛ ጽ/ቤት፤ የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት አባል ሀገራት በዛፖሪዥያ ኒውክለር ጣቢያ ዙሪያ ስብሰባ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

በዚህ ስብሰባ ላይም ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እና የተባበሩት መምግስታት የኒውክለር ተቆጣጣሪ ማብራሪያ እንዲሰጧት ሞስኮ ጠይቃለች።

ዩክሬን በኒውክለር ጣቢያው ላይ የድሮን ጥቃት እያደረገች ነው ስትል ሞስኮ ብትከስም፤ ዩክሬን ግን ይህንን አስተባብላለች። ዩክሬን በበኩሏ ሩሲያ የኒውክለር ጣቢውን በመጠቀም ትቃት እየሰነዘረች ነው ስትል ትከሳለች።

ሩሲያ በግዝፈቱ ሁለተኛ የሆነውን የዩክሬን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች
የዩክሬን ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት፤ሩሲያ የኒውክለር ጣቢያውን ለወታደራዊ ምሽግ እየተጠቀመች ነው ሲል ወቅሷል። የሩሲያ ከባድ መሳሪያዎች እና ወታደራዊ ሰዎች በዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያ መኖራቸውንም ዩክሬን ገልጻለች።

የቡድን አባት አባል ሀገራት የዛፖሪዥያ የኒውክለር ጣቢያን በሚመለከት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳሉ ገልጸዋል።

News today, Politics

ቻይና፤ አሜሪካ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገለጸች

ቤጅንግ፤ ከዋሸንግተን ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ማቋረጧን መግለጿ ይታወሳል

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት በአሜሪካ እና ቻይና መካከል ከፍተኛ ውጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል

ቻይና፤ አሜሪካ ከዚህ በኋላ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቷን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ፡፡

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ ዋሸንግተን በቻይና ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያነጣጠረ ጸብ አጫሪ ድርጊት ከፈጸመች እንደማይታገስ ገልጿል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢን ዛሬ በመግለጫቸው አሜሪካ፤ ቻይናን ለመያዝ ታይዋንን ከመጠቀም እንድትቆጠብ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ 

የቻይና ባለስልጣናት አሜሪካ ፤ ታይዋንን በመጠቀም፣ የቤጅንግ ብሔራዊ ጥቅም እየጎዳች መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለጹ ናቸው፡፡ ቃል አቀባይ ዋንግ ዌንቢንም ይህንኑ ሃሳብ በዛሬ ድጋሚ አንስተውታል፡፡ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፤ የናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ጸብ አጫሪ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ በኋላ ግን ለጸብ የሚያነሳሳ ድርጊት ከዋሸንግተን ከመጣ ቻይና አጸፋውን ለመመለስ መዘጋጀቷን ተናግረዋል፡፡ 

ቻይና ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ወታደራዊ ትብብር ማቋረጧን ተከትሎ ዋሸንግተን ድርጊቱን አውግዛ ነበር፡፡ ቤጅንግ ግን ሁሉንም እርምጃዎች የወሰደችው አሜሪካ ጸብ አጫሪ ድርጊትን ከፈጸመች በኋላ በመሆኑ የወሰደቻቸው እርምጃዎች ሚዛዊና ትክክል መሆናቸውን ገልጻለች፡፡

ቻይና እና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብርን ጨምሮ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያም ንግግርና ውይይት የነበራት ቢሆንም በፔሎሲ ጉብኝት ምክንያት ሁሉንም ላለማድረግ ውሳኔ ማሳለፏን ማሳወቋ ይታወሳል፡፡ 

ከዚህ ባለፈም የፕሬዝዳንት ዢ ሺን ፒንግ አስተዳደር፤ ሀገሪቱ ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን የማጓጓዝ፣ አደገኛ ዕጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን ማቋረጡን ገልጿል፡፡

ቻይናና አሜሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ የበላይነትን ለማስፈን ከሚደረግ ሽኩቻ ባለፈ በንግድና ኢኮኖሚ ላይ ያተኮረ እሰጥ አገባ የነበራቸው ቢሆንም ታይዋን ግን የሀገራቱን ግብ ግብ የበለጠ እንዲካረር አድርጋዋለች ተብሏል፡፡ 

News today, Politics

ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” አሉ

ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” አሉ
“በዙሪያየ ያሉ ሰዎች ሁሉ ኢላማ ሲደረጉ ዝም ከማለት “ምንም አማራጭ አል

የኒውዮርክ አቃቤ ህግ ዶናልድ ትራምፕ የሚያስተዳድሩትን ተቋም የግብር እና ብድር እፎይታ ለማግኘት በሚል ” የሚያሳስት እና ያልተገባ የንብረት ግምገማ” በማድረግ አጭበርብረዋል ሲል መክሰሱ የሚታወቅ ነው፡፡

በዚህም መሰረት ኒውዮርክ ወደ ሚገኘው ፍርድ ቤት የቀረቡት ዶናልድ ትራምፕ በተጠረጠሩበት የማጭበርበር ድርጊት መሰረት ምርመራ ላይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች “መልስ አልሰጥም” ማለታቸው ተሰምቷል፡፡

ትራምፕ ጉዳዩን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ “በአሜሪካ ህገ መንግስት ለእያንዳንዱ ዜጋ በተሰጡት መብቶች መሰረት፤ ጥያቄዎች ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆንኩም”ብለዋል።

ትራምፕ መልስ ላለመስጠታቸው “ቤተሰብ፣ ድርጅት እና በዙሪያየ ያሉ ሰዎች ሁሉ የፖለቲካ ፍለጎት ባላቸው ጠበቆች፣ በዐቃብያነ-ህግ የሚደገፉ የሀሰት ዜና የሚያሰራጩ ሚድያዎች ዒላማ ሲሆኑ፣ ምንም አማራጭ አልነበረኝም” የሚል ምክንያት ማቅረባቸውም ነው ፍራንስ-24 የዘገበው፡፡

በፍሎሪዳ የሚገኘውን የአሜሪካ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ) ከቀናት በፊት የዶናልድ ትራምፕ መኖሪያ ቤትመበርበሩ የሚታወስ ነው፡

ፍተሻው ዶናልድ ትራምፕ ምናልባትም በደጋፊዎቻቸው ከተፈጸመው የካፒቶል ሂል ጥቃት ጋር በተያያዘ ከቤተ መንግስት ያሸሹት ሚስጥራዊ ሰነድ ይኖር ይሆን በሚል የተካሄደ ነው መሆኑን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል፡፡

ትራምፕ ኒውዮርክ በሚገኘው ህንጻቸው ላይ ሳሉ ነው መኖሪያቸው የተፈተሸው።

“ማር-ኤ-ላጎ የሚገኘው ቅንጡ መኖሪያ ተከቦ ነው የሚገኘው፤ በብዙ የኤፍ.ቢ.አይ ፖሊሶች ተወርሮም ይገኛል” ሲሉም ነበር ዶናልድ ትራምፕ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘ ማህበራዊ ሚዲያቸው በወቅቱ ያስታወቁት።

ድርጊቱ በቀጣዩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ (2024) እንዳይወዳደሩ ለማድረግ በማሰብ የተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

K^አወዛጋቢው ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2024 በሚካሄደው ምርጫ ለመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ፍንጭ መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡

News today, Politics

የቻይና ጦር በታይዋን ዙሪያ ሲያካሂድ የነበረውን ወታደራዊ ተልዕኮ ማጠናቀቁን አስታወቀ


“ለውጊያ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ለመሆን” ያለመው ልምምድ እንደሚቀጥል የቻይና ጦር አስታውቋል

ቻይና በታይዋን ዙሪያ ስታካሂዳቸው የነበሩትን የተለያዩ ወታደራዊ ተልዕኮዎችን ማጠናቀቋን አስታወቀች።

የቻይና ጦር፤ “አሁን ያለው ሁኔታ በታይዋን የባህር ዙሪያ ያለውን ለውጥ በቅርበት መከታተል ይፈልጋል” ሲል አሳስቧል።

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን አቋረጠች
የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው
ጦሩ “ለውጊያ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ለመሆን” ወታደራዊ ልምምድ ማድረጉን እንደሚቀጥል መጠቆሙም ቻይና ደይሊ ግሎባል ታይምስ ዘግቧል።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በታይዋን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ፤ በሩቅ ምስራቅ የነገሰው ውጥረት እንደቀጠለ ነው።

አፈ ጉባኤዋ ባሳለፍነው ሳምንት ታይዋንን የጎበኙ ሲሆን ድርጊቱ ቻይናን እንዳስቆጣ የዓለም ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል።

ይሄንን ተከትሎም ቻይና በታይዋን ባህር ዙሪያ ለቀናት የሚዘለቅ ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆኗን አሳውቃ ነበር።

ቻይና ባሳለፍነው ሳምንት ልምምድ ላይ ዶንግ ፋንግ የተሰኘው የቻይና የረጅም እና አጭር ርቀት ባልስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ታይዋን ባህር ተኩሳ እንደነበርም ሚታወስ ነው።

በታይዋን ስድስት አቅጣጫዎች ምንም አይነት የባህር እና አየር ላይ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ቻይና አስቀድማ ማስጠንቀቋ ይታወሳል።

በቻይና ድርጊት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የገባቸው ታይዋን በበኩሏ ቻይና “ለወረራ እየተዘጋጀች” መሆኑን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በመናገር ላይ ናት፡፡

የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆሴፍ ዉ ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መሆኗን መግለጻቸው ኤኤፍፒ ማክሰኞ እለት ዘግቧል፡፡

ጆሴፍ ው የቻይናን የሶሞኑ ወታደራዊ እንቅስቀሴ በማስመልከት በታይፔ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ቤጂንግ በእስያ-ፓሲፊክ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመቀየር እየሰራች ነው ብለዋል።

ቻይና፤ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተች
የቤጂንግ የጦርነት ጨዋታ “የታይዋንን መብት የሚጻረር” እና በታይዋን ዙሪያ ያለውን ውሃ እና ሰፊውን የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነው” ብለዋል ጆሴፍ ው።

ቤጂንግ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ” ስታስጠነቅቅ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡

እናም በምስራቅ ታይዋን የባህር አከባቢ የተፈጠረው ውጥረት ወዳልተፈለገ የጦር መማዘዝ እንዳያመራ ተሰግቷል።

News today, Politics

ኢዜማ የመንግስት ተሿሚ አባላቱ በያዙት ኃላፊነት እንዲቀጥሉ መወሰኑን አስታወቀ

ዶ/ር ኦንጋይ ኦዳን የደቡብ ክልል የኢዜማ የመሪ ክንፍ ተጠሪ ሆነው እንዲሰሩም ወስኗል
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመንግስት የተሾሙ አመራርና አባላቱ በተረከቡት ስልጣን ይቀጥሉ ሲል ወሰነ።
 ፓርቲው በፌስቡከ ገጹ ባወጣው መግለጫ ወሳኔው በአርባ ምንጭ ከተማ ለሁለት ቀናት ተሰብስበው በነበሩት የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እና የፓርቲው ሊቀመንበር ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የተሰጠ ነው።


ከስብሰባቸው ጎን ለጎን ከፌደራል እስከ ወረዳ ባሉ የመንግስት መዋቅሮች ተካተው ሕዝብን በማገልገል ላይ ከሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ጋር በሥራ አፈጻጸም እና በአደረጃጀት ጉዳዮች ላይ የተወያዩት ከፍተኛ አመራሮቹ ጉዳዩን የተመለከተ ውሳኔ አሳልፈዋል።
በውሳኔው መሰረትም መንግስት አብሮ ለመሥራት ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ በመዋቅሩ ተካተው ሥልጣን ተረክበው ሕዝብን በማገልገል ላይ የሚገኙ የኢዜማ አባላት አርአያ መሆን የሚችሉ ስለሆኑ በኃላፊነታቸው እንዲጥሉ መደረጉን መግለጫው ጠቅሷል፡፡


በመልካም ሥነምግባር የታነጹ፣ ሌብነትን የሚጸየፉ፣ በሥራ ትጋታቸው እና በአፈጻጸም ብቃታቸው የተመሠከረላቸው እና አርአያ መሆናቸውን እንዲቀጥሉም ማሳሰብያ ተሰጥቷል እንደ ፓርቲው ገለጻ።
የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በስብሰባቸው በደቡብ ክልል በመንግስት መዋቅር ውስጥ ስለተካተቱ አባላት አደረጃጀት እና ተጠሪነት የመከሩም ሲሆን ኦንጋይ ኦዳ (ዶ/ር) በደቡብ ክልል የኢዜማ የመሪ ክንፍ ተጠሪ ሆነው እንዲሰሩ መወሰናቸው ተገልጿል፡፡
ኢዜማ በመጀመርያ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ከመንግስት የቀረበውን የአብረን እንስራ ጥሪ ተቀብሎ መንግስት ለከፍተኛ አመራሮቹ ጭምር የሰጠውን ሹመት መቀበሉ ይታወሳል።


በዚህም የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በፌዴራል መንግስት ካቢኔ ውስጥ ተካተው በትምህርት ሚኒስትርነት ሲሾሙ፤ የፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ካቢኔ ተካተው የአስተዳደሩ የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሆነው ተሾመው በማገልገል ላይ ናቸው።
በደቡብ ክልል የመንግስት መዋቅር ውስጥ የተካተቱ የድርጅቱ አባላትም አሉ።


ሆኖም ይህ ኢዜማ የበለጠ እንዲዳከምና “የመንግስት ተለጣፊ” ሆኖ እንዲታይ አድርጎታል የሚሉ ወቀሳዎች ከራሱ ከፓርቲው ሰዎች ጭምር እንዲሰነዘሩ ምክንያት ሆኗል።
ጉዳዩ፤ የፓርቲው አቋምና አካሄድ ጭምር በፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ሳይቀር የልዩነት ምንጭ ሆኖ ፓርቲውን አመራር ለመቀየር እስከሚያስችል ምርጫ እስከማካሄድ አድርሶት እንደነበር ይታወሳል።


ይህን ተከትሎ የፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንን መሪ እና ምክትል መሪ አድርጎ መምረጡ የሚታወስ ነው፡፡

News today, social life

የዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ


በዓለማችን ለኑሮ ምቹ የሆኑ 10 ከተሞች ይፋ ሆኑ። ከተሞቹ ምርጥ የተባሉት ለኑሮ ባላቸው ምቹነት መሠረት ነው።

አውሮፓዊቷ አገር የኦስትሪያ ዋና ከተማ ቪዬና ቀዳሚዋ የዓለማችን ምቹ ከተማ ተብላለች።

በተከታይነት ደግሞ የዴንማርክ ኮፐን ሃገን እና የስዊትዘርላንድ ዙሪክ ከተሞች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

የካናዳ ከተማ የሆኑት ካልጋሪ እና ቫንኩቨር ደግሞ በአራተኝነት በቀጣይ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ሲሆን፤ የስዊትዘላንዷ ጄኔቫ፣ የጀርመኗ ፍራንክፈርት፣ የካናዳዋ ቶሮንቶ፣ የኔዘርላንድስ አምስተርዳም፣ የጃፓን ኦሳካ እና የአውስትራሊያዋ ሜልበርን ቀዳሚዎቹን አስር ደረጃዎች ለመያዝ በቅተዋል።

ይህንን ደረጃ ይፋ ያደረገው ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት እንደሚለው ከሆነ ከተሞች ለኑሮ ያላቸው ምቹነት ቢጨምርም ዓለም አቀፉ አማካይ ግን አሁንም ዝቅተኛ ነው ብሏል።

ለኑሮ ምቹነት ከታዩት ጉዳዮች አንዱ የኮሮናቫይረስ ስርጭት ተጽዕኖ መሆኑን ተጠቁሟል።

የዩክሬን ጦርነት ደግሞ ኪዬቭ ከጥናቱ ውጪ እንድትሆን ሲያስገድዳት፣ በሩሲያዎቹ ሞስኮ እና ሴንት ፒተርስበርግ ውጤት ላይም ተጽዕኖ አሳድሯል።

በዚሁ ጦርነት ምክንያት የምሥራቅ አውሮፓ ከተሞች ደረጃም ዝቅ ብሏል።

የምዕራብ አውሮፓ እና የካናዳ ከተሞች ደረጃውን በመምራት ቀዳሚ ሆነዋል።

ደማስቆ፣ ትሪፖሊ እና ሌጎስ ደግሞ ከማኅበራዊ አለመረጋጋት፣ ሽብር እና ግጭት ጋር ተተያይዞ በደረጃው መጨረሻ ላይ ለመገኘት ተገደዋል።

በዘንድሮው ጥናት 33 አዳዲስ ከተሞች ተካተዋል።

በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ከተሞች ብዙ መሻሻል አላሳዩም ተብሏል።

የሶሪያዋ ደማስቆ በደረጃው የመጨረሻው ስፍራን ይዛለች።

ቴህራን፣ ዱዋላ፣ ሃራሬ፣ ዳካ፣ ፖርት ሞርስባይ፣ ካራቺ፣ አልጀርስ፣ ትሪፖሊ፣ ሌጎስ እና ደማስቆ ናቸው የመጨረሻዎቹን አስር ደረጃዎች የያዙት።

ለኑሮ ባላቸው ምቹነት መሻሻል ያሳዩ ከተሞችም ታይተተዋል።

እነዚህ ከተሞች በአብዛኛው በምዕራብ አውሮፓ የሚገኙ የጀርመን፣ የዩናይትድ ኪንግደም እና የፈረንሳይ ከተሞች ናቸው።

ፍራንክፈርት ካለፈው ዓመት 32 ደረጃዎችን በማሻሻል ሰባተኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ በቅታለች።

ሃምቡርግ ደግሞ ከ31ኛ ወደ 16ኛ ተመንድጋለች።

የኒውዚላንድ እና የአውስታራሊያ ከተሞች ደግሞ ደረጃው ላይ ማሽቆልቆል አስመዝግበዋል።

በዚህም ዌሊንግተን እና ኦክላንድ 46 እና 33 ደረጃዎችን ለመውረድ ተገደዋል።

ድርጅቱ ይህን ደረጃ ለማውጣት የከተሞቹን መረጋጋት፣ የጤና ዘርፍ፣ ባህል እና አካባቢ፣ ትምህርት እና መሠረተ ልማት ከግምት ያስገባል።

ይህንን ደረጃ ይፋ ያደረገው ተቋም የዩክሬን ጦርነት እና ኮቪድ በሚቀጥለው ዓመት በሚኖረው የከተሞች ለኑሮ ምቹነት ደረጃ ላይ ተጽዕኖ ይኖራቸዋል ብለዋል።

ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት ላለፉት 70 ዓመታት ኢኮኖሚያዊ ትንታኔዎች በመስጠት የሚታወቀው ሲሆን የዘ ኢኮኖሚስት ጋዜጣ እህት ኩባንያ ነው።

News today, Technology

የባህር ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪው አዲሱ የቻይና ድሮን


ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ድሮኑ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል
ድሮኑ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘር ይችላል

ቻይና በአይነቱ ለየት ያለ ባህር ስር እንደ ሰርጓጀ አየር ላይ ደግሞ ድሮን የሚሆን መሳሪያ እየሰራች መሆኑ ተሰምቷል።

የቻይና ተመራማሪዎች እየሰሩት ነው የተባለው አዲሱ ስተሊዝ ድሮን ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ሲሆን፤ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል።

ሚሳዔል አስወንጫፊው የቻይና CH-7 የውጊያ ድሮን
በዓለም ላይ ካሉ “በጣም አደገኛ” የጦር መርከቦች አንዱ የሆነው የቻይናው “ለሃሳ” መርከብ
የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አሁን ላይ ለናሙና የሚሆን አዲሱን ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪ ድሮን በመስራት ሙከራ እያደረጉበት መሆኑም ታውቋል።

ሳውዝ ቻይና ሞኒተሪንግ ፖስት ጋዜጣ ባወጣው መረጃ፤ ድሮኑ አራት ተሸከርካሪ ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሁለቱ ከፊት ሁለቱ ደግሞ ከኋላ የተገጠሙ ናቸው።

ደሮኑ በባህር ስር በሚሆንበት ጊዜ ሁለቱ ክንፎቹን በማጠፍ የሚቀዝፍ ሲሆን፤ ይህም በጣም ዘመናዊ የሆነ የሰርጓጅ መርከብ ቅርጽ እንዲላበስ የሚያደርገው ነው።
ከባህር በመውጣት አየር ላይ በሚንሳፈፍበት ወቅት ደግሞ ክንፎቹን የሚዘረጋ ሲሆን፤ በሰዓት እስከ 120 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር የሚችል መሆኑንም የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታውቀዋል።

ድሮኑ በባህር ስር እንዲሁም በአየር ላይ ፈጣን እና የረጅም ርቀት ተልእኮዎችን በቀላሉ መከወን የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር አንግ ሂሶንግ ገልፀዋል።

“J-20” ዘመናዊዎቹ የቻይና ተዋጊ ጄቶች
አዲሱ ድሮን ከራዳር እይታ ውጪ እንዲሆን ታስቦ መሰራቱን የሚያነሱት የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ትክክለኛ ጥቅሙ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር መቻሉ እንደሆነም ተናግረዋል።

ድሮኑ መቼ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የቻይና ጦር ይታጠቀዋል በሚል ላይ እንዲሁም ድሮኑ ምን አይነት መሳሪያዎችን መታጠቅ ይችላል በሚለው ላይ የወጣ መረጃ የለም።

News today, Politics

አሜሪካ የአልሻባብ ተዋጊዎችን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት መፈጸሟ ተነገረ

የአልሻባብ ታጣቂዎች

ከ 5 ሰአት በፊት

የአሜሪካ ጦር በሶማሊያ ማዕከላዊ ሒራን ክልል በአልሻባብ ተዋጊዎች ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሙን የሶማሊያ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘገበ።

መገናኛ ብዙኃኑ እንዳለው ጥቃቱ የተፈፀመው የሶማሊያ መንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ተከትሎ ነው።

የአየር ድብደባ ስለመፈፀሙ ግን የአሜሪካ እና አፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ አስተያየት አልሰጠም።  

የአሜሪካ ባለሥልጣናት በሰኔ እና በሐምሌ ወር በተፈፀሙ ሁለት የአየር ድብደባዎች ሰባት የጂሃዲስት ቡድኑ ተዋጊዎች መገደላቸውን መናገራቸው ይታወሳል።

ከቅርብ ወራት ወዲህ አልሻባብ በመንግሥት ኢላማዎች ላይ የሚፈጽመው ጥቃት የጨመረ ሲሆን በቅርቡም ድንበር በመሻገር በኢትዮጵያ ደንገተኛ ጥቃት ፈጽሟል።

አሜሪካ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት በአል ሻባብ ቡድን ላይ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን በሰው አልባ አውሮፕላኖች ስትፈጽም ቆይታለች።

በተለይም የቡድኑን አመራሮች ኢላማ በማድረግ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች ከፍተኛ መሪዎቹን ጨምሮ በርካታ የቡድኑ አባላትን መግደሏ መዘገቡ ይታወሳል።

ሐምሌ 13/2014 ዓ.ም እስላማዊ ታጣቂዎቹ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንባቸው የድንበር ከተሞች የከፈቱትን ጥቃት ተከትሎ ከባድ ውጊያ ተካሂዶ ነበር።

ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለው አልሻባብ ጥቃቱን የፈፀመው ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ግዛት በኩል በሚገኙት ዬድ እና አቶ ላይ ነው።

ከኢትዮጵያ ጋር በሚዋሰኑት የሶማሊያ ድንበር አካባቢዎች ነበሩ በተባሉ የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት ጋር በተካሄደው በዚህ ከባድ ውጊያም በሁለቱም ወገን ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናት ተናግረዋል።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ ዑመርም እስላማዊ ታጣቂ ቡድኑ የከፈተውን ጥቃት የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች መክተው መመለሳቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ድንበር ተሻግረው ጥቃት ከሰነዘሩት የአልሻባብ አባላት መካከል ከ800 በላይ የሚሆኑ መገደላቸውንና በርካቶች መማረካቸውን ገልጿል።

ቀደም ሲልም የኢትዮጵያ ሠራዊት በቡድኑ ላይ ወሰዳቸው ወታደራዊ እርምጃዎች በአሜሪካ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ ግለሰብን ጨምሮ ሦስት ከፍተኛ የአልሻባብ ከፍተኛ አመራሮችን መግደሉን አሳውቋል።

በተያያዘ ዜና የአልሻባብ ታጣቂ ቡድን የቀድሞ መሪ የሆነው ሙክታር ሮቦው አዲስ በተቋቋመው ካቢኔ ውስጥ የሶማሊያ የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር በመሆን ባለፈው ሳምንት ተሹመዋል።

የእርሳቸው ሹመትም የአል ሸባብን ጽንፈኛ ርዕዮተ ዓለም ለመመከት የተደረገ ሙከራ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል።

News today, Politics

የዩክሬን ጦርነት “ክሬምያን ነጻ በማውጣት” መጠናቀቅ አለበት -ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ


ዘሌንስኪ ‘‘በክሬምያ የተጀመረው ጦርነት፤ ክሬምያን ነጻ በማውጣት መጠናቀቅ አለበት” ብለዋል
የዩክሬን አካል የነበረቸው ክሬምያ እንደፈረንጆቹ 2014 በተካሄደው ህዝበ ውሳኔን ወደ ሩሲያ መቀላቀሏ የሚታውስ ነው

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘሌንስኪ፡የዩክሬን ጦርነት ክሬምያን ነጻ በማውጣት መጠናቀቅ አለበት አሉ፡፡

ዘለንስኪ በሰጡት መግለጫ ‘‘ክሬምያ ዩክሬናዊት ናት፤ አንተዋትም’’ ሲሉም ተደምጠዋል፡፡

የዩክሬን አካል የነበረቸው ክሬምያ፤ እንደፈረንጆቹ 2014 የተካሄደውና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተቀባይነት ያላገኘው ህዝበ ውሳኔን ተከትሎ ወደ ሩሲያ መቀላቀሏ የሚታውስ ነው፡፡

በርካታ ዩክሬናውያን አሁን ላይ ከሩሲያ ጋር እየተደረገ ያለው ጦርነት የተጀመረው ያኔ ክሬምያ ወደ ሩሲያ ስትሄድ ነበር ብለውም ያምናሉ፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በትናንትናው እለት በክሬምያ ሳኪ ተብሎ በሚታወቅ የሩሲያ ወታደራዊ ማዕከል ከባድ ፍንዳታ እንዳጋጠመ እየተነገረ ነው፡፡

ሩሲያ፤ ባይረጋገጥም ጥቃቱን የፈጸመችው ዩክሬን ከሆነች መዘዙ ከባደ ነው ስትል ማስጠንቅቋ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ስለ ፍንዳታው ከመናገር የተቆጠቡት ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ ግን፤ አሁንም ክሬምያ ተመልሳ የዩክሬን ግዛት መሆኗ የማይቀር እንደሆነ በመዛት ላይ ናቸው፡፡

‘‘ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት የተጀመረው በክሬምያ ነው፤ መጠናቀቅ ያለበትም በክሬምያ ነው….ነጻ ሆና’’ም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፡፡

ክሬምያን ወደ ዩክሬን የመመለስ ፍላጎት የሚያመላክተው የፕሬዝዳንቱ ንግግር፤ ከዚህ በፊት ይሉት ከነበረ የተለየ ይዘት ያለው እንደመሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡

ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ በወርሃ የካቲት 21 ቀን፤2022 በሰጡት መግለጫ ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸው ግዛቶች ለቃ ከወጣች ዩክሬን ሰላም እንደምትቀበልና “ክሬምያ ቅድመ ሁኔታ እንደማትሆን” መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

News today, Politics

ሩሲያ ‘ካያም’ የተሰኘችውን የኢራን ሳተላይት ወደ ህዋ አመጠቀች


ሳተላይቷ የመጠቀችው ከደቡብ ከዛኪስታን ነው

አሜሪካ፤ ኢራን በሳተላይቷ በእስራኤል እና በሌላው አለም ወታደራዊ ኢላማ ለመለየት ያስችላታል የሚል ፍርሃት አላት

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ጠቅላይ መሪ የሆኑት አያቶላ አሊ ካሜኔ በጋራ ለመስራት ቃል ከገቡ ከሶስት ሳምንታት በኋላ ሩሲያ የኢራንን ሳተላይት በትናንትናው እለት ከደቡብ ካዛኪስታን ወደ ምህዋር አምጥቃለች፡፡

ሩሲያ ሳተላይቷን ያመጠቀችው ሁለቱ መሪዎች ምእራባውያንን በጋራ ለመመከት ከተስማሙ በኋላ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ኢራን የእስራኤልን የስለላ ኔትወርክ መያዟን አስታወቀች
በ11ኛው ክፍለ ዘመን በፋርስ ገጣሚ እና ፈላስፋ ኦማር ካያም ስም የተሰየመችው የሪምት ካያም ሴንሲንግ ሳተላይት በሩሲያዋ ሶዩዝ ሮኬት ነው የተመነጨፈችው፡፡ በካዛኪስታንከሚትገኘው የሩሲያ ባይኮኑር ኮስሞድሮም የተወነጨፈችው ሳተላይቷ በተሳካ ሁኔታ ወደ ኦርቢት መግባቷን የሩሲያ ስፔስ ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡

የኢራን ስፔስ ኤጀንሲ የመጀመሪያ የሆነው ቴሌሜታሪ ዳታ ከሳተላይት መቀበሉን የአራን ዜና አገልግሎት(ኢርና) ዘግቧል፡፡

ቴህራን፤ ሩሲያ ሳተላይቷን ከዩክሬን ጋር ለምታደርገው ጦርነት የሚጠቅም መረጃ ለመብሰብ ትጠቀምባታለች የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጋለች፡፡ ኢራን ሳተላይቷን ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ እንደምትቆጣጠር ገልጻለች፡፡

የአሜሪካውን የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣን ጠቅሶ እንደዘገበው የአሜሪካ ባለስልጣናት በሩሲያ እና በኢራን መካከል ያለው የስፔስ ትብብር አሳስቧታል፤ ምክንያቱም ሳተላይቷ ሩሲያ በዩክሬን የምታደርገውን ጦርነት መርዳት ብቻ ሳይሆን በእስራኤል እና በሌላው አለም ወታደራዊ ኢላማ ለመለየት ታስችላለች የሚል ፍርሃት አላት፡፡

News today, Technology

በስህተት የጣለውን ቢትኮይን በ13 ሚሊዮን ዶላር እያፈላለገ ያለው ግለሰብ


ከ10 ዓመታት በፊት ነው። ጄምስ ሃዌልስ ያስቀመጠውን ቢትኮይን ረስቶ የኮምፒውተሩን የመረጃ ቋት (ሃርድ ድራይቭ) አውጥቶ ጣለው።

ጄምስ ተዝናግቶ የወረወረው ቢትኮይን ዘንድሮ ባለው ገበያ 184 ሚሊዮን ዶላር ሊያወጣ ይችላል።

ይህ የከነከነው ጄምስ ከዓመታት በፊት የጣለውን ቢትኮይን ሚሊዮን ዶላር ከፍሎ ሊያስቆፍረው አስቧል።

የሰውዬው ‘ሃርድ ድራይቭ’ ኒውፖርት በተሰኘችው የዩናይትድ ኪንግደም ከተማ ቆሻሻ መጣያ ሥፍራ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል።

ጄምስ ይህ ውድ ቁስ ከተገኘለት ከቢትኮይኑ 10 በመቶውን ቆንጥሮ ከተማዋን የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቃል ገብቷል።

ነገር ግን የከተማዋ ምክር ቤት የቆሻሻ መጣያውን መቆፈር ሥነ-ምኅዳራዊ (ኢኮሎጂካል) ቀውስ ያስከትላል እያለ ነው።

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (አይቲ) ባለሙያው ጄምስ ከዘጠኝ ዓመት በፊት በፈረንጆቹ 2013 ነበር፤ 8 ሺህ ቢትኮይን ያቀፈውን ሃርድ ድራይቭ ጠርጎ የጣለው።

ወቅቱም ቢትኮይን የተሰኘው ዲጂታል የመገበያያ ገንዘብ ብቅ ብቅ ማለት የጀመረበት ነበር።

ቢትኮይን ገበያው ላይ የሚታወቀው በሚዋዥው ዋጋው ነው።

ለምሳሌ የጄምስ ቢትኮይን ዋጋ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት [2021] 256 ሚሊዮን ዶላር ደርሶለት ነበር።

ነገር ግን ከዘንድሮው ዓመት መባቻ ጀምሮ ዋጋው አሽቆልቁሏል።

ጄምስ በተደጋጋሚ ለኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ቆሻሻ ማከማቻው ይቆፈርልኝ ብሎ ቢያመልክትም ጥያቄው ሰሚ አጥቷል።

ይህ ያታከተው ግለሰብ አሁን ሃርድ ድራይቩ ከተገኘ 10 በመቶ ገቢውን ለከተማዋ የክሪፕቶከረንሲ ማስፋፊያ ለመስጠት ወስኗል።

ነገር ግን የጄምስን መዳፍ የምታክል ቁስ ለማግኘት ሲል ከተማ አስተዳደሩ በርካታ ወጪ አውጥቶ ለዓመታት የተከማቸውን ቆሻሻ ይቆፍር እንደሁ አልታወቀም።

ከተማ አስተዳደሩ የቆሻሻ ማከማቻውን ማመስ አካባቢውን ሊበክለው ይችላል የሚል ስጋት አለው።
ጄምስ ደግሞ “እኔ ማከማቻውን የማስቆፈር አቅም እንዲሁም አደጋ ሳያደርስ የሚያስስ ባለሙያ አለኝ” ይላል።

“እርግጥ ነው ቆሻሻ ማከማቻ መቆፈር ራሱን የቻለ ትልቅ ሥራ ነው” ይላል ጄምስ።

“ነገር ግን ማስቆፈሪያ ወጪውን እችላለሁ። የሰው-ሠራሽ ልኅቀት [አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ] ባለሙያ አስመጥተናል። ሃርድ ድራይቩን ነቅሎ የሚያወጣ ቴክኖሎጂ አለ።”

ግለሰቡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከበቢያዊ አደጋን የሚመረምር ቡድን ማዘጋጀቱን ይገልጣል።

“በሁሉም ዘርፍ የተካኑ ልምድ ያላቸው ሙያተኞች ይዣለሁ። ከተፈቀደላቸው ይህንን ሥራ በብቃት መከውን የሚችሉ ናቸው።”

ነገር ግን ሃርድ ድራቩን ማግኘት ብቸኛው ሥራ አይደለም። ይህ የመረጃ ማከማቻ ቁስ ቢገኝ እንኳ ለመሥራቱ ማስተማመኛ የለም።

ይህ በርካታ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን ያቀፈው ቁስ ቢገኝ ጄምስ ሚሊየነር ይሆናል። ነገር ግን የቢትኮይንን የገበያ ዋጋ መገመት ከባድ ነው።

ቢሆንም የ37 ዓመቱ ግለሰብ የበርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ባለቤት ሊሆን ይችላል።

ጄምስ ገንዘቡ ተቆፍሮ ይውጣለት እንጂ፣ ያደገባትን ከተማ የክሪፕቶከረንሲ ማዕከል ለማድረግ ቆርጦ ተነስቷል።

“ሕብረተሰቡን የሚጠቅም ሥራ ለመሥራት የሚያስችል ዕቅድ አስቀምጫለሁ” ይላል።

“አንደኛው ሥራ የቆሻሻ ማከማቻውን ማዘመን ነው። ከተቻለ በአካባቢው በነፋስ ኃይል የሚሠራ የኤሌክትሪክ ማመንጫ እንገነባለን።”

የኒውፖርት ማኅበረሰብ የሚጠቀምበት የክሪፕቶከረንሲ ገበያ ለመዘርጋት ነው የጄምስ ዓላማ።

ለእያንዳንዱ የኒውፖርት ነዋሪ 61 ዶላር ዋጋ ያለው ቢትኮይን ለመስጠትም ቃል ገብቷል። በተከማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ደግሞ ክሪፕቶ ላይ የተመሠረቱ ፌርማታዎች ለመግንባትም አስቧል።

የኒውፖርት ከተማ ምክር ቤት ግን በተደጋጋሚ የሰውዬውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።

የከተማዋ ቃል አቀባይ “ቆሻሻ ማከማቻን በተለመከተ የተቀመጠ ሕግ አለን። ይህን ሕግ መከተል አለብን” ብለዋል።

“አንደኛው ጉዳይ ይህ የቆሻሻ ማከማቻ ከተቆፈረ በአካባቢው ማኅበረሰብ ላይ የሚያደርሰው ሥነ ምኅዳራዊ አደጋ ነው። የጄምስ ዕቅድ ደግሞ ይህን አደጋ የሚያስከትል ነው። ይህን ልንቀበለው አንችልም። በሕጉ መሠረት እንዲያውም ከግምት ውስጥ ልናስገባው የምንችለው ሐሳብ አይደለም።”

News today, Technology

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን መገጣጠም ሊጀምር መሆኑን ግሪን ቴክ አፍሪካ ገለፀ


እስካሁን 320 በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ሀገር ቤት ገብተዋል
ግሪን ቴክ አፍሪካ በወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን መገጣጠም እጀምራለሁ ብሏል

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ በሁለት ወይም ሶስት ወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም እንደሚጀምር አስታወቀ።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚይ ኢንጅነር ቅደም ተስፋዬ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኩባንያው የአሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈም በሀገር ቤት ለማምረት ማቀዱን አስታቀዋል።

በዚህም መሰረት ድርጅቱ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች የመኪና መገጣጠም ስራን ይጀምራል ነው ያሉት።
አሁን ለይ ከ320 በላይ በኤሌትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት መቻሉን የገለጹት ኢ/ር ቅደም፤ ተሸከርካሪዎቹ 100 በ 100 በባትሪ የሚሰሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።

የተሸከርካሪዎቹ ዋጋ በነዳጅ ከሚሰሩት መኪኖች ጋር ተቀራራቢና እኩል እንደሆነ ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የጉምሩክ፣ ሱርታክስታና ተጨማሪ እሴት ታክስ ባይኖር ግን ዋጋቸው ከዚህ ይቀንስ እንደነበር ገልጸዋል።

ተሸከርካሪዎቹን ከውጭ ሀገራት እያሰገቡ ከመሸጥ ባለፈም በሀገር ውስጥ ለመገጣጠም መታቀዱን ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።ይህም በሶስት ወይም በሁለት ወራት ውስጥ በሰንዳፋ እና በድሬዳዋ ከተሞች እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

የመገጣጠሙ ሂደት በዚህ ሲቀጥል፤ በአምስት አሊያም በስድስት ዓመታት ውስጥ 60 በመቶ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት እንደሚቻል ነው የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው።

መኪኖቹን በሀገር ቤት ከመገጣጠም የሚያስችል የሰለጠነ የሰው ኃይል በቻይና እየሰለጠ እንደሆነ የገለጹት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፤ ተጠቃሚዎች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ብለዋል።
መኪኖቹን በቤት ውስጥ ቻርጅ ማድረግ እደሚቻልና ከ 4 እስከ 6 ሰዓታት ውስጥ ተሽከርካሪዎቹ 80 በመቶ ቻርጅ እንደሚያደርጉም ነው የተገለጸው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በፍጥነት ቻርጅ እንዲያደርጉ ለማድረግ 40 ቦታዎች ተዘጋጅተዋል ተብሏል፡፡

አንዱ ፈጣን ቻርጀር ማድረጊያ በአንድ ጊዜ ሁለት መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ የሚችል ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ 80 መኪኖችን ቻርጅ ማድረግ ይቻላል ተብሏል።

ግሪን ቴክ አፍሪካ፤ የአህጉሩ ሕዝብ የኢነርጂ ሃይል ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በምስራቅ፣ በምእራብ እና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት ውስጥ እየሰራ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለአል ዐይን አማርኛ አስታውቀዋል።

ኩባንያው፤ በኤሌትሪክ ሀይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ አፍሪካ ሀገራት በማስገባት ስራውን መጀመሩን የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው፤ ከዚህ ባለፈም ድርጅታቸው፤ በታዳሽ ሃይል እና በአዳዲስ የኢነርጂ ምንጮች ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

News today, Politics

ተመድ በእስራኤል-ጋዛ ጉዳይ አስቸኳይ ስበሰባ አደረገ


ድርጅቱ ተኩስ አቁሙ እምብዛም አስተማማኝ እንዳይደለ አስታውቋል
የማይከበር ከሆነ የከፋ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችልም ነው ያስጠነቀቀው

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) በእስራኤል እና በእስላማዊ ጂሃድ ታጣቂዎች መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱን ተከትሎ አስቸኳይ ስበሰባ አደረገ፡፡

ስብሰባው በድርጅቱ የጸጥታው ምክር ቤት የተደረገ ነው፡፡

የድርጅቱ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ተኩስ አቁም ቢደረግም እምብዛም አስተማማኝ አለመሆኑን በመጠቆም ሁለቱ አካላት ዳግም ወደ ግጭት የሚገቡ ከሆነ ጉዳቱ ሊከፋ ይችላል ሲሉ በስብሰባው ተናግረዋል፡፡

ሁለቱም ወገኖች አጸፋዊ ምላሽ ሊሰጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ ሁኔታዎችን የበለጠ ሊያከፋ እንደሚችልም ነው ልዩ መልዕክተኛው የተናገሩት፡፡

መፍትሔዎችን ለመፈለግ የሚደረጉ ጥረቶችን ሊያወሳስብ ይችላልም ብለዋል፡፡

እስራኤል ካሳለፍነው አርብ ጀምሮ በነበሩ ተከታታይ ሶስት ቀናት ዒላማ ባደረገቻቸው የታጣቂዎቹ ይዞታዎች ከባድ ድብደባዎችን ፈጽማለች፡፡ ታጣቂዎቹም በመልሱ 1100 ገደማ ሮኬቶችን አስወንጭፈዋል፡፡ በዚህም 15 ህጻናትን ጨምሮ 44 ሰዎች ሲገደሉ 360 ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡

ሆኖም ከተተኳሾቹ 20 በመቶ ያህሉ በተለያዩ የጋዛ ሰርጥ አካባቢዎች መውደቃቸውን ነው ልዩ መልዕክተኛው ቶር ውንስላንድ በድንገት ለተሰበሰው ምክር ቤት የተናገሩት፡፡

እስራኤል ከየትኛውም አቅጣጫ የሚወነጨፉ ሮኬቶችንና ሌሎች ተተኳሾችን ለማምከን የሚያስችል አይረን ዱምን መሰል ዘመናዊ መሳሪያዎችን መታጠቋን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡

የእስራኤልን የደህንነት ስጋት ያነሱት ልዩ መልዕክተኛው ታጣቂዎቹ ተመጣጣኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ ይልቅ ሮኬቶችን ማስወንጨፋቸውን ኮንነዋል፡፡

በተመድ የእስራኤል አምባሳደር ጊላድ ኤርዳን ታጣቂዎቹ በንጹሃን መካከል በመሸሸግ ወደ ንጹህ እስራኤላውያን መተኮሳቸውን በማውገዝ ሙሉ ኃላፊነቱን ሊወስዱ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካ ተወካይ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድም ቢሆኑ እስራኤል ዜጎቿን ከአሸባሪዎች ጥቃት የመጠበቅ መብት አላት ብለዋል፡፡

ሆኖም በድርጅቱ የፍልስጤም አምባሳደር ሪያድ መንሱር የእስራኤል ድርጊት ወረራ ነው በሚል ጥቃቱን ተቃውመዋል፡፡ ስንት ንጹሃን እስኪገደሉ ነው በሚልም ተመድ በቃ እንዲል ጠይቀዋል፡፡

ለሶስት ተከታታይ ቀናት የዘለቀው ውጊያ በግብጽ አግባቢነት ለጊዜው እንዲቆም ስምምነት ላይ መደረሱ ይተቃወሳል፡፡

News today, Politics

ታይዋን፤ ቻይና “የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር እየሰራች ነው” አለች


ታይዋን ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መሆኗን ገለጸች
ጆ ባይደን አሜሪካ ታይዋንን ከቻይና ወረራ ለመጠበቅ “ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል” መግለጻቸው ይታወሳል

በአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት የተበሳጨችው ቤጂንግ፤ የጦር አውሮፕላኖቿንና መርከቦቿ በታይዋን ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆናቸው የእየተነገረ ነው፡፡

በዚህ ስጋት የገባቸው የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆሴፍ ዉ ቻይና “ለወረራ ለመዘጋጀት” የሚያስችላት ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች መግለጻቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡
ጆሴፍ ዉ፡ የቻይናን የሶሞኑ ወታደራዊ እንቅስቀሴ በማስመልከት በታይፔ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ፤ቤጂንግ በእስያ-ፓሲፊክ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመቀየር እየሰራች ነውም ብለዋል፡፡

“የቻይና እውነተኛ አላማ በታይዋን የባህር ዳርቻ እና በጠቅላላው አካባቢ ያለውን ሁኔታ መለወጥ ነው”ሲሉም ተናግረዋል፡፡

“ቻይና ልምምዱን እና ወታደራዊ መጫወቻ ደብተሩን ለታይዋን ወረራ ለማዘጋጀት ተጠቅማበታለች” በማለትም ቤጂንግን የከሰሱት ከሰዋል ጆሴፍ ዉ፤በተጨማሪም የታይዋን የህዝብን ሞራል ለማዳከም መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ልምምዶችን እና የሚሳዔል ጥቃቶችን እንዲሁም የሳይበር ጥቃትን፣ የሀሰት መረጃ ዘመቻን እና ኢኮኖሚን የማዳከም ስራ እየሰራች ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

የዉ ጋዜጣዊ መግለጫ የመጣው የታይዋን ጦር በደሴቲቱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የራሱን ወታደራዊ ልምምድ ማድረግ ከጀመረ በኋላ መሆኑ ነው።

ጆሴፍ ዉ፡ የቤጂንግ የጦርነት ጨዋታ “የታይዋንን መብት የሚጻረር” እና በታይዋን ዙሪያ ያለውን ውሃ እና ሰፊውን የእስያ-ፓሲፊክ ቀጠናን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነው”ም ብለውታል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጆሴፍ ዉ፤ የምዕራባውያን አጋሮችን ቻይናን መቃወማቸውንም አመስግነዋል።

“የተቀረው ዓለም አቋም ዴሞክራሲ ለአምባገነንነት ዛቻ እንደማይንበረከክ ለዓለም ግልጽ መልእክት ያስተላለፈ ነው”ም ብለዋል፡፡

ቤጂንግ፤ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ” ስታስጠነቅቅ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡

እናም በምስራቅ ታይዋን አከባቢ የተፈጸረው ውጥረት ወዳልተፈለገ የጦር መማዘዝ እንዳያመራ ተሰግቷል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ፤ ታይዋንን ከቻይና ወረራ ለመጠበቅ ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል ፕሬዝዳንት ጆ-ባይደን ከወራት በፊት በጃፓን ጉብኝታቸው መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡

ጆ-ባይደን “ቻይና ታይዋንን በተመለከተ ኃይል የምትጠቀም ከሆነ እኛም መጠቀማችን አይቀርም” ነበር ያሉት፡፡

News today, Technology

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን

ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን
በሱፐርሶኒክ ፍጥነት የሚበረው አውሮፕላኑ በሰዓት ከ1 ሺህ 200 ኪ.ሜ በላይ ይጓዛል
እስከ 16 ሺህ ኪ.ግ ቦምቦችንና ክሩዝ ሚሳዔሎችን ታጥቆ ያለምንም ችግር መብረር ይችላል

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በገጠመችው ጦርነት ከተጠቀመችባቸው የጦር አውሮፕላኖች ውስጥ “Tu-160” አንዱ እንደሆነ ይነገራል።

በጣም ግዙፍ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጦር አውሮፕላን በሶቪየት ህብረት ወቅት ማለትም በፈረንጆቹ 1981 ወደ አገልግሎት የገባ ሲሆን፤ በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት እስካሁን እያገለገል ይገኛል።

በሰዓት ከ6 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚምዘገዘገው ሃይፐርሶኒክ ሚሳዔል
ሩሲያ አውሮፕላኑ ላይ በፈረንጆቹ 2008 አዳዲስ ማሻሻዎንብመ በማድረግ ይፋ ያደረገች ሲሆን፤ Tu-160R በሚል ስያሜ የአየር ኃይሏን ዳግም አስታጥቃለች።
ለመሆኑ ግዙፉ Tu-160 የጦር አውሮፕላንን ምን የተለየ ያደርገዋል?

የአወሮፕላ ቁመት 54.1 ሜትር ሲሆን፤ ክንፉ ርዝማኔም 35.6 ሜትር ይረዝማል፤ ክንፎቹ ላይ አራት ኩዜንትዞቭ NK-321 ቱርቦፋን ሞተሮች ተገጥመውለታል።

አውሮፕላኑ ከመሬት እስከ 52ሺ ገጫማ ወደላይበመነሳት መብረር ይችላል ተብሏል።

ሱፐርሶኒክ ፍጥነት እንዳለው የተነገረው Tu-160 የጦር አውሮፕላን በሰዓት 1,236 ኪሎ ሜትሮች መብረር የሚችል መሆኑም ይነገርለተል።

“አደገኛው” የሩሲያ “ዛላ ኬ.ዋይ.ቢ” ድሮን
Tu-160 የጦር አውሮፕላን 16,330 ኪ.ግ የሚመዝኑ ቦምቦችን ተሸክሞ በሱፐርሶኒክ ፍጥነት መብረር የሚችል ነው ተብሏል።

አውሮፕላኑ ከቦምቦች በተጨማሪም Kh-101 እና Kh-102 የሚባሉ ክሩዝ ሚሳኤሎችን መታጠቅ የሚችል እና ኢላማውን በአግባ የሚመታ መሆኑም ተነግሯል።

News today, Politics

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፤ “አፍሪካ ምን መምረጥ እንዳለባት አሜሪካ አታዝም” አሉ


“በአፍሪካ ለታየው ዋጋ ንረት ምክንያት ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ነው” የሚለውን ክስ ብሊንከን ውድቅ አደረጉ
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ አፍሪካ ምን መምረጥ እንዳለባት አሜሪካ “አታዝም” አሉ።

ሩሲያን ከዓለም ለመነጠል ያለመ በተባለው የአፍሪካ ጉብኝት ላይ የሚገኙት አንቶኒ ብሊንከን፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ ሀገራት ይበጃል ያሉትን አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ አቅርበዋል።

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ
ብሊንከን ባቀረቡት ጽሁፍ፡ የአፍሪካ ሀገራት ለገዛ እድገታቸው የሚታገሉ ሳይሆን የሌሎች መሳሪያ እንደሆኑ ተደረገው ሲታዩ መቆየታቸውም አንስተዋል።

“የአፍሪካ ሀገራት ከህዝቦቻቸው ፍላጎት ውጭ በሆነ መልኩ፤ የዓለም ኃያላን ፉከክር በሚያደርጉበት ጉዳይ ላይ አቋም እንዲይዙ ሲነገራቸው ነበር” ነው ያሉት ብሊንከን።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ብሊንከን፤ ሀገራቸው አሜሪካ መሰል ጫና እንደማትደገፍ የገለጹ ሲሆን፤ አሜሪካ አሁንም ቢሆን በአፍሪካ ቅድሚያ ሰጥታ የምትሰራባቸው ጉዳዮች ቢኖሩ “ዴሞክራሲ፣ ሰላም እና ጸጥታ” ናቸው ብለዋል።

አንቶኒ ብሊንከን፤ በዛሬው እለት ምርጫ በማካሄድ ላይ ያለችውን ኬንያ አንስተው ሲናገሩም፤ “አፍሪካ ችግሮች ያሉባት፤ አሜሪካ ደግሞ መፍትሄ ሰጪናት” ብለው እንደማያስቡ ፤ ነገር ግን በጋራ በመሆን ችግሮችን ለመፍታት ለሚደረጉ ጥረቶች አሜሪካ እውቅና እንደምትሰጥ አስረድተዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በሊቢያ፣ ማሊ እና ማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ስለሚገኙና የ“ዋግነር” ቡድን በመባል ስለሚታወቁ የሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች ያላቸው አስተያየትም ሰንዝረዋል።

ብሊንከን፡ በክረምሊን የሚደገፈው የ“ዋግነር” ቡድን፤ ” በአለመረጋጋት ውስጥ ሃብትን የሚዝቅና በደል የሚፈጽም ቡድን ነው” ሲሉ ከሰውታል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ ላለው የዋጋ ንረት ዋና ምክንያት ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ የጣሉት ማዕቀብ ነው ለሚለው ክስም ምልሽ ሰጥተዋል።

ብሊንከን በሰጡት ምልሽ “ፕሬዝዳንት ፑቲን ወረራ ከመጀመራቸው በፊትም ቢሆን ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ 193 ሚሊዮን ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸው ነበር” የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል።

ያም ሆኖ የዓለም ባንክ ከነበረው 193 ሚሊዮን በተጨማሪ በጦርነቱ ምክንያት ለ40 ሚልዮን ህዝብ ሰብዓዊ እርዳታ ያሰፈልጋል ባለው መሰረት፤ አሜሪካ የምግብ እጥረት ያጋጠማቸው ሀገራት ስትደግፍ፤ ሩሲያ ግን ችግር በመፍጠር ላይ መሆኗ ተናግረዋል፡፡

በደቡብ አፍሪካ ቆይታ ያደረጉት ብሊንከን ቀጣይ ጉዞዋቸውን ወደ ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ መሆኑ ተገልጿዋል።

ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics

ዩክሬን በሩሲያ ጦር ላይ ድል እየተቀዳጀች መሆኑን ገለጸች


የዩክሬን ጦር በሩሲያ ጦር ተይዞ የነበረ አንድ ከተማ በመልሶ ማጥቃት መረከቡን አስታውቋል
የሩሲያ ጦር በካርኪቭ በኩል ኢዙም የሚባለውን አካባቢ ለመቆጣጠር ቢሞክርም ተምትቶ መመለሱ ተገልጿል

ዩክሬን ወደ ግዛቷ በገባው የሩሲያ ጦር ላይ ድል እየተቀዳጀች መሆኑን ገለጸች፡፡

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ከሩሲያ ጋር ወደለየለት ጦርነት የገባችው።

ሩሲያ ከኔቶ ለዩክሬን የተለገሱ 45 ሺህ ቶን ጥይት አወደምኩ አለች
168ኛ ቀኑ ላይ በሚገኘው በዚህ ጦርነት ከ20 በመቶ በላይ የሚሆነው የዩክሬን ክፍል በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር ውሏል።

ዩክሬን ከምዕራባዊያን በሚደረግላት የጦር መሳሪያ እና የገንዘብ ድጋፍ ሩሲያን በመመከት ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።

የዩክሬን ጦር በሩሲያ ጦር እጅ ስር ባለችው ካርኪቭ አቅራቢያ ባደረገው የመልሶ ማጥቃት ዶቭሄንክ የተባለች ከተማን ዳግም መቆጣጠሩን ሮይተርስ ዘግቧል።

በአካባቢው ያለችው ኢዙም እና አካባቢውን ለመቆጣጠር በማጥቃት ላይ የነበረው የሩሲያ ጦር በዩክሬን ጦር በደረሰበት ማጥቃት ማፈግፈጉም ተጠቅሷል።

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ አማካሪ የሆኑት ኦለክሲ አርሴቶቪች እንዳሉት ካርኪቭ ከተማን ከሩሲያ ለመንጠቅ ከፍተኛ ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የአሜሪካ መከላከያ ፖሊሲ ምክትል ጸሀፊ በበኩላቸው በዩክሬን ምድር እስከ 80 ሺህ የሩሲያ ወታደሮች እንደተገደሉባት እና እንደቆሰሉባት አክለዋል።

የሩሲያ መከላከያ በበኩሉ በደበባዊ ዩክሬን የሚገኘው ዛፖሪዝህዚያ የኑክሌር ማዕከልን ባሳለፍነው መጋቢት ላይ የተቆጣጠረችው ቢሆንም የዩክሬን ጦር ይሄንን ማዕከል ሀላፊነት ከሩሲያ ለመረከብ ሀላፊነት በጎደለው መንገድ ተኩስ መክፈቷን አስታውቃለች።

ዩክሬን በሩሲያ ላይ ድልን እንድትቀዳጅ ከአሜሪካ እና ምዕራባውያን ሀገራት የጦር መሳሪያ እየተደረገላት ይገኛል።

አሜሪካ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ለዩክሬን እንደምትሰጥ አስታውቃለች።

በአጠቃላይ አሜሪካ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 18 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያቆች ለዩክሬን መስጠቷን ዘገባው አክሏል።

የሩሲያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ኔድሜዴቭ በበኩላቸው ሩሲያ በዩክሬን ያሰበችውን እቅድ ማሳካቷ አይቀርም ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

News today, Politics

የአሜሪካ ፖሊስ የዶናልድ ትራምፕን መኖሪያ ቤትን ፈተሸ


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ቤት በኤፍ ቢ አይ ተፈተሸ

የአሜሪካ ፖሊስ የቀድሞውን የሃገሪቱን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መኖሪያ ቤትን በርብረዋል፡፡

በፍሎሪዳ የሚገኘውን የትራምፕን መኖሪያ የፈተሸው የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ) መሆኑን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡

ፍተሻው ዶናልድ ትራምፕ ምናልባትም በደጋፊዎቻቸው ከተፈጸመው የካፒቶል ሂል ጥቃት ጋር በተያያዘ ከቤተ መንግስት ያሸሹት ሚስጥራዊ ሰነድ ይኖር ይሆን በሚል የተካሄደ ነው መሆኑን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል፡፡

ትራምፕ ኒውዮርክ በሚገኘው ህንጻቸው ላይ ሳሉ ነው መኖሪያቸው የተፈተሸው።

“ማር-ኤ-ላጎ የሚገኘው ቅንጡ መኖሪያ ተከቦ ነው የሚገኘው፤ በብዙ የኤፍ.ቢ.አይ ፖሊሶች ተወርሮም ይገኛል” ሲሉ ዶናልድ ትራምፕ ሶሻል ትሩዝ በተሰኘ ማህበራዊ ሚዲያቸው አስታውቀዋል።

በቀጣዩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ (2024) እንዳይወዳደሩ ለማድረግ በማሰብ የተደረገ መሆኑንም ነው የገለጹት።

ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2024 ለሚካሄደው ምርጫ ለመወዳደር ያላቸውን ፍላጎት በይፋ ባይገልጹም፣ ባለፉት ጥዊት ወራት ለመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ትራምፕ ከካፒቶል ሂሉ ጥቃት እንዲሁም የተሸነፉበትን የምርጫ 2020ን ውጤት በኃይል ለመቀየር ሞክረዋል፤ ሌሎች ሚስጥራዊ ሰነዶችንም አሽሽተዋል ከመባሉ ጋር በተያያዘ በምርመራ ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

News today, Politics

ብሊንከን ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለመመከት ያለመ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለማሳደግ የምታደርገውን የዲፕሎማሲ ጥረት ለመመከት ያለመ ጉብኝት ጀመሩ።

ብሊንከን በዚህ ጉብኝታቸው ወደ ሦስት የአፍሪካ አገራት እንደሚጓዙ ይጠበቃል።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከደቡብ አፍሪካ በኋላ ወደ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ቀጥሎ ደግሞ ወደ ሩዋንዳ ይሄዳሉ ተብሏል።

የብሊንከን የመጀመሪያ መዳረሻ የሆነችው ደቡብ አፍሪካ በዩክሬኑ ጦርነት ሞስኮን ለማውገዝ የምዕራባውያንን ጥሪዎች ሳትቀበል ገለልተኛ ሆና ቆይታለች።

ከሁለት ሳምንታት በፊት የሩሲያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ስድስት ቀናትን በፈጀ ጉብኝት አዲስ አበባን ጨምሮ ወደ ተለያዩ አገራት ተጉዘው ነበር።

ላቭሮቭ የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በግብጽ ጀምረው ቀጥሎም ወደ ኮንጎ ብራዛቪል፣ ዩጋንዳ እና ኢትዮጵያ ተጉዘው ከባለስልጣናት ጋር ተገናኝተዋል።

በቆይታቸውም በተለይም በዩክሬኑ ጦርነት ምክንያት በአፍሪካ በተከሰተው የስንዴ አቅርቦት እጥረት ላይ ትኩረት ሰጥተው ንግግሮችን አካሂደው ለምግብ እጥረቱ ተጠያቂዎቹ ምዕራባዊያን አገራት ናቸው ሲሉም ተደምጠዋል።

“ምዕራባውያን አገራት የበላይነታቸውን በሌሎች ላይ ለመጫን እየሞከሩ ነው” ሲሉም ከሰዋል። እንዲሁም ሞስኮ የዓለምን የምግብ ቀውስ አስከትላለች የሚለውን ወቀሳ አጣጥለውታል።

News today, Politics

ቻይና፤ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተችየቻይና መከላከያ ሚኒስቴር “በታይዋን የባህር ወሽመጥ ላይ ላለው ውጥረት አሜሪካ ኃላፊነቱን ትወስዳልች” ብሏል


የፔንታጎን፣ የስቴት ዲፓርትመንት እና የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የቻይና እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ሲሉ በማውገዝ ላይ ናቸው

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት እጅጉን ያስቆጣት ቻይና፣ አሜሪካ የሚመጡትን “ከባድ መዘዞች መቻል ይኖርባታል” ስትል ዛተች፡፡

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዉ ኪያን በኦን ላይን ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፡ “በታይዋን የባህር ወሽመጥ ላይ ያለውን ውጥረት በትንኮሳ እንዲፈጠር ያደረገቸው አሜሪካ ናት፣ ስለዚህም አሜሪካ ለድረጊቷ ኃላፊነት በመውሰድ የሚከተሉ አስከፊ መዘዝ መሸከም ይኖርባታል” ብለዋል፡፡

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን አቋረጠች
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቻይና ወታደራዊ መርከቦች፣ አውሮፕላኖች እና ሰው አልባ አውሮፕላኖች በደሴቲቱ እና በባህር ሃይሏ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን የታይዋን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

“ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት” አውሮፕላኖችን እና መርከቦችን መላካቸውንም ጭምር አስታውቋል ታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር፡፡

በፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት የተቆጣችው ቻይና ለአሜሪካ ምላሽ ነው በሚል አስካሁን በታይፔ ላይ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን የመተኮስ ሙከራዎች ከማድረግ በተጨማሪ ከአሜሪካ ጋር የነበሯት የመከላከያ ፖሊሲ ማስተባበሪያን እና የባህር ኃይል-ወታደራዊ ምክክርን ያካተቱ መደበኛ ንግግሮችን መሰረዟ ባሳለፍነው አርብ ይፋ አድርጋለች፡፡

የፔንታጎን፣ የስቴት ዲፓርትመንት እና የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት የቻይና እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ነው ሲሉ አውግዘውታል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፤ቻይና የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማቆም አደንዛዥ እጾች፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ በስምንት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ የወሰደችው አጸፋዊ እርምጃ፤ አሜሪካን ብቻ ሳይሆን ዓለምን የሚቀጣ ነው ሲሉ ከቀናት በፊት መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

ብሊንከን “የአየር ንብረት ትብብርን ማገድ አሜሪካን ብቻ ሳይሆን ዓለምን በተለይም በማደግ ላይ ያሉትን ሀገራት የሚቀጣ ነው።በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው ልዩነት ምክንያት ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ትብብሮችን እንደ መያዣ መጠቀም የለብንም” ሲሉ መደመጣቸውም ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ቻይና በታይዋን ዙሪያ እየፈጸመች ያለውን አደገኛና በቀጠናው አለመረጋጋት ሊፈጥር የሚችል ድርጊትን በተመለከተ ዋሽንግተን ከአጋሮቿ እየሰማች ነው ያሉት ብሊንከን ፤ “ ዋሽንግተን ጉዳዩን በምታስተናግድበት መንገድ እያስተናገደች ጸንታ ትቀጥላለች”ም ብለዋል ብሊንከን፡፡

News today, Politics

ሩሲያ፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ “ዛፖሪዥያ ኒውክሌር ጣቢያ” ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰች

ሩሲያ፤ ዩክሬን የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ ላይ የከፈተችው ተኩስ “ከባድ መዘዝ” የሚያስከትል ነው ስትል አስጠንቅቃለች

ዩክሬን በበኩሏ ክሬምሊንን በዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ላይ “የኒውክሌር ሽብር” ፈጽማለች ስትል ከሳለች

የሩሲያ ቤተ መንግስት ክሬምሊን፤ የዩክሬን ጦር በግዙፉ የዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ላይ ተኩስ ከፍቷል ስትል ከሰሰ።

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን የሚገኘው ዛፖሪዥያ አቶሚክ ሃይል ማመንጫ በአውሮፓ ትልቁና በዓለም ላይ ካሉት 10 ትላልቅ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያዎች መካከል አንዱ ነው።

እናም ሩሲያ ፤ የዩክሬን ጦር ግዙፉን የኒውክሌር ጣቢያ ለማውደም ተኩስ ከፍተዋል በማለት ኪቭን ከሳለች።

ሩሲያ፤ ዩክሬን ግዙፉን አቶሚክ ሃይል ማመንጫ ጣቢያ ማውደሟ “አሰቃቂ መዘዝ” ይዞ ሊመጣ እንደሚችል ልታውቅ ይገባል ስትል አስጠንቅቃለች።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “የዩክሬን ታጣቂ ሃይሎች የኒውክሌር ጣቢያን ማውደም ከዩክሬን ባለፈ ለአውሮፓ ምድር እጅግ አደገኛ ሊሆን የሚችል ተግባር ነው”ሲሉ ተደምጠዋል።

የዩክሬን አጋሮች “እንዲህ ዓይነቱ የዩክሬን እርምጃ እንዳይቀጥል ተጽእኖ ያድርጉ” ሲሉም ጠይቀዋል ቃል አቀባዩ።

ሩሲያ ይህን ትበል እንጅ ዩክሬን በተቃራኒው፤ የሩሲያ ኃይሎች በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ኩባንያው ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል የሚል ክስ በማቅረብ ላይ ናት።

ጥቃቱን ተከትሎ መግለጫ የሰጡት የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ “የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጠንካራ ምላሽ” እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርበዋል።

ፕሬዝዳንቱ፤ በሞስኮ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦች ለመጣል በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ከአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ጋር መነጋገራቸውንም አስታውቋል ።

ክሬምሊንን “የኒውክሌር ሽብር” ፈጽማለች ሲሉም ከሷል ፕሬዝዳንት ዘሌንስኪ።

News today, Politics

የዩክሬኗ ዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ


የዛፖሮዝሂ ክልል በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን ትገኛለች
እስካሁን በዛፖሮዝሂ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ የዘገቡት የሩሲያ ሚዲያዎች ናቸው

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን የምትገኘው የዛፖሮዝሂ ክልል ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል ሕዘበ ውሳኔ ልታደርግ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ግዛቲቱ ወደ ሩሲያ ለመጠቃለል ሕዝበ ውሳኔ እንደምታደርግ አስተዳዳሪው መግለጻቸውን የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

የሩሲያ ጦር የተቆጣጠራቸው የዩክሬን ግዛቶች ወደ ሩሲያ ለመቀላቀል ህዝበ ውሳኔ ሊያካሂዱ ነው
የግዛቲቷ አስተዳዳሪ ከሩሲያ ጋር ለመቀላቀል የሚስችል ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ ያስታወቁት ዛሬ ነው፡፡

የግዛቲቱ ደቡባዊ ክፍል አሁን ላይ በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን ሙሉ ግዛቱ ግዛቱ ሕዝበ ውሳኔ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሕዝበ ውሳኔው ከዩክሬን ጋር መቀጠል ወይስ ወደ ሩሲያ ግዛት መጠቃለል የሚሉ ምርጫዎች እንዳሉትም ነው የተገለጸው፡፡

የግዛቲቱ አስተዳዳሪ ኢቭጌኒ ባሊትስኪ ጉባዔ በተደረገበት ወቅት ሕዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ተብሏል፡፡

የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን የሆኑት ሩሲያ ቱዴይ እና ታስ እንደዘገቡት ከሆነ ከ700 በላይ የሚሆኑ ተወካዮች ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አጽድቀዋል ብለዋል፡፡

በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በምትገኘው ዛፖሮዚ ግዛት ይደረጋል የተባለው ሕዝበ ውሳኔ በመስከርም ወር ሊካሄድ እንደሚችል ፍንጭ ተሰጥቷል፡፡

በዛፖሮዚ ግዛት ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ውሳኔ መተላለፉን በተመለከተ የዘገቡት የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ብቻ ናቸው፡፡

ሩሲያ በምስራቅ ዩክሬን ውስጥ ላሉ ተገጣይ ግዛቶች እውቅና ሰጠች
አሁን ላይ ሕዝበ ውሳኔ ይደረግባታል ተብላ የምትጠበቅ ግዛት ግማሽ ክፍል በሩሲያ ወታደሮች የተያዘው ገና ሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በጀመሩ ሰሞን ነበር፡፡

የተወሰነው የግዛቲቲ ክፍል ብቻ በዩክሬን ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት አራት ወራትን የተሻገረ ሲሆን አሁንም አልተቋጨም፡፡

News today, Politics

ሩሲያ፤ ፑቲንና ዘለንስኪ የሚገናኙበት ምክንያት እንደሌለ አስታወቀች

ሁለቱ ፕሬዝዳንቶች መገናኘት ካለባቸው እንኳን ተደራዳሪዎች ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ነው ተብሏል
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭለድሚር ፑቲን እና የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ሊገናኙ የሚችሉበት ምክንያት እንደሌለ ክሬምሊን አስታወቀ፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፒስኮቭ ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር የሚገናኙበት ምንም መሰረት እንደሌለ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

ፒስኮቭ መሪዎቹ መገናኘት ካለባቸው እንኳን የሚገናኙት የተሰየሙት ተደራዳሪዎች ስራቸውን ከሰሩ በኋላ ብቻ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬን ከጦርነት በኋላ ድርድር የጀመሩ ቢሆንም እስካሁን ግን ትልቅ ለውጥ ያመጣ ውሳኔ አልተወሰነም፡፡

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣኢብ ኤርዶሃን ጦርነት ውስጥ የገቡት የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተነናኝተው እንዲመክሩ ሀሳብ አቅርበው ነበር፡፡

ይሁንና ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፒስኮቭ፤ ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር ሊነጋገሩ ቢችሉ እንኳን ተደራዳሪዎች የተሰጣቸውን የቤት ስራ ሰርተው ካጠናቀቁ በኋላ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ሁለቱም ወገኖች የተጀመረው ድርድር ውጤት አለማምጣቱን ቢናገሩም ውጤት ላለመገኘቱ ግን እርስ በእርስ ግን እየተወነጃጀሉ ነው፡፡

ዲሚትሪ ፒስኮቭም አሁን ላይ እየተደረገ ያለ ንግግር እንደሌለና ለዚህም ተጠያቂዎቹ ዩክሬንን የወከሉ ተደራዳሪዎች እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ሞስኮ እና ኪቭ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ይፋዊ ድርድር ጀምረው የነበረ ቢሆንም ዩክሬን፤ የሩሲያ ኃይሎች ከክሪሚያ ጭምር እንዲወጡ ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት አማካሪ አሌክሰይ አርስቶቪች ሀገራቸው፤ የሩሲያ ወታደሮች ከክሬሚያ እና ዶንባስ ግዛቶች እንዲወጡላት እንደምትፈልግ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

“አሁን ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር መገናኘታቸው አስፈላጊ አይደለም” ያሉት የፑቲን ቃል አቀባይ፤ በዩክሬንም ሆነ በሩሲያ ወገን ያሉት ተደራዳሪዎች ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ምናልባት ሁለቱ ፕሬዝዳንቶች የመገናኘት ዕድል ሊኖራቸው ይችላል ብለዋል፡፡

News today, Politics

የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ “ሩሲያ በዩክሬን ያላትን አላማ ታሳካለች” አሉ


ሜድቬድየቭ “ምዕራባውያን ሩሲያን ለማጥፋት የረዥም ጊዜ እቅድ አላቸው” ሲሉም አስጠነቅቀዋል
የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ “ሩሲያ በዩክሬን ያላትን አላማ ታሳካለች” አሉ፡፡


የፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቅርብ ሰው እንደሆኑ የሚነገርላቸው ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ ፤ “ምዕራባውያን ሩሲያን ለማጥፋት የረዥም ጊዜ እቅድ አላቸው” ሲሉም ከሩሲያው ኒውስ ኤጀንሲ ታሳ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ተናግረዋል፡፡


ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ የጸጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ፤ “ሩሲያ በዩክሬን ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ እያካሄደች ነው እናም በምትፈልገው መልኩ ሰላምን እያመጣች ነው” ማለታቸውም ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ሜድቬድየቭ፤ እንደፈረንጆቹ የ2008 የጆርጂያ ጦርነት ፣ የኔቶ ወታደራዊ ህብረት ማጠናከር እና የአሁኑ የዩክሬን ጦርነት፤ አሜሪካ ና አጋሮቿ ሩሲያን ለማጥፋት እስካሁን ያደረጓቻ ሙከራዎች አካል መሆናቸውም በአብነት አንስተዋል።


“ዓላማው አንድ ነው፤ ሩሲያን ለማጥፋት” ሲሉም አክለዋል የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬድየቭ፡፡
በዩክሬን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በእቅዳቸው መሰረት እየሄደ መሆኑን ፕሬዝዳንት ፑቲን ቀደም ሲል ገልጸው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
“በዩክሬን ያለው ጦራችን በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተልዕኮውን በሚገባ እየፈጸመ ነው፣ በዩክሬን መስራት ያለብንን ስራዎች ሁሉ እያከናወኑ ነው”ም ነበር ያሉት ፕሬዘዳንት ፑቲን፡፡


የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቪላድሚር ፑቲን ከወራት በፊት በሰጡት አጭር መግለጫ “ሊስቆመን የሚሞክር፣ በሀገራችን እና በህዝባችን ላይ ተጨማሪ አደጋ የሚጥል ማንኛውም አካል በታሪኩ አይቶት የማያውቀው እጣፋንታ ይገጥመዋል” ሲሉ ምእራባውያን ማስጠንቀቃቸውም አይዘነጋም፡፡
የሩሲያ ምላሽ ፈጣን እንደሚሆን የገለጹት ፕሬዝዳንት ፑቲን የወታደራዊ ዘመቻው አላማ በኪቭ አስተዳደር ለበርካታ አመታት ጥቃት እና የዘርማጥፋት ሲፈጸምባቸው የነበሩትን ዜጎች መታደግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

News today, social life

የአውስትራሊያው አየር መንገድ ባለሥልጣናት ሻንጣ በማውረድና በመጫን እንዲያግዙት ጠየቀ

ሻንጣ እያወረ ያለ ሰው

የአውስትራሊያው አየር መንገድ ካንታስ የጉልበት ሠራተኞች እጥረት ስላጋጠመው የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ሻንጣ በመጫን እና በማውረድ እንዲያግዙት ጠየቀ።

የአየር መንገዱን የዕለት ከዕለት የመንገደኞች ማስተናገድ ሥራውን የሚካታተለው ክፍል እንደገለጸው፣ ሲድኒ እና ሜልበርን ውስጥ በሚገኙ አየር ማረፊያዎች ቢያንስ 100 በጎ ፈቃደኛ የጉልበት ሠራተኞችን እንደሚፈልግ አስታውቋል።

ካንታስ የሚፈልጋቸው የጉልበት ሠራተኞች ሻንጣዎችን ከአውሮፕላኖች ላይ በማውረድና በመጫን እንዲሁም ሻንጣ የሚጫንባቸው ተሽከርካሪዎችን በአየር ማረፊያዎች ውስጥ የሚያንቀሳቅሱ ሾፌሮችን ነው።

በኮሮናቫይረስ ምክንያት አገራት ድንበሮቻቸውን ለአየር በረራዎች ዝግ አድርገው ከቆዩ በኋላ አሁን መክፈት በመጀመራቸው፣ ካንታስን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ አየር መንገዶች የተለያዩ ፈተናዎች እየገጠሟቸው ነው።

“ጉንፋን እና ኮቪድ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራጨቱ እና በገበያው ላይ ሠራተኞችን ለማግኘት ያለው ፈተና አየር መንገዶች ሥራቸውን በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዳያከናውኑ እንቅፋት ፈጥሯል” ሲሉ የካንታስ ባለሥልጣን የሆኑት ኮሊን ሁግስ ለቢቢሲ በኢሜይል ገልጸዋል።

“ያለው አማራጭ በከፍተኛ ኃላፊነት ላይ ሙሉ ጊዜያቸውን ወደሚሰሩ ሰዎች ፊትን ማዞር ነው” ሲሉም ሁግስ አክለዋል።

በዚህም ሳቢያ የካንታስ አየር መንገድ ሥራ አመራሮች ለቀጣይ ሦስት ወራት በፈረቃ፣ በቀን ለስድስት ወይም ለአራት ሰዓታት፣ በሳምንት ለሦስት ወይም ለአምስት ቀናት ሻንጣ የመጫን እና የማውረድ ሥራን እንዲያከናውኑ ተጠይቀዋል።

ካንታስ ባሰራጨው መልዕክት ላይ ለሻንጣ ጫኝነት እና አውራጅነት የሚያመለክቱ ኃላፊዎች ብቻቸውን አስከ 32 ኪሎ ግራም የሚመዝን ክብደት የማንሳት አቅም ሊኖራቸው ይገባል።

“አስካሁን ባለው ሥራችን የደንበኞቻችንን ፍላጎት እና የሚጠበቀውን ደረጃ ማሟላት እንዳላቻልን ግልጽ ነው፣ ስለዚህ ሥራችንን ለማሻሻል ሁሉንም ነገሮች ማድረግ ይጠበቅብናል” ሲሉ የካንታስ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

አየር መንገዱ ከዚህም በፊት ከፍተኛ የመንገደኞች ቁጥር ለማስተናገድ በተገደደበት ጊዜ 200 የሚደርሱ የቢሮ ውስጥ ሠራተኞቹን በተመሳሳይ ሥራ ላይ እንዲያግዙት ማድረጉን አመልክቷል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት አገራት የአየር ክልሎቻቸውን መዝጋታቸውን ተከትሎ ከባድ ቀውስ ከገጠማቸው አየር መንገዶች መካከል ካንታስ አንዱ ነው።

በዚህም ሳቢያ በመላው ዓለም ያሉ አየር መንገዶች በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞቻቸውን መቀነሳቸው ይታወሳል።

አገራት የወረርሽኙን መስፋፋት ለመግታት ወስደዋቸው የነበሩትን ጥብቅ እርምጃዎችን በአሁኑ ወቅት ማላላት በመጀመራቸው ካንታስ እና ሌሎች አየር መንገዶች ሥራቸውን በቀደመው መልኩ ለማካሄድ ፈተና ገጥሟቸዋል።

News today, social life

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው

ዶ/ር ቴድሮስ እንዳልተከተቡ የሚሳዩ ናቸው በሚል የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ሃሰተኛ መሆናቸውንም ድርጅቱ አስታውቋል
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የኮሮና ክትባቶችን አልተከተቡም መባሉ እያነጋገረ ነው።

ዶ/ር ቴድሮስ አለመከተባቸውን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች (ቪዲዮ) ተለቀዋል።
የምስሎቹን እውነተኛነት ያጣጣለው የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ አልተከተቡም መባሉን ያለ ሲሆን፤ የድርጅቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ሳይቀሩ ጉዳዩን በማስተባበል ላይ መሆናቸውም ነው የተነገረው።

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በመሆን በድጋሚ ተመረጡ 
በተለያዩ የማህበረሰብ ትስስር ገጾች በመዘዋወር ላይ ያለው ቪዲዮ ዶ/ር ቴድሮስ በአንድ ጆን ኮኸን በተባለ ሰው መቼ እንደተከተቡ ሲጠየቁ እና ክትባቶቹ በአፍሪካ በተለይም ኢትዮጵያ እስከሚደርሱ ድረስ ሳይከተቡ እንደሚቆዩ ሲናገሩ ያሳያል።

ሆኖም ቪዲዮው ሃሰተኛ ነው ሲል ድርጅታቸው አስተባብሏል። እንዲህ ዐይነቱ የፈጠራ ወሬ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር አሁንም በመደረግ ላይ ያሉ ጥረቶችን ይጎዳል ሲልም ነው ጉዳዩን ባስተባበለበት ጽሁፉ የገለጸው።
እንደ ድርጅቱ ከሆነ ዶ/ር ቴድሮስ ባለፈው ዓመት ግንቦች ላይ የመጀመሪያውን ክትባት ወስደዋል። ከዚያም ወዲህ የማጠናከሪያ ክትባቶችን ተከትበዋል።

የድርጅት ቃል አቀባይ ጋቢ ስተርን ትናንት እሁድ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ “ውሸታሞች ሲዋሹ እና ህይወትን አደጋ ላይ ሲጥሉ እርምጃ መወሰድ አለበት” ብለዋል፤ መጻፋቸው በዶ/ር ቴድሮስ ላይ የተነዛውን ውሸት ለማስተባበል እንደሆነ በመጠቆም።
“ቁም ነገሩ ክትባቶች ህይወትን መታደጋቸው ነው”ም ብለዋል ቃል አቀባዩ።
ዶ/ር ቴድሮስን ጠያቂው ጆን ኮኸን ዋና ዳይሬክተሩ አልተከተብኩም በሚል የተናገሩት ነገር እንደሌለ ተናግሯል።

ባሳለፍነው ሰኔ በሳይንስ መጽሄት ላይ የወጣ መጣጥፍ ዶ/ር ቴድሮስ በባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት 2021 ግንቦት ላይ መከተባቸውን ያትታል።
ክትባቶች እያሉ ቀደም ብለው ለምን እንዳልተከተቡ የተጠየቁት ዋና ዳይሬክተሩ “ኢትዮጵያ ከምትባል ደሃ ሃገር እና አፍሪካ ከሚባል ደሃ አህጉር መምጣቴን አውቃለሁ፤ ስለሆነም አፍሪካ እና ሌሎች ደሃ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሃገራት ክትባቱን እስከሚያገኙ ለመጠበቅ እፈልግ ነበር” ሲሉ መመለሳቸውንም ያስቀምጣል።

“ከኮሮና ክትባቶች ጋር በተያያዘ ዓለም ‘አስከፊ’ የሞራል ውድቀት እየደረሰበት ነው”- ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር)
በሌላ አገላለጽ ኢ-ፍትሐዊውን የክትባቶች ስርጭት በድርጊት እየተቃወሙ መሆኑንም ነው ዶ/ር ቴድሮስ የሚናገሩት።

ሆኖም አሁን በማህበራዊ ሚዲያዎች በመዘዋወር ላይ ያለው አጭር ቪዲዮ ይህን ምላሻቸውን በማካተት ከተዘጋጀ ዘጋቢ ፊልም (ዶክመንታሪ) ላይ ብዙዎችን ሊያሳስት በሚችል መልኩ ተቀንጭቦ መለቀቁን ነው ተቋማቸው ያስታወቀው።

News today, Politics

የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው


ቻይና የአሜሪካ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታዋንን መጎብኝቷን ተከትሎ ነበር የጦር ልምምዱን የጀመረችው

የቻይና የጦር ልምምድ ትናንት ይጠናቀቃል ቢባልም ልምምዱ እንደቀጠለ ነው

ቻይና በታይዋን አቅራቢያ የጀመረችው የጦር ልምምድ እንደቀጠለ ነው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ጨምሮ አምስት የእስያ ሀገራትን መጎብኘታቸውን ተከትሎ በሩቅ ምስራቅ የነገሰው ውጥረት እንደቀጠለ ነው።

አፈ ጉባኤዋ ባሳለፍነው ሳምንት ታይዋንን የጎበኙ ሲሆን ድርጊቱ ቻይናን እንዳስቆጣ የዓለም ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል።

ይሄንን ተከትሎም ቻይና በታይዋን ባህር ዙሪያ እስከ ቀጣዩ ትናንት ድረስ የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ መሆኗን አሳውቃ ነበር።

ይሁንና የቻይና ወታደራዊ የጦርነት ልምምድ ትናንት ያበቃል ተብሎ ቢጠበቅም ልምምድ ዛሬም እንደቀጠለ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል።

የቀጠለው ወታደራዊ ልምምድም የአየር፣የባህር እና የየብስ ጦርነት ልምምድ ሲሆን ታይዋን እና የቡድን ሰባት ሀገራት ልምምዱን ተችተዋል።እንደ ዘገባው ከሆነ ቻይና በታይዋን 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በስድስት አቅጣጫ የጦርነት ልምምዱ እንደቀጠለ ይገኛል ተብሏል።

ቻይና ባሳለፍነው ሳምንት ልምምድ ላይ ዶንግ ፋንግ የተሰኘው የቻይና የረጅም እና አጭር ርቀት ባልስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ታይዋን ባህር ተኩሳለች።

በታይዋን ስድስት አቅጣጫዎች ምንም አይነት የባህር እና አየር ላይ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ቻይና አስቀድማ ማስጠንቀቋ ይታወሳል ።ታይዋን የቻይና ድርጊት የጦርነት ትንኮሳ መሆኑን አስታውቃ እስከ እሁድ የሚቆየውን የጦር ልምምድ እንደማትታገሰው አስቀድማ ተናግራም ነበር።

በቀጠለው የቻይና በታይዋን ባህር አቅራቢያ የጀመረችው የጦር ልምምድ ታይዋን እስካሁን በይፋ የሰጠችው መግለጫ የሌለ ሲሆን ቻይናም ልምምዱ እስከመቼ እንደሚቀጥል አላሳወቀችም።

News today, Politics

ተጠባቂው የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ነገ ይካሄዳል


August 8, 2022
በዚህ ምርጫ ላይ 22 ሚሊየን ኬንያዊያን በመራጭነት ድምጽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል
ተጠባቂው የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ነገ ይካሄዳል።
ኬንያን በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ለመምራት የምረጡኝ ቅስቀሳቸው ሲያካሂዱ የነበሩ እጩ ፕሬዝዳንቶች ምርጫ ነገ እንደሚካሄድ ቢቢሲ ዘግቧል።
ኬንያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት አራት እጩዎች የቀረቡ ሲሆን ባለፉት ምርጫዎች ላይ ለአራት ጊዜ ተወዳድረው ሽንፈትን ያስተናገዱት የኦሬንጅ ዲሞክራቲክ ሙቭመንቱ ራይላ ኦዲንጋ ዋነኛው ተፎካካሪ ናቸው፡፡

ራይላ ኦዲንጋ በፈረንጆቹ 1997 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራቸውን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት እጩ የነበሩ ሲሆን በምርጫው ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡
በነዳጅ እና ሀይል ልማት ዘርፍ ነጋዴ የሖኑት የ77 ዓመቱ ኦዲንጋ ላለፉት አራት ተከታታይ ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ወቅቶች ላይ እጩ ቢሆኑም አብላጫ የህዝብ ድምጽ ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
ውጤታቸውን ተከትሎም ራይላ ኦዲንጋ ከፕሬዝዳናታዊ ምርጫ ራሳቸውን ማግለላቸውን ከአምስት ዓመት በፊት ቢናገሩም ዘግይተው በሰጡት መግለጫ ለአምስተኛ ጊዜ ለፕሬዝዳንትነት መልሰው እንደሚወዳደሩ አሳውቀዋል፡፡
ኬንያን አሁን ላይ በምክትል ፕሬዝዳንትነት እያገለገሉ ያሉት የዲሞክራቲክ ዩኒየኑ ዊሊያም ሩቶ ሌላኛው እጩ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የራይላ ኦዲንጋ ዋነኛ ተፎካካሪ ናቸው ተብሏል፡፡
የ55 ዓመቱ ሩቶ ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በግጭት ውስጥ ሲሆኑ የጸባቸው መንስኤ ደግሞ ፕሬዝዳንቱ ለራይላ ኦዲንጋ ድጋፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው፡፡
ከራይላ ኦዲንጋ እና ዊሊያም ሩቶ በተጨማሪ ለኬንያ ፕሬዝዳንትነት እየተፎካከሩት ያሉት ቀሪዎቹ እጩዎች ዳቪድ ዌሂጋ ጆርጅ ዋጃኮያህ ናቸው፡፡
የሬጌ ሙዚቃ ወዳጅ እንደሆኑ የሚናገሩት እጩ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዋጃኮያህ የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
እጩ ፕሬዚዳንቱ በምርጡኝ ቅስቀሳቸው ላይ ማሪዋና የተሰኘው አደገኛ እጽ ማንኛውም አርሶ አደር እንዲያመርተው እና ምርቱን መጠቀም የፈለጉ ሁሉ በነጻነት እንዲጠቀሙት አደርጋለሁ፣ እንዲሁም ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ እንሲያስገኝ አደርጋለሁ ብለዋል።

የእባብ መርዝ በስፋት በማምረት ለኬንያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ መንገድ አደርጋለሁ ማለታቸው የብዙ ኬንያዊያንን ትኩረት እንዲስቡ ማድረጋቸውም ተገልጿል።
ኬንያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት 55 እጩዎች ቀርበው የነበሩ ቢሆንም በመጨረሻም አራት ብቻ ቀርተዋል።
ኬንያን ላለፉት 10 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት የመሩት ኡሁሮ ኬንያታ የስልጣን ጊዜያቸውን ከሁለት ጊዜ በላይ ማራዘም ስለማይችሉ ለተመራጩ ፕሬዝዳንት እንዲያስረክቡ የሀገሪቱ ህገ መንግስት ያስገድዳቸዋል።

News today, Politics

እስራኤል በጋዛ ባደረሰችው ጥቃት ሁለት የታጣቂ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ፍልስጤማውያን ተገደሉ

Ke alemi zuriya-ከዓለም ዙሪያ

በአየር ጥቃቱ የፈረሰ ቤት

7 ነሐሴ 2022

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን (ፒአይጄ) ሁለት አመራሮች አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ፍልስጤማውያን ተገደሉ።

አመራሮቹ ካሊድ መንሱር እና ጣይር ጃብሪ፣ በርካታ የቡድኑ ተዋጊዎችና ስድስት ህፃናትን ጨምሮ 32 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸው ተዘግቧል።

ከአርብ ጀምሮ ወደ 400 የሚጠጉ የፍልስጥኤም ሮኬቶች እና ሞርታሮች በእስራኤል ላይ መተኮሳቸውን የእስራኤል ባለስልጣን ተናግረዋል።

እስራኤል ወታደራዊ ዘመቻ ብላ የምትጠራውን ይህንን የአየር ጥቃት የጀመረችው የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን በደቀነው ከፍተኛ ስጋት ነው ብላለች።

ባለፈው አመት ግንቦት ወር ለ11 ቀናት በዘለቀው እና ከ200 በላይ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም በርካታ እስራኤላውያን ከተገደሉበት ግጭት ወዲህ ይህ በቅርቡ በእስራኤልና በጋዛ መካከል የተከሰተ አሳሳቢ ግጭት አድርጎታል።

‘ብሬኪንግ ዳውን’ ( መሰባበር) የሚል የኮድ ስም እስራኤል የሰጠችው ወታደራዊ ዘመቻ ለአንድ ሳምንት ሊቆይ እንደሚችል ባለስልጣናቷ አስጠንቅቀዋል።

በሁለተኛው ቀን ጥቃት ትናንት ቅዳሜ በደቡባዊ ጋዛ ራፋህ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ከፍተኛ የፒአይጄ መሪ ካሊድ መንሱርን መግደሏን አስታውቃለች።

ከጋዛ ውጭ ወታደራዊ ጥቃቶችን ፈጽሟል በማለት እስራኤል የምትከሰው ካሊድ መንሱር ከዚህ ቀደም በእስራኤል ጦር ከአምስት የግድያ ሙከራዎች ተርፎ ነበር።

ከሱ ሞት በፊት አርብ እለት ከፍተኛ የፒአይጄ አመራር የሆነው ታይሲር ጃባሪ በእስራኡል የአየር ጥቃት ተገድሏል።

እንዲሁም በጋዛ በተፈጸመው የአየር ጥቃት ድብደባ በርካታ የቡድኑ አባላት ከመገደላቸው በተጨማሪ እስራኤል ተቆጣጥራት ባለቸው የዌስት ባንክ በተደረገ ከበባ 19 የሚሆኑ የፒአይጄ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እስራኤል ገልጻለች።

የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለፍልስጥኤማውያን ሞት እንዲሁም ለቆሰሉት 203 ሰዎች “የእስራኤል ወራራን ተጠያቂ አድርጓል።

News today, Politics

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ደቡብ አፍሪካ ደርሰዋል

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን

ብሊንከን በአፍሪካ ጉብኝታቸው ከፕሪቶሪያ በተጨማሪ ኬንሻሳ እና ኪጋሊን ይጎበኛሉ ተብሏል

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መጀመራን ተከትሎ በሩሲያ ላይ ጫና ለመፍጠር ከወራት በፊት በመንግስታቱ ድርጅት በተጠራ ስብሰባ ላይ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጋቸው አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያንን አስቆጥቷል።

ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ ጊዜያት የአሜሪካ እና አውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ አፍሪካ በመጓዝ ጫና በማድረግ ላይ ናቸው።

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም የመነጠል ስራውን ለማጠናከር የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።

ብሊንከን ከሰዓታት በፊት ደቡብ አፍሪካ መዲና ፕሪቶሪያ የደረሱ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ስሪል ራሞፎሳ ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

ብሊንከን ከደቡብ አፍሪካ በተጨማሪም ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።

ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።

ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ከነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ በግጭት ውስጥ ያሉት ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል እንደሚሰሩም ተገልጿል።

እንዲሁም አንቶኒ ብሊንከን በኪጋሊ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ጋር በስህተት ስለታሰሩት የሆቴል ሩዋንዳ ፊልም ሰሪ ፖል ሩሴሳባጊና ጉዳይ እንደሚወያዩም ይጠበቃል ተብሏል።

የአንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት የሩሲያው አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ መሆኑ የጉዟቸው አላማ የሩሲያን ተጽዕኖ ከአፍሪካ ለመነጠል ያለመ እንደሆነ ሌሎች ዘገባዎች እየወጡ ይገኛል።

አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ

በጥቃቱ ከ265 የሚልቁ ሰዎችም ቆስለዋል ተብሏል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት

ከሟቾች መካከል ሁለት የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን አመራሮች ይገኙበታል

እስራኤል በጋዛ በሰነዘረችው ጥቃት የሟቾች ቁጥር 32 ደረሰ።

በየጊዜው ግጭት ውስጥ የሚገቡት እስራኤል እና ፍልስጥም አሁንም መልሰው ግጭት ውስጥ ገብተዋል።

የእስራኤል ጦር ባሳለፍነው ሰኞ የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን መሪ የሆኑት ባሳም አልሳዲን በዌስት ባንክ ማሰራቸውን ተከትሎ በጋዛ አውዳሚ ግጭት ተቀስቅሷል።

በጋዛ ሰርጥ ውስጥ እየተካሄደ ባለው በዚህ ጦርነት እስራኤል በተኮሰቻቸው የሮኬት ጥቃቶች የሞቱ ሰዎች ቁጥር 32 መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።

ከ265 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ዘገባው አክሏል።

ከሟቾች ውስጥ ስድስቱ ህጻናት ሲሆኑ አራቱ ደግሞ ሴቶች እንደሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የሟቾች እና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተጠቅሷል።

የእስራኤል ጦር የእስላሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን ምክትል መሪ ካሊድ ማንሱርን በጋዛ ሰርጥ በሮኬት ጥቃት መግደሏን አስታውቃለች።

የእስራኤል ጦር በፍልስጤም ጋዛ እንደሚንቀሳቀስ የተገለጸው የእስልሚክ ጅሀድ የተሰኘው ቡድን የሚለውን ለመስማት በሚል የተኩስ አቁም አውጇል።

የፍልስጤም ጤና ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ እስራኤል የምትተኩሳቸው የሮኬት ጥቃቶች ንጹሀንን እየገደለ መሆኑን ገልጿል።

News today, Politics

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ


ብሊንከን በአፍሪካ ጉብኝታቸው ከፕሪቶሪያ በተጨማሪ ኬንሻሳ እና ኪጋሊን ይጎበኛሉ ተብሏል
የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር አንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀመሩ።
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት መጀመራን ተከትሎ በሩሲያ ላይ ጫና ለመፍጠር ከወራት በፊት በመንግስታቱ ድርጅት በተጠራ ስብሰባ ላይ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ድምጸ ተዓቅቦ ማድረጋቸው አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባዊያንን አስቆጥቷል።
“ሉዓላዊነትን እና ግዛታዊ አንድነትን ማክበር ለአፍሪካ ቀንድ መረጋጋትና ልማት አስፈላጊ ነው” – ብሊንከን 
ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በተለያዩ ጊዜያት የአሜሪካ እና አውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ አፍሪካ በመጓዝ ጫና በማድረግ ላይ ናቸው።
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያን ከተቀረው ዓለም የመነጠል ስራውን ለማጠናከር የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።
ብሊንከን ከሰዓታት በፊት ደቡብ አፍሪካ መዲና ፕሪቶሪያ የደረሱ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ስሪል ራሞፎሳ ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።
ብሊንከን ከደቡብ አፍሪካ በተጨማሪም ሩዋንዳን እና ዲሞክራቲክ ኮንጎን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።
ብሊንከን በአፍሪካ ቆይታቸው በምግብ ደህንነት ፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ ንግድ እና ጤና ጉዳዮች ዙሪያ ከአፍሪካ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።
ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ከነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ በግጭት ውስጥ ያሉት ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ ግንኙነታቸው እንዲሻሻል እንደሚሰሩም ተገልጿል።
እንዲሁም አንቶኒ ብሊንከን በኪጋሊ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ጋር በስህተት ስለታሰሩት የሆቴል ሩዋንዳ ፊልም ሰሪ ፖል ሩሴሳባጊና ጉዳይ እንደሚወያዩም ይጠበቃል ተብሏል።
አንቶኒ ብሊንከንና ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ተወያዩ 
የአንቶኒ ብሊንከን የአፍሪካ ጉብኝት የሩሲያው አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ሶስት የአፍሪካ ሀገራትን ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ መሆኑ የጉዟቸው አላማ የሩሲያን ተጽዕኖ ከአፍሪካ ለመነጠል ያለመ እንደሆነ ሌሎች ዘገባዎች እየወጡ ይገኛል።
አንቶኒ ብሊንከን የአሁኑ የአፍሪካ ጉብኝት ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ባሳለፍነው ህዳር ላይ ናይጀሪያ፣ ሴኔጋል እና ኬንያን ጎብኝተው መመለሳቸው ይታወሳል።

News today, Politics, social life

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጣለች

የሞስኮ ማዕቀብ ካናዳ ከዚህ በፊት በሩሲያዊያን ላይ ለጣለችው ማዕቀብ የአጸፋ እርምጃ ነው ተብሏል

ሩሲ እና ካናዳ

ሩሲያ ካናዳዊያን ዲፕሎማቶች፣ የሀይማኖት መሪዎች፣ ፖለቲከኞችና ምሁራን ላይ ነው ማዕቀብ ጣለችው

ሩሲያ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታውቃለች።

ሩሲያ ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ወደ ይፋዊ ጦርነት የገባችው።

 ይሄንን ጦርነት ተከትሎም በሩሲያ ላይ ከ6 ሺህ በላይ ማዕቀቦች ሲጣልባት ከ400 በላይ ዲፕሎማቶቿ ደግሞ ከተለያዩ ሀገራት ተሰናብተዋል።

ካናዳም የሩሲያ ዲፕሎማቶችን ከማባረሯ ባለፈ በሩሲያ ጋዜጠኞች ፣ ባለሀብቶች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

የሩሲያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ካናዳ ለወሰደችው ማዕቀብ ምላሽ በ62 ካናዳዊያን ላይ ማዕቀብ ጥላለች።

ይህ ማዕቀብ የተጣለባቸው ካናዳዊያን ወደ ሩሲያ እንዳይገቡ እና በሩሲያ ያላቸው ሀብት እንዳይንቀሳቀስ እንደሚደረግ ሮይተርስ ዘግቧል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በሀገሪቱ እንዲሁም በተቋማቶቿ እና ባለሃብቶቿ ላይ ማዕቀብን ጨምሮ የተለያዩ እገዳዎችን የጣሉ እርምጃዎቹን የደገፉ ሀገራትን “ወዳጅ አይደሉም” ማለቷ ይታወሳል።

News today, Politics

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ተባብራ የምትሰራባቸውን ቁልፍ ጉዳዮች ማቋረጧን አስታወቀች

የቻይና የጦር አውሮፕላን
የምስሉ መግለጫ,ቻይና በታይዋን ዙሪያ በባሕር እና በአየር የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ እንደቀጠለ ነው

6 ነሐሴ 2022

የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን በታይዋን ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ቻይና በበርካታ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ጋር ተባባሮ የመሥራት ስምምነቷን ማቋረጧን አሳወቀች።

አሜሪካ እና ቻይና በዓለም የአየር ፀባይ ለውጥ፣ በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ሊያደርጉ የነበረው ውይይት እና የዓለም አቀፍ ወንጀሎችን በመዋጋት በኩል ተባብሮ ለመሥራት ስምምነት ነበራቸው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሴ ግዛቴ በምትላት ታይዋን ይፋዊ ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው ቻይና ከአሜሪካ ጋር ተባብሮ ለመሥራት የነበራትን እቅድ ለመቋረጥ የወሰነችው።

በተጨማሪም ቻይና ሉዓላዊ ግዛቴ ናት በምትላት ታይዋን ላይ ያላትን ይገባኝል በመቃረንም በአፈ ጉባኤ ፔሎሲ እና ቤተሰቦቻቸው ላይ ዕቀባን ጥላለች።

ቻይና እንደተገንጣይ ግዛትዋ የምትመለከታት ታይዋን እራሷን ከቻይና የተለየች ግዛት አድርጋ ትመለከታለች።

ቻይና ውሳኔዋን ያሳወቀችው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ሲሆን፣ በዚህም በአሜሪካ እና በቻይና የመከላከያ ባለሥልጣንት መካከል የሚካሄድ ውይይት ሲሰረዝ፣ ሕገ ወጥ ስደተኞችን የመመለስ ትብብር፣ የአየር ፀባይ ለውጥ፣ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ላይ በጋራ ምርመራ የማድረግ ሥራም እንዲቀቋረጥ ተደርጓል።

ሁለቱ ኃያላን አገራት የዓለም የአየር ፀባይ ለውጥን ለመከላከል በቀጣይ ዓመታት መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ደርሰው ነበር። ባለፈው ዓመት በተደረገው ጉባኤ ላይም ቻይና የበካይ ጋዝ ልቀትን ለመቀነስ ከአሜሪካ ጋር በጋራ ለመስራት ቃል ገብታ ነበር።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው ይህ ውሳኔ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፔሎሲ “የቻይናን ጠንካራ ተቃውሞ ችላ በማለት ባሳዩት ከባድ ምሳሌ” ምክንያት መሆኑን ገልጿል።

ቻይና በአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት የፔሎሲ ጉብኝትን “የከፋ ጠብ አጫሪነት” ነው በማለት ተቃውሞዋን ያሰማች ሲሆን፣ የቻይና የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ በትዊተር ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ ባለፈው ዓመት አሜሪካ ውስጥ በፖሊስ ተንቆ የተገደለውን ጥቁር አሜሪካዊን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

“አሜሪካ የዓለም ፖሊስ እንድትሆንና አገራትን በማስፈራራት እንደ ጆርጅ ፍሎይድ እንድታንቅ አንፈቅድም” ሲሉ ጽፈደዋል።

አርብ ዕለት የዋይት ሐውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ካሪን ጂን-ፔሪ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን የመሄድ “ሙሉ መብት ነበራቸው” በማለት፣ ቻይና የወሰደችውን እርምጃ “ኃላፊነት የጎደለው” ሲሉ ተቃውመውታል።

News today, Politics, social life

ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ


የሩሲያ እና የቱርክ ፕሬዝደንቶች በትናንትናው እለት በሩሲያ ሶቺ ከተማ ተገናኝተው መክረዋል

ሩሲያ እና ቱርክ፤ በሩሲያው ገንዘብ ሩብልስ ለመገበያየት ተስማምተዋል፡፡

የሩሲያ እና ቱርክ መሪዎች በትናንትናው እለት በሩሲያዋ ሶቺ ከተማ ባደረጉት ውይይት የኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት መፈረማቸውን የሩሲያ አርቲ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

ሩሲያ ያለባትን የውጭ ሀገራት እዳ በራሷ ገንዘብ “ሩብል” እንደምትከፍል አስታወቀች
ስምምነቱ መፈረሙን የገለጹት የቱርኩ ፕሬዝደንት ረሲፕ ተይፕ ኤርዶጋን ናቸው፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬንን የማደራደር ሚያ ያላት ቱርክ ከሩሲያ ጋር በሩብልስ ለመገበያየት መስማማቷን ፕሬዘደንት ኤርዶጋን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አርብ ዕለት በቱርክ እና በሩሲያ ልዑካን መካከል የተካሄዱት ስብሰባዎች ፍሬያማ እንደነበሩ እና በሩሲያ በሚያደርጉት ጉብኝት በሶሪያ ስላለው ሁኔታ ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል።

ሩሲያ በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ ሩሲያ አሜሪካን ጨምሮ ከምእራባውያን ጋር ሁሉን አቀፍ ፍጥጫ ውስጥ ገብታለች፡፡

አሜሪካን ጨምሮ ምእራበውያን ሀገራት ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ማእቀብ ሁሉ በሩሲያ ላይ አዝንበዋል፤ ሩሲያ ማእቀቡን ለመመከት ምእራባውያን ሀገራት ጋዝ በሩብል እንዲገዙ አስገድዳለች፡፡

News today, Politics

የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪ ሆቴል ውስጥ ሞተው ተገኙ

የሀገሪቱ መርማሪ ፖሊስ የኦው ያንግ የሞቱበትን ምክንያት በማጣራት ላይ መሆኑ አስታውቋል

የታይዋን መከላከያ ሚኒሰቴር “ኦው ያንግ የታይዋን የሚሳዔል የማምረት አቅምን ለማሳደግ ሲሰሩ የነበሩ ከፍተኛ ባለሙያ ናቸው”ብሏል

የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪና በወታደራዊ ባለቤትነት የተያዘው የናሽናል ቹንግ-ሻን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ምክትል ኃላፊ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ፤ ሆቴል ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን  የታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

እንደ የታይዋኑ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ዘገባ ከሆነ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ሞተው የተገኙው በደቡባዊ ታይዋን በሚገኝ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡

ከቤተሰቦቹ በተገኘ መረጃ መሰረት የ57 አመቱ ኦው ያንግ የሞት ምክንያት የልብ ድካም ሊሆን እንደሚችል ቢገለጽም፤ የሀገሪቱ መርማሪ ፖሊስ ትክክለኛው የሞት ምክንያት ለማወቅ አስፈላጊውን የማጣራት ሂደት ላይ መሆኑ አስታውቋል፡፡

ኦው ያንግ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ የተለያዩ የሚሳዔል ማምረቻ ፕሮጀክቶችን ለመከታተል በሚል ወደ ሃላፊነት የመጡ እንዲሁም ወደ ሃላፊነት ከመጡ ወዲህ የታይዋን የሚሳዔል የማምረት አቅምን ከእጥፍ በላይ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የቆዩ ከፍተኛ ባለሙያ እንደነበሩ የታይዋን መከላከያ ሚኒሰቴር መረጃ ያስረዳል፡፡

ታይና ከቻይና ሊቃጣባት የሚችለውን አደጋ ለመከላከል በሚል ሚሳዔልን በከፍተኛ ሁኔታ በማምረት ላይ ተጠምዳለች፡፡ በዚህ አመት ብቻ የሚሳዔል ማምረት አቅሟን ወደ 500 ለማሳደግ እየሰራች መሆኗም ይገለጻል፡፡

የወቅቱ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ ቻይና እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷ፤ የታይዋን መሪዎች ነገሮች በቅርበት እንዲከታተሉ ያስገደደና ሁኔታ መፈጠሩ የሚታወቅ ነው፡፡

በዚህም አሁን ላይ የናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት ተከትሎ ቻይና በምታደርገው የአየር ላይ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በሩቅ ምስራቅ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰ ሲሆን ታይዋን ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ እንዳወጀች ነው፡፡

የታይዋን ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን ሀገራቸው ማንንም እንደማትተነኩስና ነገርግን ራሷን እንደምትከላከል መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለታይዋን ብቻ ሳይሆን ለመላው አለም ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲም ነበር የተናገሩት ፕሬዝዳንቷ፡፡

News today, Politics, social life

በእስራኤል ጥቃት አንድ የታጣቂ ቡድን መሪን ጨምሮ አስር ሰዎች ተገደሉ


እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት አንድ የፍልስጤም ታጣቂዎች ቡድን መሪን እና አንዲት ህጻንን ጨምሮ 11 ሰዎች መገደላቸውን ሪፖርቶች አመለከቱ።

ይህን የእስራኤል ጥቃት ተከትሎ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ሮኬቶች ከጋዛ ወደ እስራኤል የተተኮሱ ሲሆን፣ በዚህም ሳቢያ በአካባቢው ከባድ ውጥረት ነግሷል።

ይህንንም ተከትሎ እስራኤል በወረራ በያዘችው የዌስት ባንክ አካባቢ ባደረገችው አሰሳ 19 የኢስላሚክ ጂሃድ ቡድን አባላት ናቸው የተባሉ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሏ ተገልጿል።

በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት 11 ሰዎች መካከል ታይሰር ጃባሪ የተባለ የታጣቂዎች መሪ ይገኝበታል።

የአየር ጥቃቱ ግለሰቡ የሚመራው የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ የተባለው ቡድን “ጥቃት ሊሰነዝር” መሆኑን ተከትሎ የተወሰደ እርምጃ ነው ስትል እስራኤል ምክንያቷን አሳውቃለች።

ከተገደሉት መካከል የአምስት ዓመት ታዳጊ የምትገኝበት ሲሆን፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸው የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት ተናግረዋል።

የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ የተባለው ቡድን ለእሰራኤል ጥቃት “የመጀመሪያ ምልሽ” ባለው አጸፋ ከ100 በላይ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ሌሊቱን ተኩሷል።

ከተተኮሱት ሮኬቶች አብዛኞቹ በእስራኤል የሚሳኤል መከላከያ አማካይነት መክሰማቸው የተነገረ ሲሆን፣ በበርካታ የእስራኤል ከተሞች ውስጥ ሌሊቱን በሙሉ የጥቃት ማስጠንቀቂያ ደውሎች ሲሰሙ አድረዋል።
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር እስከ ቅዳሜ ንጋት ድረስ የዘለቁ የሮኬት ጥቃቶችን ጋዛ ውስጥ በሚገኙ በርካታ የታጣቂዎቹ ይዞታዎች ላይ ሲፈጽም ማደሩን ኣሰውቋል።

ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ተመሳሳይ ግጭት ተከስቶ ከ200 በላይ ፍልስጤማዊያን እና በርካታ እስራኤላውያን ከተገደሉ በኋላ በግብፅ አደራዳሪነት የተኩስ አቁም መደረሱ ይታወሳል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ያይር ላፒድ ሠራዊታቸው ለአገራቸው ስጋት በሆኑ ኢላማዎች ላይ ፈጣን ፀረ ሽብር ጥቃት መፈጸሙን የገለጹ ሲሆን፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ደግሞ ግጭቱ የተራዘመ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን አመልክተዋል።

ጋዛ ውስጥ በእስላማዊ ቡድን ኢላማዎች ላይ ነው የተፈጸመው በተባለው ጥቃት “15 የሚሆኑ ታጣቂዎች” መገደላቸውን የእስራኤል ሠራዊት ቃል አቀባይ መናገራቸው ተዘግቧል።

የጋዛ የጤና ባለሥልጣንት ግን ታይሲር ጃባሪን ጨምሮ አራት የእስላማዊ ቡድኑ ታጣቂዎች በእስራኤል ጥቃት መገደላቸውን አረጋግጠዋል።

የእስራኤል የመከላከያ ኃይል ታይሲር ጃባሪ የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን “ከፍተኛ መሪ” መሆኑን እና “በርካታ የሽብር ጥቃቶችን” በእስራኤላውያን ሰላማዊ ሰዎች ላይ ፈጽሟል ሲል ይከሰዋል።

የጋዛ ባለሥልጣናት እንዳሳወቁት በጥቃቱ ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ 79 ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው መናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል።

የፍልስጥኤም እስላማዊ ጂሃድ ቡድን ዋና ፀሐፊ ዚያድ አል-ናኻላ ወደ ኢራን በጉዞ ላይ ሳሉ “ለተፈጸመው ጥቃት በሙሉ ኃይላችን ምላሽ እንሰጣለን፣ በአሸናፊነት የምንወጣበት ጦርነት ይሆናል። የማይነካ ቦታ አይኖርም፣ ቴል አቪቭ በሮኬቶቻችን ጥቃት ስር ትሆናለች” ማለታቸው ተዘግቧል።

የጋዛ ሰርጥን የሚያስተዳድረው ሐማስ የፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች ዝም እንደማይሉና በሚካሄደው ዘመቻ ውስጥ በአንድነት እንደሚቆሙ ገልጿል።

News today, Politics

ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቅ ለመፍታት ከመንግስት ጋር ተስማሙ


ታጣቂዎቹ ላለፉት 40 ገደማ ዓመታት ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ ነበር
በሀገሪቱ መንግስት እና በታጣቂዎቹ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል

የሴኔጋል መንግስት እና ደቡባዊ ሴኔጋልን ለመገንጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች እርቅ አወረዱ።

በሴዛር አቶቴ ባዲያቴ የሚመራው የካሳማንቼ ኃይሎች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (MDFC) ላለፉት 40 ገደማ ዓመታት ነፍጥ አንግቦ በደቡባዊ ሴኔጋል ሲንቀሳቀስ ነበር።

ሆኖም አሁን ትጥቅ አውርዶ ሰላማዊ ትግል ለማድረግ መስማማቱን አስታውቋል።

ስምምነቱን በፀጋ የተቀበሉት ፕሬዝዳንት ማኪ ሳልም ከሴዛር አቶቴ ጋር ከትናንት በተስቲያ ሐሙስ ተፈራርመዋል እንደ ሲጂቲኤን ዘገባ።

ማኪ ሳል የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ናቸው።

ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እንደሚያስችል ተስፋ የተጣለበት የሰላም ስምምነት በጊኒ ቢሳው ነው የተፈረመው።

ስምምነቱ በሸምጋዮች ጥረት እውን የሆነ ሲሆን፤ ማኪ ሳል አማጺ ቡድኑን ከመንግስታቸው ጋር ለማሸማገል ላደረጉት ጥረት የጊኒ ቢሳውን ፕሬዝዳንት ዑማሮ ሲሶኮ ኢምባሎን አመስግነዋል።

የካሳማንቼ ኃይሎች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (MDFC) ነፍጥ አንግበው ለረጅም ዓመታት ከተንቀሳቀሱ የአፍሪካ አማፂ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው።

News today, Politics

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ቤጂንግ ለናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት በዚህ ደረጃ ምላሽ የመትሰጥበት “ምንም ምክንያት የለም” አሉ

ብሊንከን፤ ቻይና ታይዋንን በመክበብ የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ “ውጥረትን የሚያባብስ” ነው ሲሉ ኮንነዋል

2022/8/5 16:12 GMT

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን

በፔሎሲ ጉብኝት የተበሳጨችው ቻይና “ከአሜሪካ ጋር ስታደረግ የነበረው ወታደራዊ ማቋረጧን” ይፋ እስከማድረግ ደርሳለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ቻይና ታይዋንን በመክበብ የምታካሂደው ወታደራዊ ልምምድ ‘ያለው ውጥረት የሚያባብስ’ ነው ሲሉ ኮነኑ።

ብሊንከን የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ላደረጉት ጉብኝት ምላሽ ለመስጠት በሚል ቤጂንግ ለጀመረችው ወታደራዊ ልምምድ የምታቀርበው “ምንም ምክንያት የለም” ማለታቸውም ኤፒ ዘግቧል።

ቻይና ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ተዋጊ ጄቶች እና የጦር መርከቦች በታይዋን ዙሪያ ማሰማራቷን ተከትሎ በዓለም ላይ እጅጉን የመርከብ መስመሮች የሚበዙበት ቀጠና አደጋ እንዳንዣበበበት እየተገለፀ ነው።

ከደቡብ ምስራቅ እስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ለመወያየት በበካምቦድያ መዲና ፕኖም ፔን የሚገኙት ብሊንከን ጉዳዩን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ “የቻይና ድርጊቶች ያለውን ውጥረት ትርጉም ባለው ደረጃ የሚያባብሱ ናቸው” ሲሉ ተደምጠዋል።

በቅርቡ በኢንዶኔዥያ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ዋንግ ዪን፤ በ25 ዓመታት ውስጥ ታይዋንን የጎበኙ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ፒሎሲ ወደ ደሴቲቱ ሊጓዙ እንደሚችሉ ነገሬው ነበር ያሉት ብሊንከን፤ የቻይና ድርጊት ከጠበቅነው ውጭ ባይሆንም የተጋነነ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

“እውነታው ግን የአፈ ጉባኤዋ ጉብኝት ሰላማዊ ነበር፤ እንደዚህ አይነት የተጋነነ እና ተመጣጣኝ ያልሆነ ወታደራዊ ምላሽ የሚያሰጥበት ምንም ምክንያት የለም” ሲሉም አክለዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ብሊንከን ይህን ይበሉ እንጂ፤ ናን ፔሎሲ ቻይና እንደ አንድ ግዛቷ አድርጋ በምትቆጥራት ታይዋን ላይ ያደረጉት ጉብኝት የቤጂንግ ሰዎች ኩፉኛ ማስቆጣቱ እየተገለጸ ነው።

በአሜሪካ ድርጊት እጅጉን የተበሳጨችው ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን ማቋረጧን ከሰዓታት በፊት አስታውቃለች።

ቻይና በውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ በኩል በሰጠቸው መግለጫ፤ ቤጂንግ እስካሁን ከከፍተኛ ወታደራዊ ትብብሮች ባለፈ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ከዚህ በፊት የነበራትን የከፍተኛ መሪዎች የጋራ ውይይት መድረኮችን ከአሜሪካ ጋር በትብብር ላለመስራት ወስናለች።

እንዲሁም ቻይና ከአሜሪካ ጋር የነበራትን የድንበር አልባ ወንጀል መከላከል፣ ስደተኞችን ማጓጓዝ፣ አደገኛ እጽ ዝውውር መከላከል እና ሌሎች ስምንት የትብብር መስኮችን አቋርጣለች።

ቻይና ሰሞኑን ታይዋንን በጎበኙት የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ላይ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።

News today, Politics

ኢትዮጵያ የ“አንድ ቻይና” ፖሊሲን እደግፋለሁ አለች

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህ የኢትዮጵያ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ብሏል

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም

የናንሲ ፔሎሲን ጉዞ ተከትሎ በቻይና-ታይዋን ጉዳይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱ ይታወቃል

ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የ”አንድ ቻይና” ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ከወቅታዊ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የሚከሰቱ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ያሳስቧታል ብለዋል።

ሰሞኑን በቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑንም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ የ“አንድ ቻይና” ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት አምባሳደር መለስ፥ “ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው” ብለዋል።

አሁንም ኢትዮጵያ ለ“አንድ ቻይና” ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉም ሲሆን፥ ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረትም እንደሚያራምዱት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን የሚያጠናክር ውጤታማ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው አምባሳደር መለስ ያነሱት።

የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የተመሰረተበትን 95ኛ ዓመት ክብረ በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የቻይና የመከላከያ ሰራዊት የሀገሩን ሉዓላዊነት፣ ጸጥታና ጥቅም ከማስከበር አልፎ ለዓለማችን ሰላምና መረጋጋት እያደረገ ላለው በጎ ሚና ያላቸውን አድናቆት መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲን የቻይናን ዛቻ ወደ ጎን በመተው ወደ ታይዋን መጓዛቸውን ተከትሎ በቻይና-ታይዋን ጉዳይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱ ይታወቃል።

ቻይና አሜሪካ በዴሞክራሲ ሽፋን ሉአላዊነቴን ተዳፍራለች ያለች ሲሆን፤ ቻይናን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ ማለቷ አይዘነጋም።

የቻይና ጦር የፔሎሲን ጉብኝት ተከትሎ የአጸፋ እርጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ በትናንትናው እለትም 27 የቻይና የጦር ጄቶች የታይዋንን የአየር ክልል ጥሰው ገብተዋል።

ሩሲያ፣ ሰሜን ከሮያ እና ኤርትራ ቻይናን በመደገፍ አቋማቸውን ያንፀባረቁ ሲሆን፤ ኤርትራ የፔሎሲን ጉብኝት ህግን የጣሰ ነው ስትልም ተችታለች።

News today, Politics

ሙሴቪኒ ከአሜሪካዋ ዲፕሎማት ጉብኝት አስቀድመው ‘ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም’ አሉ

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ
የምስሉ መግለጫ,ዬዌሪ ሙሴቪኒ

ከ 6 ሰአት በፊት

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር የኡጋንዳ ጉብኝትን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም ሲሉ ለቢቢሲ ተናገሩ።

አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸው ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 28/2014 ዓ.ም. ከኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አምባሳደሯ ከዋሽንግተን ዲሲ መመሪያዎችን ይዘው ይመጡ እንደሆነ የተጠየቁት ሙሴቬኒ፤ “ማንም ትዕዛዝ አይሰጠንም” ሲሉ መልሰዋል።

ሙሴቬኒ አገራቸው ኡጋንዳ ከምዕራባውያን የሚላከውን እርዳታ በመልካም ጎኑ እንደምትመለከተው ጠቅሰው፤ አገራቸው ያለ እርዳታ መኖር እንደምትችልም ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ ኡጋንዳ በሩሲያ እና በዩክሬን ጦርነት ዙሪያ የያዘችውን አቋም ለማስቀየር የተደረገ ጥረት እንደሌለ ገልጸዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ወረራ እንድታቆም ያወጣውን ምክር ሃሳብ በድምጸ ታዕቅቦ ካለፉት 16 የአፍሪካ አገራት መካከል ኡጋንዳ አንዷ መሆኗ ይታወቃል።

አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪን ፊልድ ወደ ካምፓል የሚያመሩት የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኡጋንዳ ጉብኝት ካደረጉ ከቀናት በኋላ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ በቅርቡ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ በአራት የአፍሪካ አገራት ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል።

ሙሴቬኒ፤ “ጥሩ ጓደኛ” ሲሉ የገለጿቸው አምባሳደር ቶማስ-ግሪንፊልድን ሁሌም ወደ ኡጋንዳ እንዲመጡ በራችን ከፍት ነው ካሉ በኋላ፤ አስተዳደራቸው ለምዕራባውያን ጫና እንደማይበረከክ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ በሩሲያ እና በዩክሬን ጦርነት ዙሪያ አቋማቸው ምን እንደሆነ ሲጠየቁ፤ ጦርነቱን ከ1962ቱ የኩባ ሚሳኤል ቀውስ ጋር አነጻጸረውታል።

ሙሴቪኒ ዛሬ ላይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) በሩሲያ ዙሪያ መገኘትን ሶቪየት ሕብረት አሜሪካ አፍንጫ ስር ኩባ ውስጥ ሚሳኤል ከመትከሏ ጋር አነጻጽረውታል።

የኩባ ሚሳኤል ቀውስ ተብሎ የሚታወቀው ክስተት የወቅቱ የዓለማችን ኃያላንን ወደ ኒውክሌር ጦርነት እንዲገቡ ከጫፍ አድርሶ ነበር።

በወቅቱ ሶቪየት ሕብርት የኩባን ደኅንነት ከአሜሪካ ጥቃት ለመጠበቅ በሚል፣ ኩባ ውስጥ የአሜሪካ ከተሞችን መምታት በሚያሰችሉ ስፍራዎች ላይ የኒውክሌር አረሮችን ማስወንጨፍ የሚችሉ ሚሳኤሎችን ተክላ ነበር።

ሙሴቬኒ ይህ ክስተት የአሜሪካንን የደኅንነት ስጋት ውስጥ ከትቶ እንደነበረ ተናግረው፤ በወቅቱ አገራቸው ለአሜሪካ ድጋፏን መሽጠቷን አስታውሰዋል።

ሙሴቬኒ ዛሬም ተመሳሳይ መርኅ ማረመድ አለብን ብለዋል።

ሙሴቬኒ ኔቶ በሩሲያ ዙሪያ መክተሙ፤ የሩሲያን እርምጃ እንዲገነዘቡ ያደርግዎታል ወይ ተብለው ሲጠይቁ፤ “በትክክል” ሲሉ መልሰዋል።

“ታሪክ የምትሉትን፤ እኔ ወቅታዊ ጉዳይ እለዋለሁ” ብለዋል ሙሴቬኒ።

News today, Politics

እኛ አንተነኩስም፤ ነገርግን ራሳችንን እንከላከላለን”- የታይዋን ፕሬዝደንት

በፔሎሲ ጉብኝት የተቆጣችው ቻይና በታይዋን ዙሪያ ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች ነው

ከዓለም ዙሪያ

 2022/8/4 15:12 GMT

የታይዋን ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን

በታይዋን ዙረያ ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች ያለችው ቻይና ወደ ታይዋን ሚሳየል አስወንጭፋለች

የታይዋን ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን ሀገራቸው ማንንም እንደማትተነኩስና እና ነገርግን ራሷን እንደምትከላከል ተናግረዋል፡፡

የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለታይዋን ብቻ ሳይሆን ለመላው አለም ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

 “የሀገራችንን ሰላም እና መረጋጋት ለመጠበቅ እራሳችንን እንሰጣለን” ያሉት ፕሬዝዳንቷ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ፍትሃዊ ያልሆኑ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለማስቆም እንዲተባበር ጠይቃለች።

እናም የታይዋን ፕሬዝዳንት በመቀጠል “የፀጥታው ሁኔታ እንዳይባባስ ከአጋሮቻችን ጋር እየተገናኘን ነው” ብለዋል።

ቻይና በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በእኛ ላይ የምታደርገውን የመረጃ ጦርነት አጠናክራ ስለምትቀጥል የታይዋን ህዝብ በንቃት እንዲጠብቅ አሳስባለች።

 ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን “የፀጥታው ሁኔታ እንዳይባባስ ከአጋሮቻችን እየተነጋገርን ነው” ብለዋል፡፡

በአሜሪካዋ አፈጉባኤ ጉብኝት የታይዋን ጉብኝት የተበሳጨችው ቻይና በዛሬ እለት ጠዋት የባለስቲክ ሚሳየሎችን ወደ ታይዋን አስወንጭፋለች፡፡ የጃፓን መከላከያ ሚኒስትር አምስት የሚሆኑ የቻይና ሚሳየሎች በታይዋን ደሴት ላይ አልፈው በጃፓን በየኢኮኖሚ ዞን ማረፋቸውን ጠቅሷል፡፡

ሚኒስቴር በጃፓን ልዩ በሆነው የኢኮኖሚ ቀጠና ውስጥ የወደቁ ከሚመስሉት አምስት የቻይና ባሊስቲክ ሚሳኤሎች አራቱ “በዋናዋ የታይዋን ደሴት ላይ” መብረራቸው ጠቁሟል።

በፔሎሲ ጉብኝት የተቆጣችው ቻይና በታይዋን ዙሪያ ወታደራዊ ልምምድ እያደረገች ነው፡፡

አለምአቀፉ ማህበረሰብ የቻይናን ድርጊት እንዲያስቆም እየጠየቀች ያለችው ታይዋን፣ ቻይና ገፍታ ጦርነት የምትከፍት ከሆነ ግን ራሷን ለመከላከል እንደምትገደድ ገልጻለች፡፡

News today, Politics

ሩሲያ ባለፉት ቀናት ውስጥ 500 የዩክሬን ወታደሮችን ገደልኩ አለች

ከምዕራባዊያን ለዩክሬን የተለገሱ በርካታ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟንም ሩሲያ አክላለች

ሩሲያ በሞስኮ የኖርቄይ ዲፕሎማትንም ማባረሯን አስታውቃለች

ሩሲያ ባለፉት ቀናት ውስጥ 500 የዩክሬን ወታደሮችን ገደልኩ አለች፡፡

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ስድስት ወራት 162ኛ ቀኑ ላይ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን ጦርነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ዓለም አቀፋዊ ሆኗል።

የሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ ባለፉት ቀናት በተካሄደው ጦርነት 500 የዩክሬን ወታደሮች መግደሉን አስታውቋል።ሚኒስቴሩ አክሎም ከአሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባውያን ሀገራት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን አውድሜያለሁም ብሏል።

የሩሲያ ጦር በዶንቴስክ እና ካርኪቭ አካባቢዎች ባካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ በርካታ የዩክሬን እና ቅጥረኛ ወታደሮች ይዞታዎችን እና የጦር ማዘዣዎችን ማውደሙንም አስታውቋል።

እንዲሁም ከረጅም እና አጭር ርቀት ሚሳኤል መሳሪያዎች፣ የጦር ተሽከርካሪዎች፣ መጋዝኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ ስፍራዎችን የሩሲያ አየር ሀይል መምታቱን አርቲ ዘግቧል።

የሩሲያ ጦር 390 የዩክሬን የጦር አውሮፕላኖች ፣ 1506 ድሮኖች፣ 354 ጸረ አውሮፕላን ሚሲኤሎች እና ከ 11 ሺህ በላይ የጦር ታንኮች፣ ልዩ የጦር ተሽከርካሪዎች፣ ጸረ ሮኬት መሳሪያዎች እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎች ማውደሙን ዘገባው አክሏል።

የዩክሬን መንግስት በሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር መግለጫ ዙሪያ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም።

በተያያዘ ዜና ሩሲያ ከሰሞኑ አንድ የኖርዌይ ዲፕሎማት በአንድ መዝናኛ ስፍራ ገብታ በተናገረችው ጸረ ሩሲያ ንግግር ምክንያት ሞስኮን ለቃ እንድትወጣ መወሰኗን አስታውቃለች።

News today, Politics

ኤርትራ፤ የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ዓለም አቀፍ ሕግ “የጣሰ ነው” አለች

ኤርትራ፤ የፔሎሲን ጉብኝት ያወገዘች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ናት

የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ (ፎቶ ከፋይል)

አስመራ፤ የአፈጉባኤዋ ጉዞ የአንድ ቻይና ፖሊሲን የሚቃነረን፤ የቻይናንም አንድነት የሚጻረረ ነው ብላች

ኤርትራ፤ የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባዔ የታይዋን ጉብኝት ዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ መሆኑን ገለጸች።

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፔሎሲን የታይዋን ጉብኝት አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። መስሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ፖሊሲ የማይረባና በግልጽ የወጣ መሆኑን ጠቅሷል።

ዋሸንግተን ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች መሆኑን የገለጸችው አስመራ ይህ ድርጊት አጸያፊ ነው ብላለች።

ኤርትራ የፔሎሲ ጉብኝት ወደ ግጭት የሚያመራና የሚያባብስ እንደሆነም ነው የገለጸችው።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ግደለሽነትን የሚያመለክት እንደሆነ ነው የገለጸችው።

አሜሪካ ባለፉት ዓመታት በእስያ የማሳመን ስራ ስትሰራ የቆየችው ይህንን ታይዋንን ጉዳይ ለማሳካት እንደሆነም ነው ኤርትራ ያስታወቀችው።

የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነውም ብሏል የኤርትራ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት።

የአፈጉባኤዋ ጉዞ ድርጊቱ ፤የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም “የአንድ-ቻይና” ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነውም ብሏል የኤርትራ መንግስት።

ኤርትራ፤ የፔሎሲን የታይዋን ጉብኝት ያወገዘች ብቸኛ የአፍሪካ ሀገር ናት።

ሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያ ጉብኝቱን ማውገዛቸው ይታወሳል።

News today, Politics

ሶማሊያ የአልሸባብ የቀድሞ ሁለተኛ ቁልፍ ሰውን በሚኒስትርነት ሾመች


የሶማሊያ መንግስት የአልሸባብ መስራች ሙክታር ሮቦ አሊን (አቡ መንሱር) ሚኒስትር አደርጎ ሾሟል
አቡ መንሱር የአልሸባብ የሽበር ቡድን መስራችና በምክትልነት የመራ ሰው ነበረ

አዲሱ የሶማሊያ መንግስት በርካቶችን ያስገረመ አዲስ ከቢኔ ከሰሞኑ ይፋ አድርጓል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ቤሪ የተመራው አዲሱ የሶማሊያ መንግሰት የአልሸባብ የሽብር ቡድን ሁለተኛ ቁልፍ ሰውን በሚኒስትርነት በመሾሙ ነው በርካቶችን ያስገረመው።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ “ከአልሻባብ ጋር እንደራደራለን” አሉ
በትናትናው እለት በሚቃዲሾ በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ልምድ እና ብቃት አላቸው ያላቸውን ሚኒስትሮቻቸውን አስተዋውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ፤ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ “ሶማሊያውያን ከአለም ጋር ስምምነት ላይ ናቸው” በሚለው መርህ ላይ ለመስራት ቃል ገብተዋል።

ከዚህ ሁሉ ግን በርከቶችን ያስገረመው ጉዳይ በቅጽል ስሙ “አቡ መንሱር” በመባል የሚጠራው የአልሸባብ የሽብር ቡድን መስራች እና የቡድኑ ሁለተኛ ቁልፍ ሰው ሙክታር ሮቦ አሊ ሹመት ነበር።

ሙክታር ሮቦ አሊ (አቡ መንሱር) በአዲሱ የሶማሊየ መንግስት ካቢኔ ውስጥ የኃይማኖት ጉዳዮች እና የኢንዶውምንት ሚኒስትር ተደርገው መሾማቸውም ተነግሯል።

ሙክታር ሮቦ አሊ አልሸባብን ለቆ እስከወጣበት የፈረንጆቹ 2011 ድረስ የሽበር ቡድኑ ምክትል መሪ የነበረ ሲሆን፤ የሽብር ቡድኑ ይፋዊ ቃል አቀባይም ነበር።

በፈነረንጆቹ 2017 ላይ እጁን ለሶማሊያ መንግስት የሰጠው አቡ መንሱር፤ በወቅቱ በሰጠው መግለጫ ከቡድኑ ጋር የተለያየው ከ5 ዓመት በፊት እንደነበረ ገልጾ ነበር።

ሶስት የአልሸባብ ቡድን አመራሮችን መግደሉን የኢትዮጵያ መከላከያ አስታወቀ
በፈረንጆቹ 2018 ላይ ደግሞ የደቡብ ምእራብ ሶማሊያን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ተወዳድሮ እንደነበረም ይታወሳል።

አዲሱ ሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ቤሪ በቴሌቭዥን በሰጡት አስተያየት፤ አልሸባብን ከመልቀቁ በፊት ለጠቆመው ሰው 5 ሚሊየን ዶላር ሽልማት ተዘጋጅቶበት የነበረው ሰው አሁን ላይ የሶማሊያ ኃይማኖታዊ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኗል ብለዋል።

News today, Politics

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

ሩሲያ፤ ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍም ገልጻለች

ሩሲያ፤ ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍም ገልጻለች።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለውን ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች።

የሩሲያ ቤተ መንግስት (ክሬምሊን) ቃል አቀባይ፤ ዲሚትሪ ፒስኮቭ ሀገራቸው ከዩክሬን ጋር ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ፒስኮቭ ከሰሞኑ በእስያ ፓስፊክ ባለው ውጥረት ዙሪያም አስተያየት መስጠታቸውን ሩሲያ ቱዴይ ዘጎቧል። ቃል አቀባዩ የእስያ ፓስፊክ ውጥረት ቀላል ግምት ሊሰጠው አይገባም ሲሉም ነው አስተያየት የሰጡት።

የአሜሪካ ምክርቤት አፈጉባዔ በታይዋን ያደረጉት ጉብኝት እንደቀላል መታየት እንደሌለበት ያነሱት ፒስኮቭ ጉዳዩ ከባድ እንደሆነ ገልጸዋል።

የፔሎሲን የቻይና ጉብኝት ተከትሎ የሶስተኛው የዓለም ጦርነት ይነሳል የሚል ፍርሃትን እንዳለ የገለጹት ቃል አቀባዩ፤ ይህ ግን እንደማይከሰት ተናግረዋል።

ፒስኮቭ፤ ሀገራቸው ቻይናን ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምትወስዳቸውን “ሚዛናዊ” እርምጃዎች እንደምትደግፍ ተናግረዋል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያለባትን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነችም ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

ሩሲያ እና ዩክሬን የጀመሩት ጦርነት አራት ወራት አልፈውታል።

ምዕራባውያን ሩሲያ፤ ዩክሬይንን፤ ቻይና ደግሞ ታይዋንን ትወራለች የሚል ፍርሃት አላቸው።

News today, Technology

አል ዛዋሂሪን የገደሉት እጅግ ዘመናዊና ሚስጥራዊ የአሜሪካ ሚሳኤሎች

እጅግ ዘመናዊ የተባሉት ሚሳኤሎቹ በፕሬዝዳንት ኦባማ ዘመን የተሰሩ ናቸው

 2022/8/2 17:14 GMT

ሚሳዔል አስወንጫፊ የአሜሪካ ድሮን

የአሜሪካ ሚሳኤሎች አልዘዋሪሂን ያለ አንዳች የጎላ የፍንዳታ ድምፅ የገደሉት

መነጋገሪያ ከሆኑ ሰሞነኛ ቀዳሚ የሚዲያ ጉዳዮች መካከል አንዱና ቀዳሚው የአልቃይዳው መሪ አል ዛዋሂሪ መገደል ነው።

የቀድሞው የሽብር ቡድኑ መሪ ኦሳማ ቢን ላደን የቅርብ ሰውና አማካሪ አልዛዋሂሪ በቢላደን እግር ተተክቶ ቡድኑን መምራት ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ሆኖም ላለፉት 20 ገደማ ዓመታት ልክ እን ቢላደን ሁሉ አልዛዋሪን ስታድን የነበረችው አሜሪካ መግደሏን ትናንት ሰኞ አስታውቃለች።

አልዛዋሂሪ በአፍጋኒስታን መገደሉን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ይፋ አድርገዋል።

ሆኖም የ71 ዓመቱ ግብጻዊ ቀዶ ጠጋኝ ሐኪም አገዳደል አሁንም ብዙዎችን እንዳስደመመ ነው። አልዛዋሂሪ ያለ አንዳች ከባድ ፍንዳታ እና የከፋ ጉዳት እንደተገደለ መነገሩም ብዙዎችን ለግርምት ዳርጓል።

ከሞቱ አሟሟቱ እንዲሉም በሁኔታው የተገረሙ ብዙዎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃኑን ጨምሮ ስለሁኔታው እየጠየቁ ነው።

ቁንጮው የሽብር ቡድን መሪ እንዴትና በምን ተገደለ የሚሉ መጣጥፎችን በማስነበብም ላይ ይገኛሉ።

ሰው አልባዎቹን (ድሮን) ጨምሮ ሌሎችም የጦር አውሮፕላኖች ዒላማቸውን የሚያደባዩት እንደ ነጎድጓድ በሚያስገመግም ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፅ ታጅበው ነው የሚለው ዘ ናሽናል አልዛዋሪን የተገደለበት ሚሳኤል ግን ድምፅ አልባ እና ዒላማውን ብቻ ነጥሎ የመታ ነው የሚል ሰፊ ሃተታን ይዞ ወጥቷል።

አልዛዋሪ በመኖሪያ ቤቱ በረንዳ ላይ ሳለ የተገደለበት ሚሳኤል ምንነቱ በውል ባይገለጽም አዲስና የተለየ ነው ሲል የሚያትተው ዘ ናሽናል የጦር ተንታኞች መሳሪያው ምናልባትም ‘በራሪው ጊንሱ’ ወይም

‘R9X Hellfire’ በሚል ከሚታወቁ እጅግ ዘመናዊ የአሜሪካ የሚሳኤል ጦር መሳሪያዎች መካከል አንዱ ሳይሆን እንዳልቀረ መናገራቸውን አስቀምጧል።

መሳሪያው ‘ኒንጃ ሄልፋየር’ የሚል ቅጽል መጠሪያ እንዳለውሞ ነው ሃተታው የሚጠቁመው።

የጦር መሳሪያው ምንነት

‘በራሪው ጊንሱ’ በሚል ይጠራሎል የተባለለት እጅግ ዘመናዊው የሚሳኤል ጦር መሳሪያ ግለሰቦችንና የተለዩ ዓላማዎችን ነጥሎ ለመምታት በማሰብ የተሰራ ነው።

ዒላማውን ነጥሎ ለመምታት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ይነገራል። በመኪና ውስጥ ከሚጓዙ ሰዎች እንኳን አንዱን ብቻ ነጥሎ ለመምታት ያስችላልም ነው የሚባለው።

ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ሌሎች የሚሳኤል ዝርያዎች ቢኖሩም ይኼንኛው ግን የተለየ ስለመሆኑ ይነገርለታል።

መሳሪያው ወደ መሬት ተምዘግዝጎ ዒላማውን የሚመታና 45 ኪሎ ግራም የሚመዝን አረርን እንደሚሸከምም ነው አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን ለዎል ስትሪት ጆርናል የተናገሩት።

ሆኖም አሜሪካ ስለ በራሪው ስለሚባለው ጦር መሳሪያ አንዳችንም ነገር አላለችም። ስለ አሰራሩና ስለ ስሪቱ የተባለ ነገርም የለም።

አልዛዋሪን በመግደሉ ውጥን ንጹሃንን ከጉዳት ለመታደግ የሚያስችል ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረጉን ግን አልሸሸገችም።

ባሳለፍነው ነሐሴ በፈጸመችው ተመሳሳይ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 10 ገደማ ንጹሐን መገደላቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችትንና ውግዘትን ማስተናገዷ ይታወሳል።

በመሆኑም ይህን ተከትሎ አልዛዋሪን ለመግደል ለግለሰባዊ ዒላማዎች በሚል በፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ዘመን እንደተሰራ የተነገረለትን ‘በራሪው ጊንሱ’ን መጠቀሟ ተነግሯል።

የቀድሞው የአል ቃይዳ መሪ ቢን ላደን በፕሬዝዳንት ኦባማ ትዕዛዝ በፈረንጆቹ 2011 በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉ ይታወሳል።

News today, Politics

አይመን አል ዘዋሂሪን ማን ሊተካ ይችላል?

አሜሪካ የአልቃይዳ መሪ አይመን አል ዘዋሂሪ መግደሏን አስታውቃለች

 2022/8/2 7:43 GMT

አይመን አልዘዋሪን ሊተካ ይችላል የተባለው ግብጻዊ ሰይፍ አል ማስሪ

ትውልደ ግብፃዊው አይመን አል ዘዋሂሪ፤ ኦሳማ ቢላደንን በመተካት አል ቃይዳን ሲመራ ነበር

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአልቃይዳ መሪ አይማን አል ዘዋሂሪን እንደተገደለ መናገራቸው ይታወሳል።

 የሽብር ቡድኑ መሪ፤ የአሜሪካ የስለላ ተቋም (ሲአይ ኤ) በፈጸመው የድሮን ተልዕኮ መገደሉን ጆ ባይደን አረጋግጠዋል።

የቀድሞውን መሪ ኦሳማ ቢላደንን በመተካት አል ቃይዳን ሲመራ የነበረው ትውልደ ግብፃዊው አይመን ዘዋሂሪን የተገደለው በአፍጋኒስታን ካቡል መሆኑንም ጆ ባይደን ተናግረዋል።

አይማን አል ዘዋሂሪን የተገደለው የሽብር ቡድኑን ቁልፍ መሪዎችን ኢላማ በማድረግ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት እንደሆነም ተገልጿል።

የአል ዘዋሂሪን መገደልን ተከትሎ በቀጣይ የሽብር ቡድኑን ማን ይችላል በሚል የተለያዩ መላምቶች በመነሳት ላይ ናቸው።

አሁን ላይ እየወጡ ባሉ መረጃዎች ሌላኛው ግብጻዊ ሰይፍ አል ማስሪ ሊተካ እንደሚችል ግምቶች በመውጣት ላይ ናቸው።

ይህ ግብጻዊ በኢራን በረሀማ ስፍራዎች ውስጥ ተሸሽጎ እንዳለ የሚገመት ሲሆን ሟቹ የአልቃይዳ መሪ አይመን አልዘዋሪን ሊተካ ይችላል ተብሏል።

ሰይፍ አል ማስሪ ላለፉት 30 ዓመታት በአልቃይዳ የሽብር ቡድን ውስጥ የተለያዩ ተልዕኮዎችን ሲመራ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የሽብር ቡድኑን ከዚህ በፊት ኦሳማ ቦንላደን በነበሩበት ጊዜ ወደ ነበረበት ቁመና ሊመልሰው እንደሚችል ተሰግቷል።

አልማስሪ በፈረንጆቹ 1998 ናይሮቢ በሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ ላይ የተፈጸመውን እና ለ224 ሰዎች ህይወት ማለፍ ምክንያት የሆነውን የሽብር ድርጊት በመምራት ይፈለጋል።

አሜሪካ ይሄን የሽብር ቡድን መሪ ለያዘ ፣ለገደለ ወይም ለጠቆመ ግለሰብ 7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር እንደምትከፍል ይፋ አድርጋለች።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት፤ አል ቃይዳ መሪ መገደሉ፤ የቱንም ያህል ጊዜ ቢወስድም በመስከረም 11 ጥቃት የተጎዱት ዜጎች ፍትህ ማግኘታቸውን ያመለክታል ብለዋል።

ባይደን፤ የቡድኑ መሪ አይማን አል ዘዋሪ እንዲደመሰስ ላደረጉ የሀገራቸው የጸጥታ ኃይሎች ምስጋና አቅርበዋል።

ባይደን በካቡል በተደረገው ጥቃት ንጹኃን ኢላማ እንዳልተደረጉ ቢገልጹም ታሊባን ግን አጣጥሎታል።

በአፍጋኒስታን የተደረገውንና የአል ቃይዳ መሪ የተገደለበትን ጥቃት ታሊባን አውግዞታል።

የወቅቱ የአፍጋኒስታን ገዥ ታሊባን፤ አሜሪካ ጥቃት ያደረሰችው በመኖሪያ ቤት አካባቢ ነው ብሏል።

News today, Politics

አሜሪካ የአል ቃኢዳን መሪ ካቡል ውስጥ ገደለች

የኦሳማ ቢን ላደንን ሞት ተከትሎ አይማን አል-ዛዋሂሪን አል-ቃይዳን ሲመራ ቆይቷል

2 ነሐሴ 2022, 08:12 EAT

አሜሪካ የአል ቃኢዳውን መሪ አይማን አል-ዛዋሂሪን በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል ውስጥ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት መግደሏን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስታወቁ።

የአሜሪካ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሲአይኤ ባለፈው ዕሁድ ካቡል ውስጥ ባካሄደው የፀረ-ሽብር ዘመቻ ላይ ነው ዛዋሂሪን መግደል የቻለው ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ባይደን አይማን አል-ዛዋሂሪ “በአሜሪካ ዜጎች ላይ ግድያ እና ጥቃትን የቀረጸ ሰው ነው’’ ብለዋል።

አክለውም “አሁን ፍትህ ተሰጥቷል ፤ ይህ የአሸባሪ ቡድን መሪ ከዚህ በኋላ በሕይወት የለም” ሲሉም ግድያውን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል።

ዛዋሃሪ ከቀድሞው የአል-ቃኢዳ መሪ ቢን ላደን ጋር በመሆን ከ20 ዓመታት በፊት የተፈጸመውን የ9/11 ጥቃትን የመራ ሲሆን፣ አሜሪካ ለረጅም ዓመታት ስታፈላልገው የቆየችው የሽብር ቡድኑ መሪ ነው።

አይማን አል-ዛዋሂሪ የኦሳማ ቢን-ላደን ሕልፈትን ተከትሎም አል-ቃኢዳን ሲመራ ቆይቷል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት እንዳሉት ዛዋሂሪ በአንድ በጥብቅ በሚጠበቅ ቤት በረንዳ ላይ ተቀምጦ ባለበት ወቅት ነው የአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን ሁለት ሚሳኤሎችን ተኩሶ የገደለው።

እንዲሁም በቤቱ ውስጥ የነበሩ ሌሎች የቤተሰብ አባላት ምንም ጉዳት እንዳልደረሰባቸው እና በጥቃቱ ዛዋሂሪ ብቻ ተነጥሎ መገደሉንም አክለው ተናግረዋል።

ባይደን በ71 ዓመቱ የአል ቃኢዳ መሪ ላይ እርምጃውን ለመውሰድ ለወራት ዕቅድ ከወጣ በኋላ “የተመጠነ እና ትክክለኛውን ኢላማ የመታ ጥቃት” እንዲሰነዘር የመጨረሻውን የይለፍ ፍቃድ መስጠታቸውን ተናግረዋል።

የሽብር ቡድን መሪው ግድያም እ.ኤ.አ. በ2001 በተፈጸመው ጥቃት 3,000 የሚጠጉ ወዳጅ፣ ቤተሰቦቻቸውን ላጡ አሜሪካዊያን ለሐዘናቸው መልስ የሚሆን የመጨረሻውን መደምደሚያ የሚሰጥ እርምጃ ነውም ሲሉ አክለዋል።

“የቱንም ያህል ጊዜ ይፍጅ፣ የትም ይደበቁ፣ ለሕዝባችን ስጋት የሆነ አካል ካለ አሜሪካ ታገኛቸዋለች፣ ቀጥሎም ታስወግዳቸዋለች” ያሉት ባይደን አክለውም “አገራችንን እና ሕዝባችንን ከመከላከል ወደ ኋላ አንልም” ሲሉም አክለዋል።

ባይደን ዛዋሂሪ እ.ኤ.አ በጥቅምት 2000 በኤደን የአሜሪካ የባሕር ኃይል ግዙፍ የጦር መርከብ ላይ በተሰነዘረ የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃት 17 የአሜሪካ መርከበኞችን የገደለውን ጥቃት መርቷል ሲሉ ተናግረዋል።

እንዲሁም ለ223 ሰዎች ሕልፈት ምክንያት የሆኑት በ1998 በኬንያ እና በታንዛኒያ በአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ የተፈፀሙትን ጥቃቶችንም በማስተባበር ዛዋሂሪ ኃላፊነት እንዳለበትም አክለዋል።

ፕሬዝዳንት ባይደን አፍጋኒስታን ከእንግዲህ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ አትሆንም ሲሉም አጥብቀው ተናግረዋል።

የታሊባን ቃል አቀባይ የአሜሪካን ዘመቻ ዓለም አቀፍ መርሆችን የጣሰ ነው ሲሉ ገልፀውታል።

አክለውም “እንዲህ ያሉ ድርጊቶች ላለፉት 20 ዓመታት ያልተሳኩ ሙከራዎችን መደጋገም ናቸው። ድርጊቱም የአሜሪካን፣ የአፍጋኒስታንን ብሎም የቀጠናውን ጥቅም ጥቅም የሚፃረር ነው’’ ብለዋል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት በበኩላቸው በአል ዛዋሂሪ ላይ የተካሄደው ዘመቻ ሕጋዊ መሰረት ያለው ነው ብለዋል።

News today

በአሜሪካ የተገደለው ግብጻዊው ዶክተር እና የአል ቃኢዳ መሪ ማን ነበር?

አይማን አል-ዛዋህሪ

2 ነሐሴ 2022, 11:17 EAT

አፍጋኒስታን ውስጥ በአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት የተገደለው አይማን አል-ዛዋህሪ የአል ቃኢዳ ርዕዮተ ዓለም ዋና ጠንሳሽ ተብሎ ይጠራ ነበር።

ግብጻዊ ነው። የግብጽን እስላማዊ ጂሃድ ታጣቂ ቡድን ለመመስረትም ድጋፍ በማድረግ ይታወቃል።

አል-ዛዋህሪ የዓይን ቀዶ ሕክምና ባለሙያ ነው። እአአ ግንቦት 2011 የአሜሪካ ጦር ኦሳማ ቢን ላደን መገደሉን ተከትሎ የአል ቃኢዳ መሪ ሆነ።

ከዚያ በፊት አል-ዛዋህሪ የቢን ላደን ቀኝ እጅ እንደሆነ ይቆጠር ነበር። አንዳንድ ባለሙያዎች መስከረም 1/2001 በዩናይትድ ስቴትስ ከደረሰው ጥቃት ጀርባ የሚገኝ “ዋና ሰው” እንደሆነ ይታመናል።

የአሜሪካ መንግስት በአውሮፓውያኑ 2001 “በጣም የሚፈለጉ አሸባሪዎች” ብሎ ከዘረዘራቸው 22 ሰዎች አንዱ ነው።  በቢንላደን ብቻ ተቀድሞ አል-ዛዋህሪ ቁጥር ሁለት ላይ ተቀምጧል። አሜሪካ ያለበትን ለጠቆመ 25 ሚሊየን ዶላር እሸልማለሁ ብላ ነበር።

ከጥቃቶቹ በኋላ በነበሩት ዓመታት አል-ዛዋህሪ የአልቃኢዳ ዋነኛው ቃል አቀባይ ሆኖ ብቅ አለ። በ2007 ብቻ 16 ቪዲዮዎችን እና የድምጽ መልዕክቶችን አስተላልፏል። ይህ ከቢንላደን በአራት እጥፍ የሚበልጥ ቁጥር ነው።

ትኩረቱንም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሙስሊሞችን አክራሪ ለማድረግ እና ለመመልመል መሞከር ነበር።

ከቀናት በፊት በካቡል በተፈጸመ ጥቃት ነው አይማን አል-ዛዋህሪ የተገደለው። አሜሪካ ግለሰቡን ለማጥቃት ስትሞክር ግን የመጀመሪያዋ አልነበረም።

ጥር 2006 ፓኪስታን ከአፍጋኒስታን ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አካባቢ አሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት ዒላማዋ አድርጋው ነበር።

ጥቃቱ አራት የአልቃይዳ አባላትን ገድሏል። አል-ዛዋህሪ በሕይወት ተርፎ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ታየ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽም ሆኑ “በምድር ላይ ያሉ ኃያላን” ሞቱን “በአንድ ሰከንድ” ሊያቀርቡት እንደማይችሉ አስጠነቀቀ።

ከተከበረ ቤተሰብ የተገኘው ዶክተር

አይማን አል-ዛዋህሪ  በአውሮፓውያኑ ሰኔ 19 ቀን 1951 በግብጽ ርዕሰ መዲና ካይሮ ተወለደ። የተገኘው ከተከበሩ ሐኪሞች እና ምሁራን ቤተሰብ ነው።

አያቱ ራቢያ አል-ዛዋህሪ በመካከለኛው ምስራቅ የሱኒ እስላማዊ ትምህርት ማዕከል በሆነው የአል-አዝሃር ኢማም ነበሩ። አንዱ ከአጎቱ የአረብ ሊግ የመጀመሪያው ዋና ጸሐፊ ሆነው አገልግለዋል።

አይማን አል-ዛዋህሪ በትምህርት ቤት እያለ በፖለቲካዊ እስልምና ውስጥ ተሳትፏል። ህገ-ወጥ በሆነው የሙስሊም ወንድማማቾች አባል በመሆኑ በ15 ዓመቱ ለእስር በቅቶ ነበር። ይህ የግብጽ ትልቁ እስላማዊ ድርጅት ነው።

የፖለቲካ ዝንባሌው በካይሮ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ትምህርት ቤት ሕክምናን ከመማር አላገደውም። በ1974 ተመረቀ። ከአራት ዓመት በኋላ ደግሞ በቀዶ ሕክምና ሁለተኛ ዲግሪውን አግኝቷል።

በ1995 ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አባቱ መሐመድ በዚሁ ትምህርት ቤት የፋርማኮሎጂ መምህር ነበሩ።

አክራሪው ወጣት

አይማን አል-ዛዋህሪ መጀመሪያ የቤተሰቡን ዱካ ተከተለ። በካይሮ አካባቢ የህክምና ክሊኒክ ከፈተ። ብዙም አልገፋበትም። በኋላም የግብጽን መንግሥት ለመጣል በሚጥሩ አክራሪ እስላማዊ ቡድኖች ተማረከ።

በአውሮፓውያኑ 1973 የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ ተመሠረተ። አል-ዛዋህሪም ተቀላቀለ።

የቡድኑ የወታደር ልብስ ለብሰው ፕሬዝዳንት አንዋር ሳዳትን በካይሮ ወታደራዊ ትርኢት ላይ ገደሏቸው። ይህን ተከትሎም እአአ በ1981 ላይ ከበርካታ ተጠርጣሪ የቡድኑ አባላት ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ። ሳዳት ከእስራኤል ጋር የሠላም ስምምነት በመፈራረማቸው በቡድኑ ዘንድ ቁጣ ተቀሰቀሰ። ቀደም ሲልም የጸጥታ ሃይሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የፕሬዝዳንቱን ተቺዎች ማሰራቸው ቂም ፈጥሮ ነበር።

በጅምላ ችሎቱ ወቅት አል-ዛዋህሪ የተከሳሾቹ መሪ ሆኖ ቀርበ። “እኛ በዲናችን የምናምን ሙስሊሞች ነን። እስላማዊ መንግሥት እና እስላማዊ ማህበረሰብ ለመመስረት እየጣርን ነው” ሲል ለፍርድ ቤቱ ሲናገር ተቀርጿል።

በሳዳት ግድያ ውስጥ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንደሌለው ተገለጸ። ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በመያዝ ተከሶ ግን ሦስት ዓመት እስራት ተላለፈበት።

ቢን ላደን እና አይማን አል-ዛዋህሪ

እንደ እስላማዊ እስረኞች ገለጻ ከሆነ አል-ዛዋህሪ በግብጽ እስር ቤት በባለስልጣናት አዘውትሮ ይሰቃይና ይደበደብ ነበር። ይህም አክራሪ እንዲሆን አድርጎታል ተብሏል። 

በ1985 ከእስር የተፈታው አይማን አል-ዛዋህሪወደ ሳዑዲ አረቢያ አቀና።

ሳዑዲ ብዙም አልቆየም። ወደ ፓኪስታኗ ፔሻዋር አመራ። ቀጥሎ ወደ ጎረቤት አፍጋኒስታን አቀና። በሶቪየት ወረራ ወቅት በሐኪምነት ከመስራት ጎን ለጎን የግብጽ እስላማዊ ጂሃዳዊ አንጃን አቋቋመ።

የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ በ1993 እንደገና ሲያንሰራራ አል-ዛዋህሪ መሪነቱን ተረከበ። ቡድኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አጢፍ ሲድቂን ጨምሮ በግብጽ ሚኒስትሮች ላይ ተከታታይ ጥቃት ሰነዘረ። እሱም የጥቃቶቹ ቁልፍ ሰው ነበር።

በ1990ዎቹ አጋማሽ ቡድኑ መንግሥትን ለመጣል እና እስላማዊ መንግሥት ለመመስረት ዘመቻ አካሄደ። ይህም ከ1 ሺህ 200 በላይ ግብጻውያንን ለህልፈት ዳርጓል።

እአአ በ1997 የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዲፓርትመንት የቫንጋርድስ ኦፍ ኮንክሰስ ቡድን መሪ ነው ሲል ሰይሞታል። ይህ የእስልምና ጂሃድ ቡድን በዛው ዓመት በሉክሶር ከተካሄደው የውጭ ቱሪስቶች እልቂት ጀርባ ነበር።

ከሁለት ዓመት በኋላ በሌለበት በግብጽ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የሞት ፍርድ ተላልፎበታል። በቡድኑ ጦሩ ላይ ባደረሰው በርካታ ጥቃቶች ሚና ነው ውሳኔው የተላለፈበት።

ምዕራባውያን ዒላማዎች

አይማን አል-ዛዋህሪ እአአ በ1990ዎቹ ለሐይማኖታዊ እና የገንዘብ ድጋፍ ፍለጋ በዓለም ዙሪያ ተዘዋውሯል ተብሎ ይታሰባል።

ሶቪዬት አፍጋኒስታንን ለቃ ከወጣች በኋላ በነበሩት ዓመታት በቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ስዊዘርላንድ ይኖር ነበር። አንዳንዴ ሐሰተኛ ፓስፖርት በመጠቀም ጭምር ወደ ባልካን፣ ኦስትሪያ፣ የመን፣ ኢራቅ፣ ኢራን እና ፊሊፒንስ  ተጉዞ እንደነበር ይገመታል።

በታህሳስ 1996 ደግሞ ቺቺኒያ ውስጥ ህጋዊ ቪዛ ሳይኖረው ተይዞ ለስድስት ወራት ያህል በሩሲያ እስር ቤት እንደቆየ ይነገራል።

በአይማን አል-ዛዋህሪ  ተጽፏል በተባለው ጽሑፍ መሠረት የሩሲያ ባለስልጣናት በኮምፒዩተሩ ላይ የነበሩ አረብኛ ፅሁፎችን መተርጎም ባለመቻላቸው ማንነቱን በሚስጥር መያዝ ችሏል።

አይማን አል-ዛዋህሪ

እአአ በ 1997 አል-ዛዋህሪ ኦሳማ ቢን ላደን ወደከተመባት አፍጋኒስታኗ ጃላላባድ ከተማ እንዳቀና ይታመናል።

ከአንድ ዓመት በኋላ የግብጽ እስላማዊ ጂሃድ የቢን ላደኑን አልቃይዳን ጨምሮ ሌሎች አምስት አክራሪ እስላማዊ ታጣቂ ቡድኖችን በመቀላቀል በአይሁዶች እና በመስቀል ጦረኞች ላይ የዓለም እስላማዊ ጂሃድን መሠረተ።

የቡድኑ የመጀመሪያ አዋጅ የአሜሪካ ዜጎችን መገደል የሚፈቅደውን ፈትዋ ወይም ሃይማኖታዊ ድንጋጌን ያካትታል። ከስድስት ወራት በኋላ በኬንያ እና በታንዛንያ የሚገኙት የአሜሪካ ኤምባሲዎች በተመሳሳይ ወቅት ጥቃት ተፈጽሞባቸው 223 ሰዎች ሞቱ።

ከሴራው ጀርባ ቢንላደን እና አልቃኢዳ መኖራቸውን ለማረጋገጥ ከተወሰዱት ነገሮች አንዱ የአል-ዛዋህሪ የሳተላይት የስልክ ንግግር  ነበር።

ጥቃቱ ከተፈጸመ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ በአፍጋኒስታን የሚገኘውን የቡድኑን ማሰልጠኛ ካምፖች በቦምብ ደበደበች። በማግስቱ አይማን አል-ዛዋህሪ ለአንድ የፓኪስታን ጋዜጠኛ ደውሎ “የቦምብ ፍንዳታው፣ ዛቻው እና ጥቃቱ አያስፈራንም። ጦርነቱ ገና አሁን መጀመሩን ለአሜሪካ ንገራት” ብሎ ነግሮታል።

ከቢንላደን ሞት በኋላ በነበሩት ዓመታት የአሜሪካ የአየር ጥቃት የአል-ዛዋህሪ ምክትሎች ለመግደል አስችሏታል። ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበረ አቅሙን አዳክሞታል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ አል-ዛዋህሪ ሩቅ እና የተገነጠለ ሰው ሆነ ነበር። መልዕክቶችንም አልፎ አልፎ ብቻ ነበር የሚሰጠው።

አሜሪካ ባለፈው ዓመት ከአፍጋኒስታን የወጣችበት መንገድ በግርግር እና በጥድፊያ የተሞላ ነበር። እስላማዊ መንግሥት ያሉ አዳዲስ ቡድኖች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጽዕኖ እያሳደሩ በመሆናቸው አል-ዛዋህሪ ብዙም ስልጣን አሜሪካ መሞቱን እንደ ድል ታበስራለች።

አልቃኢዳ አዲስ መሪ ይፋ እንደሚደረግ ምንም ጥርጥር የለውም። አዲሱ መሪ ግን አይማን አል-ዛዋህሪ ያነሰ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል።

News today, Politics

የቻይና ጦር የአፀፋ እርምጃ ለመውሰድ በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆኑን ገለፀ

P.R.C


የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ጉብኝት የቻይናን ዛቻ ወደጎን ትተው የታይዋን ጉብኝታቸውን ጀምረዋል

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር የአፀፋ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆኑን አስታወቀ።

የቻይና መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ወ ዩ ኪያን፤ የቻይና ጦር የሀገሪቱን ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ ነው ብለዋል።

“የአሜሪካ ፖለቲከኞች የ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሕዝብ ጠላት መሆን አምሯቸዋል”- ቻይና
ቃል አቀባዩ የአሜሪካ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የቻይና አካል በሆነችው ታይዋን ክልል ለጉብኝት መግባታቸውን ተከትሎ የቻይና ጦር በተመረጡ ኢላማዎች ላይ ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።

የአሜሪካ አፈ ጉባኤ ናንሲ ሌሎሲ ታይዋንን ጨምሮ አምስት የእስያ ሀገራትን ጉብኝት መጀመራቸውን ተከትሎ ዓለም አይኑ ታይዋን ላይ አርፏል።

የአሜሪካዋ አፈጉባዔ የጉብኝታቸው አካል ወደሆነችው ታይዋን በዛሬው እለት ገብተዋል።

ቻይና በአሜሪካ ፖለቲካ ሶስተኛው የስልጣን ባለቤት እየሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን ከጎበኙ እርምጃ እወስዳለሁ ማለቷን ተከትሎ በሩቅ ምስራቅ ውጥረት ነግሷል።

ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ አወጀች
አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን መድረሳቸውን ተከትሎም የቻይና ሱ35 ጄቶች የታይዋንን የአየር ክልል ጥሰው መግባታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

ቻይና፤የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ጦሯ “ዝም ብሎ እንደማይቀመጥ”ቻይና ማስጠንቀቂያ አስተላልፋ እንደነበረ ይታወሳል።

News today, Politics

ፑቲን የኒዩክለር ጦርነት በየትኛውም መንገድ ቢሆን መቅረት እንዳለበት

ፑቲን የኒዩክለር ጦርነት በየትኛውም መንገድ ቢሆን መቅረት እንዳለበት አሳሰቡ
ፑቲን ሁሉም ሀገራት ኒውክለርን ለሰላማዊ ዓላማ እንዲጠቀሙ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባም ጥያቄ አቅርበዋል

የኒውዩክለር ጦርነትን በማንኛውም ዋጋ ቢሆን ማስወገድ እንደሚገባ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሳሰቡ።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከል ላይ ባተኮረው ጉባዔ ላይንግግር ማድረጋቸውን የሀገራቸው መገናኛ ብዙኃን አርቲ ዘግቧል።

ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ የሩሲያ “ዋነኛ ስጋት” ነች ሲሉ ፈረጁ
በቀጣይ ኒውክለርን በመጠቀም የሚረግን ጦርነት በየትኛውም መልኩ ማስቀረት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኒውክለር ጦርነት አሸናፊ የሌለውና ዓለም በፍጹም ሊሄድበት የማይገባ እንደሆነም ነው ቭላድሚር ፑቲን ያሳሰቡት።

ፑቲን ሀገራቸው ከአሜሪካ ለገባችውን ኒውክለርን ያለመታጠቅ ስምምነት እንደምትታመንም የገለጹት።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከልን የሚተገብሩ ሁሉም ሀገራት ኒውክለርን ለሰላማዊ ዓላማ እንዲጠቀሙ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባም ጥያቄ አቅርበዋል።

የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እንዴት ሊጠናቀቅ ይችላል?
የኒውክለር ጦር መሳሪያ ስርጭትን መከላከል ውል ዓላማዎች ስርጭቱን መግታት፣ አለመታጠቅና ለሰላማዊ ኃይል መጠቀም የሚሉትን ያጠቃልላል።

ይህንን ስምምነት 192 ሀገራት የተቀላቀሉት ሲሆን ኒውክለር የታጠቁትም በዚህ ስምምነት ውስጥ ተሳታፊ ናቸው።

ፕሬዝደንት ቫላድሚር ፑቲን አሜሪካን ዋነኛ የሩሲያ ጠላት እንደሆነች ትናንት የሀገራቸው የባሕር ኃይል ቀን ሲከበር ይፋ አድርገዋል።

News today, Politics

ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ የሩሲያ “ዋነኛ ስጋት” ነች ሲሉ ፈረጁ!!

ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ የሩሲያ “ዋነኛ ስጋት” ነች ሲሉ ፈረጁ!!

ፕሬዝደንት ፑቲን ይህን ያሉት በሩሲያ በሴንት ፒተርስበርግ በተከበረው እና ታሪካዊ ነው በተባለው የባህር ቀን ላይ ነው፡፡ ባለፈው ቅዳሜ አዲስ የባህር ኃይል መተዳደሪያ ላይ ፊርማቸውን ያስቀመጡት ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ ዋነኛ የሩሲያ ተቀናቃኝ አድርገው አስቀምጠዋል፡፡

በአዲሱ የባህር ኃይል መተዳደሪያ በአርክቲክ እና በጥቁር ባህር ሊኖር የሚችለው የሩሲያ እቅድ መነደፉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ በታላቁ ቄሳር ፒተር በተመሰረተችው የቀድሞዋ የንጉሠ ነገሥት ግዛት ሴንት ፒተርስበርግ በተከበረው የሩሲያ የባህር ኃይል ቀን ላይ ንግግር ያደረጉት ፑቲን ሩሲያን ታላቅ የባህር ሃይል እንዲኖራት የያደረጉትን ፒተርን አመስግነዋል፡፡

ፑቲን የባህር ሃይሉን ከጎበኙ በኋላ አጭር ንግግር ያደረጉት ሩሲያ ልዩ የሆነችው የዚርኮን ሃይፐርሶኒክ ክሩዝ ሚሳኤሎች በማሳየት ሩሲያ ወታደራዊ አቅም እንዳላት አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንቱ ንግግር ከማድረጋቸው ቀደም ብሎ የሩሲያን የባህር ኃይል ሰፊ ስትራቴጂካዊ አላማዎችን የያዘ ባለ55 ገጽ ሪፎርም ፈርመዋል፡፡

ከሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በኋላ በሩሲያ እና በምእራባውያን መካከል ያለው ፍጥጫ አይሏል፡፡ሩሲያ የኔቶ ጦር ወደ ቀድሞ የሶቬት ሀገራት መስፋፋት ለደህንነቷ እንደማያሰጋት በመግለጽ ነበር በዩክሬን ላይ “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ያወጀችው። ከዚህ በተጨማሪም ዩክሬንን ትጥቅ ማስፈታት እና የናዚን አስተሳሰብ ማጥፋት የዘመቻው አላማ መሆኑን ሩሲያ መግለጿ ይታወሳል።

በሩሲያ ርምጃ የተቆጡት ምእራባውያን ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ሁሉ ማእቀብ በሩሲያ ላይ ጥለዋል። የዶምባስ ግዛትን ነጻ የማውጣት የወሰነቸው ሩሲያ አሁንም በደቡብ እና ምሰራቃዊ ዩክሬን ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡

News today, Politics

የቻይና ጦር ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ


ፕሬዝዳንት ባይደንና የቻይና ሺ ጂንፒንግ በታይዋን እና በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ጉዳይ ይወያያሉ

በታይዋን ጉዳይ አለመግባባት ውስጥ ያሉት የአሜሪካ እና ቻይና ፕሬዝዳንቶች ውይይት ሊያደርጉ መሆኑ ተገለጸ።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በታይዋን እና በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ላይ ትኩረት ያደረገ ንግግር እንደሚያደርጉም ነው የተገለጸው፡፡

የአሜሪካዋ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ቻይና አስጠነቀቀች
ሁለቱ መሪዎች ነገ ከአራት ወራት በኋላ በስልክ ንግግር እንደሚደርጉ አንድ ከፍተኛ የዋሸንግተን ባለስልጣን መናገራቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

የአሜሪካዋ አፈ ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ ከሰሞኑ ታይዋንን እንደሚጎበኙ መግለጻቸውን ተከትሎ ቤጅንግ ቁጣዋን ገልጻለች፡፡

ከዚህ ባለፈም ቻይና አፈጉባዔዋ ወደ ታይዋን የሚሄዱ ካልሆነ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር፡፡

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የስልክ ውይይት ያደርጋሉ የተባለው በዚህ ውጥረት ውስጥም ሆነው እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የመሪዎቹን የስልክ ንግግር አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበለት የቻይና ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በታይዋን ጉዳይ ላይ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚወያዩ ቢጠበቅም በአውሮፓ ያለው ወታደራዊ ሁኔታም የውይይታቸው አካል እንደሚሆን ተገምቷል፡፡

ቻይና በታይዋን ጉዳይ ለአሜሪካ ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጠች
መሪዎቹ በዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ላይ ትኩረት ያደረገ ንግግር ይኖራቸዋል ተብሎ የተጠበቀ ሲሆን በእስካሁኑ ሂደት ዋሸንግተን ከዩክሬን፤ ቤጅንግ ደግሞ ከሩሲያ ጎን መሆናቸው ይታወሳል፡፡

የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ፤ ሁለቱ መሪዎች በኢኮኖሚ ውድድር ላይም ይነጋገራሉ ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ባይደን ከቻይናው አቻቸው ጋር ነገ ውይይት የሚያደርጉት ከኮሮና ቫይረስ ካገገሙ በኋላ ነው፡፡

News today, Politics

ኢራን የእስራኤልን የስለላ ኔትወርክ መያዟን አስታወቀች


ኢራን የስለላ ቡድኑ አባላት መረጃ ሲሰበሰቡ እና ጸረ -ኢራን የሆነ ፕሮፖጋንዳ ሲጽፉ ነበር ብላለች

የኢራን የደህንነት ድርጅት እንዳስታወቀው ኢራን ወሳኝ በሆኑ ዘርፎች ላይ መረጃ ለመሰብሰብ ሲንቀሳቀስ የነበረ የእስራኤል የስለላ ኔትዎርክ ይዛለች።

በቴህራን ያለው የአል ዓይን ኒውስ ጋዜጠኛ ያየው የኢራን የደህንነት ድርጅት መግለጫ፣ የእስራኤሉ ሞሳድ አካል የሆነው መረብ ተበጥሷል፤ኪሳራም ደርሶበታል ብሏል።

መግለጫው የስለላ ቡድኑ አባላት ከእስራኤል ጋር የመስራት ታሪክ ካለው የተገንጣይ ቡድን አመራር ከሆኑት መካከል በአንዱ አማካኝነት ከሞሳድ ኃላፊ ጋር መገናኘታቸውን ጠቅሷል።

ከዚህ በተጨማሪም የስለላ ቡድኑ አባት መረጃ ሲሰበስቡ፣ የጦር መሳሪያ ስልጠና ሲወስዱ እንዲሁም ጸረ ኢራን የሆነ የፕሮፖጋንዳ መፈክር ሲጽፉ ነበር ብሏል መግለጫው።

የኢራን የደህንነት ሚኒስቴር የታሰሩት እነማን እንደሆኑ፣የየት ሀገር ዜጎች እንደሆኑ እና የት እንደታሰሩ ግልጽ አላደረገም።

ደህንነቱ ባለፈው ሳምንት ወሳኝ የሆነ ተቋም ላይ ጉዳት ሊያደርሱ የነበሩ የእስራኤል የስለላ መረብ መያዙን ባለፈዉ ቅዳሜ ገልጾ ነበር።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ “ይህ የስለላ ኔትወረክ በሰሜን ኢራን በሚገኘው የኩርዲስታን ግዛት በኩል ወደ ኢራን ገብቷል፤ ፍንዳታ ለማድረስ የሚያስችል ዘመናዊ መሳሪያ ታጥቀው የነበሩት የኔትውኩ አባላት በክትትል ተይዘዋል።”

ነገርግን የኩርዱ ኮምላ የተባለው ፖርቲ አባላቱ ከእስራኤሉ ሞሳድ ጋር ግንኙነት አላቸው የሚለውን ክስ አስተባብለዋል

News today, Politics

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው ከአሜሪካ ጋር ለሚደረግ ማንኛውም ወታደራዊ ግጭት ዝግጁ መሆኗን በልበሙሉነት ተናገሩ፡፡

ሮይተርስ ዮንሃፕ የዜና አገልግሎትን ጠቅሶ እንደዘገበው ፤ ኪም የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ዮን ሶክዬኦል እና ሰራዊታቸው “አደገኛ” ሙከራዎችን ካደረጉ የመጥፋት አደጋ ሊደርስባቸው እንደሚችልም አስጠንቅቋል።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወታደሮቻቸው የኒውክሌር መከላከያ እንዲኖራቸውም መመሪያ ሰጥተዋል።

ሰሜን ኮሪያ ሩሲያ ቀደም ሲል በተባበሩት መንግስታት ያቀረበቸውንና መጋቢት በነበረው የተመድ  ጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ውድቅ የተደረገውን የ“አሜሪካ በዩክሬን ውስጥ ባዮሎጂካል የጦር መሳሪያ ትሰራለች” ክስም አቅርባለች፡፡

የሞስኮ አጋር የሆነችው ፒዮንግያንግ፤ ዋሽንግተንን “የሰው ልጅን ለጥፋት የሚወረውር የባዮ ሽብርተኝነት መጥፎ ስፖንሰር” እና በ1950ዎቹ በኮሪያ ጦርነት ወቅት “የባክቴሪያ ጦርነት” ያደረገች ሀገር ናት ስትልም ወቅሳለች፡፡

ይህንን መሰል ወቀሳዎች ከሰሜን ኮሪያ በተጨማሪ ቻይና እና ሩሲያ ደጋግመው ሲሉት የሚደመጡ ቢሆንም በዋሽንግተን ግን ይህንን ስታስተባብል ትስተዋላለች።

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፤ ከሁለት ወራት በፊት የሰሜን ኮሪያ ጦር ሃይሎች ምስረታ ቀንን ምክንያት በማድረግ ባደረጉት ንግግር ከእኛ ጋር ግጭት ውስጥ ለመግባት የሚፈልግን ማንኛውንም ሀገር “እናጠፋለን” ሲሉ መዛታቸው የሚታወስ ነው፡፡

ማንኛውም ሀገር ሰሜን ኮሪያ ከነካ አጸፋው የከፋ እንደሚሆን ያስጠነቀቁት ኪም ጆንግ ኡን፤ ፒዮንግያንግ አሁንም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እድገትን ለማፋጠን ጠንክራ ትሰራለች ሲሉም ተደመጠዋል፡፡

ኪም “በማንኛውም ጊዜ ሪፐብሊኩ የጣለባችሁን ኃላፊነት የተሞላበት ተልእኮ እና ልዩ መከላከልን ለመፈጸም ዝግጁ መሆን አለባችሁ” የሚል መልእክት ለኒውክሌር ኃይል ማስተላለፈቻውም ነበር የሰሜን ኮሪያ የዜና አገልግሎት ኤጀንሲ በወቅቱ የዘገበው።

እናም አሁን አሜሪካ በዩክሬን ምድር ባዮሎጂካል መሳሪያዎችን እያመረተች ትገኛለች የሚሉት ኪም፤ ከአሜሪካ ጋር ግጭት እንዳይገቡ እጅጉን ተሰግቷል፡፡

ሩሲያ በየካቲት ወር መጨረሻ በዩክሬን ላይ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ማካሄድ የጀመረችው፤ ዋሽንግተን በዩክሬን ውስጥ ባዮሎጂካል መሳሪያዎችን ለማምረት ለምርምር የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች የሚል ክስ ማቅረብ ከጀመረች በኋላና ወደፊት በሩሲያ ላይ ሊጋረጡ የሚችሉ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል በሚል እንደነበር አይዘነጋም፡፡

News today, social life

ሩሲያ ለኢትዮጵያ 162 ሚሊዮን ዶላር ብድር መሰረዝዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሩሲያ ለኢትዮጵያ 162 ሚሊዮን ዶላር ብድር መሰረዝዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ያጎለብተዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ከሶቭየት ህብረት የተበደረቻቸውን ብድሮች መሰረዟን በይፋ አሳውቃለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ከሶቭየት ህብረት ወይም አሁን ላይ ሩሲያ ተብላ ከምትጠራው ሀገር 162 ሚሊዮን ዶላር የተበደረችውን ገንዘብ ሰርዛለች ያሉት አምባሳደር መለስ በብድር መልክ ሊከፈል የነበረው ገንዘብ ለምን አገልግሎት መዋል እንዳለበትም ሁለቱ ሀገራት ተስማምተዋልም ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለሩሲያ በብድር መልክ ልትከፍለው የነበረው 162 ሚሊዮን ዶላር ባልቻ ሆስፒታልን እና መልካ ዋከና የሀይል ማመንጫ ጣቢያ ለማዘመን እንዲውል መስማማታቸውም ተገልጿል።

ቃል አቀባዩ አቶምባሳደር መለስ በመግለጫቸው አክለውም፣ በኢትዮጵያ በህገወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች ምዝገባ መጀመሩን እና እስካሁን 60 ሺህ ሰዎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በእስካሁኑ ምዝገባ የካናዳ፣ አሜሪካ፣ኮንጎ፣ ናይጀሪያ ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ኤርትራ ፣ሱዳን፣ቻይና፣ ቡሩንዲ ጋና፣ ህንድ፣ ባንግላዲሽ፣ ላይቤሪያ፣ ጣልያን እና የካሜሩን ዜግነት ያላቸው ህገወጥ ሰዎች መገኘታቸው ተገልጿል።

በዚህ ምዝገባ የተካተቱት በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቪዛ ጊዜያቸው የለፈበት፣ በህጋዊ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ፣ የስደተኝነት ፈቃድ የሌላቸው እና ፈቃድ ለማግኝት በሂደት ላይ ያሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች ናቸው ተብሏል።

ዲፕሎማቶች፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና ህጋዊ ቪዛ ያላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች በምዝገባው እንደማይካተቱም ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

ህገወጥ የውጭ ሀገራትን የመመዝገብ ስራው በአዲስ አበባ 21 ቦታዎች፣ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፎች ሰበታ፣ ቡራዩ፣ ሆለታ፣ሱሉልታ፣ ለገጣፎ፣ ገላን እና ዱከም ከተሞች እየተመዘገቡ እንደሆነ ተገልጿል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ግብጽን ከጎበኙ በኋላ በካይሮ ስለ ህዳሴው ግድብ ተናገሩት ተብሎ የወጣውን መረጃ የሶማሊያ መንግሥት አቋም እንዳልሆነ ኢትዮጵያ ትረዳለችም ሲሉ አምባሳደር መለስ በመግለጫቸው ተናግረዋል።

በግብፅ ብዙሃን መገናኛዎች የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ከግብጽ አቻቸው ጋር በጋራ ሆነው ተናገሩት ተብሎ የወጣው ዘገባ የአንድ ወገን አስተያየት ነው፣ በመሆኑም የሶማሊያ መንግስት በይፋ ስለ ህዳሴው ግድብ ያወጣው መግለጫ እንደሌለም ተገልጿል። 

News today, Politics

አሜሪካ፤ ሩሲያ የዩክሬን ግዛቶች ለመጠቅለል መሰረት እየጣለች ነው አለች


አሜሪካ፤ ሩሲያ የዩክሬን ግዛቶች ለመጠቅለል መሰረት እየጣለች ነው አለች

በኔቶ የአሜሪካ ተልዕኮ “የሩስያን ቀጣይ እርምጃ እናውቃለን” ብሏል

አሜሪካ፤ ሩሲያ የዩክሬን ግዛቶችን በጉልበት የመጠቅለል እቅዷን ከቀጠለችበት ፈጣን ምላሽ እንወስዳለን ስትልም ዝታለች

ሩሲያ የዩክሬንን ሉዓላዊነት በቀጥታ በመጣስ ግዛቶችን የምትቆጣጠረው በስሯ ያሉ ግዛቶችን ለመጠቅለል የሚያስችላት መሰረት ለመጣል መሆኑን በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) የአሜረካ ተልዕኮ ገለጸ፡፡

ተልዕኮው በትዊተር ገጹ ላይ ባጋራው ጽሁፉ “የሩስያን ቀጣይ እርምጃ እናውቃለን”ም ብሏል ፡፡

ሩሲያ የዩክሬን ግዛቶች በጉልበት የመጠቅለል እቅዷን ከቀጠለችበት ከአጋሮቻችን ጋር በመሆን በፍጥነት እና በከፍተኛ ሁኔታ ምላሽ እንሰጣለን ሲል ተልዕኮው ዝቷል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ምድር እየሄደችበት ያለው ግዛቶችን የመጠቅለል ወታደራዊ እርምጃ ያሰጋውና አሜሪካና አጋሮቿን በአባልነት ያቀፈው ኔቶ የጦሩን ቁጥር ለማሳደግ እየሰራ መሆኑ በድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ አማካኝነት በቅርቡ መግለጹ አይዘነጋም፡፡

ዋና ጸሃፊው “የኔቶን ኃይል እናጠናክረዋለን እንዲሁም የከፍተኛ ዝግጁነት ሀይላችንን ቁጥር ከ 40 ሺህ ወደ 300 ሺህ እናሳድጋለን” ነበር ያሉት፡፡

ሩሲያ በበኩሏ አሜሪካም ሆነ ኔቶ አጋሮቿ በዚህ ጉዳይ ላይ እጃቸው ካስገቡና ወደ እንደ ክሪሚያ ወደ መሳሰሉ ግዛቶች ከተጠጉ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ይጀመራል ስትል ማስጠንቀቋ የሚታወስ ነው፡፡

የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዝዳንት ድሚትሪ ሜድቬዴቭ በቅርቡ እንደተናገሩት ኔቶ ወደ ክሪሚያ የሚያደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴ “ሶስተኛውን የዓለም ጦርነት የሚያስነሳ ነው”ም ብለው ነበር፡፡ 

News today, Politics

የብሪታንያ እጩ ጠቅላይ ሚንስትር ቻይናን በጠላትነት ፈረጁ


ቻይና የአውሮፓን ቴክኖሎጂ በመስረቅና ሩሲያን ትደግፋለች ሲሉ ሱናክ ከሰዋል

የብሪታንያ እጩ ጠቅላይ ሚንስትር ቻይናን በጠላትነት ፈረጁ።

የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ከፓርቲያቸው እና ከስራ ባልደረቦቻቸው በደረሰባቸው ጫና ስልጣን እለቃለሁ ማለታቸው ይታወሳል።

ይሄንን ተከትሎም ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት 11 እጩዎች ቀርበው በመጨረሻም የህንድ ዝርያ ያላቸው ሪሺ ሱናክ እና ሊዝ ትሩስ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል።

ቻይና የእስያ ሀገራት የዓለማችን ኃያላን መጠቀሚያ ከመሆን እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀች
የብሪታንያ ፋይናንስ ሚንስትር የሆኑት እና አሁን ላይ ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት በመጨረሻ ትንቅንቅ ላይ የሚገኙት ሪሺ ሱናክ ምርጫውን አሸንፈው የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ከሆኑ በቻይና ላይ ማዕቀቦችን እንደሚጥሉ ተናግረዋል።

ቻይና የአውሮፓን እና የብሪታንያ ቴክኖሎጂዎችን እየሰረቀች ነው የሚሉት እጩ ጠቅላይ ሚንስትሩ በስልጣን ዘመናቸው ቻይና ለፋብሪካዎቿ ከብሪታንያ የምትገዛቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዳይደርሷት አደርጋለሁ ሲሉም ተናግረዋል።

እጩ ጠቅላይ ሚንስትሩ አክለውም ቻይና ዩክሬንን ከወረረችው ሩሲያ ነዳጅ በገፍ በመግዛት ድጋፍ እያደረገች እንደሆነም ገልጸዋል።ቻይና ከዚህ በፊት እጩ ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ከሌሎች እጩዎች ጋር ሲነጻጸሩ የተሻሉ መሪ እንደሆኑ ተናግራ ነበር።

እጩ ጠቅላይ ሚንስትር ሱናክ በምርጫው ካሸነፉ በብሪቴን ያሉ ከ30 በላይ የቻይና ባህል ማዕከላትን እንደሚዘጉም ዝተዋል።

ቻይና ከቴክኖሎጂ ወረራዎች ባለፈ በባህል እና ሌሎች ተያያዥ ዘርፎች ተጽዕኖ እየፈጠረች ነው የሚሉት ሱናክ ይህን በብሪታንያ ምድር እንዲከወን አልፈቅድም ሲሉም ተናግረዋል።

ቦሪስ ጆንሰንን የሚተኩት ጠቅላይ ሚንስትር በፈረንጆቹ መስከረም 5 ቀን 2022 የብሪታንያ ወግ አጥባቂ ፓርቲ ያሳውቃል ተብሏል።

News today, Politics

የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚልኩት የነዳጅ መጠን በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ

የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚልኩት የነዳጅ መጠን በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ

ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ አውሮፓ የሚላከው የድፍድፍ ነዳጅ መጠን ካሳለፍነው ጥር ወር ወዲህ በ90 በመቶ መጨመሩ ተገለፀ።

የነዳጅ ፍላጎቱ የጨመረው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎ የአውሮፓ ሀገራት በሩሲያ ነዳጅ ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ተከትሎ ነው።

ብሉምበርግ ባወጣው ሪፖርት መሰረት ባሳለፍነው 20 ቀናት ብቻ 1 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከሳዑዲ አረቢያ በግብጽ በኩል በሚያልፍ መስመር ወደ አውሮፓ የገባ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊየን በርሜል ደግሞ በስዊዝ ካናል በኩል ወደ አውሮፓ ገብቷል።

News today, Politics

የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ከህወሓት ጋር ስለሚደረገው ድርድርና ስለ ህዳሴ ግድብ ለመነገጋገር ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ


የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ከህወሓት ጋር ስለሚደረገው ድርድርና ስለ ህዳሴ ግድብ ለመነገጋገር ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ

ማይክ ሀመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው የአፍሪካ ህብረት ጋርም የሚመክሩ ይሆናል

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር

ልዩ መልእከተኛው ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ወደ ግብጽና እና አረብ ኢሚሬትስ ያቀናሉ

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር በዛሬው እለት አዲስ አበባ ይገባሉ።

ማይክ ሀመር በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል ይደረጋል የተባለውን የሰላም ድርድር ለማፋጠን የሚደረገውን ጥረት የመገምገም ዕድል እንደሚኖራቸውም ነው የተገለጸው።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት ማምሻውን ባወጣው መገልጫ፤ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ያለበትን ሁኔታ መገምገም እንዲሁም በጦርነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ ማድረግን የተመከቱ ጉዳዮች ማይክ ሀመር በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከሚመክሩባቸው አንኳር ጉዳዮች መሆናቸውን ጠቅሷል።

ልዩ መልዕክተኛው ከጦርነቱ በተጨማሪ ስለ ታላቁ ህዳሴ ግድብም ይነጋገራሉ ተብሏል።

ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በሚወዛገቡበት ጉዳይ ላይ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ ለማምጣት የአሜሪካ ድጋፍ እንደሚያደርጉ መግለጫው የጠቀሰ ሲሆን ይህም የሁሉንም አካላት ፍላጎት በሚያረካ መልኩ ነው ተብሏል።

ማይክ ሀመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው የሶስትዮሹን ድርድር ሲመራ ከነበረው የአፍሪካ ህብረት ጋርም የሚመክሩ ይሆናል።

ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ወደ ግብጽ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንደሚያቀኑም ነው የተገለጸው።

ዴቪድ ሳተርፊልድን በመተካት በአፍሪካ ቀንድ አዲስ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው የተሾሙት ማይክ ሀመር ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ሲያደርጉ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ “አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሁሉም ህዝቦች ዘላቂ ሰላም፣ ደህንነት እና ብልጽግና ለማምጣት ያስችል ዘንድ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደትን መደገፍ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ለማራመድ ቁርጠኛ ነች” ነች ብሏል፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተው ግጭት የተለያዩ አሳዛኝ ክስተቶች እያስተናገደና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዋና አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል።አሁን ላይ የጦርነቱ ተዋናዮች ማለትም የፌዴራል መንግስት እና ህወሐት ወደ የድርድር ሃሳብ መምጣታቸው የሚታወቅ ነው።

በፌዴራል መንግስት እና ህወሐት መካከል ያለውን ቀውስ በሰለማዊ መንገድ የሚፈታበት መንገድ ካለ፤ አሳዘኝ ውድመት ያስከተለውንና በርካቶችን ለሞትና እንግልት የዳራገውን ጦርነት በድርድር ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከሰሞኑ የህወሐት ተደራዳሪ ቡዱን ማዋቀሩን በቃል አቀባዩ ጌታቸው ረዳ በኩል ያስታወቀው ህወሐት በኬንያ መንግስት አሸማጋይነት በናይሮቢ የሚደረግ የሰላም ንግግር ካለ በድርድሩ የሚሳተፍ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

የፌዴራል መንግስት በበኩሉ የሀገር ብሄራዊ ጥቅምን ባስጠበቀ መልኩ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚካሄድ ድርድር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑና ስራ መጀመንሩ፤ በጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ እንዲሁም በሌሎች ባለስልጣናት አማካኝነት ሲገልጽ ቆይቷል።

ሁለቱ አካላት ለሰላም ድርድሩ ያላቸውን ፍላጎት ቢገልጹም ውይይቱ መቼ ይጀመር፣ የትስ ቦታ ነው በሚለው ላይ በግልጽ የተባለ ነገር የለም።

News today, Politics

የሩሲያው ጋዝፕሮም ከኢራን ጋር የ40 ቢሊዮን ዶላር ንግድ ስምምነት ፈጸመ

የሩሲያው ጋዝፕሮም ከኢራን ጋር የ40 ቢሊዮን ዶላር ንግድ ስምምነት ፈጸመ
በስምምነቱት መሰረት ጋዝፕሮም ኢራን በቀን 100 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ጋዝ ማምረት የሚያስችላትን መሰረተ ልማት ይዘረጋል ተብሏል
የሩሲያ፣ ተርኪዬ እና ኢራን ፕሬዝዳንቶች በቴህራን እየተወያዩ ነው

የሩሲያው ጋዝፕሮም ከኢራን ጋር የ40 ቢሊዮን ዶላር ንግድ ስምምነት ተፈራረመ።

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በኢራን ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው።የፕሬዝዳንቱን ጉብኝት ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት የንግድ እና ኢንቨስትመንት ስምምነቶችን ፈጽመዋል ተብሏል።

የሩሲያው ጋዝፕሮም የነዳጅ ኩባንያ ከኢራን አቻው ጋር የ40 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርሟል ሲል አርቲ ዘግቧል።

ስምምነቱ ኢራን በሰሜናዊ የሀገሪቱ አካባቢ በቀን 100 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ተጨማሪ ነዳጅ እንድታመርት የሚያስችል መሰረተ ልማት ጋዝፕሮም ኩባንያ ይፈጽማል ተብሏል።

ቴህራን የሩሲያ፣ ተርኪዬ እና ኢራን የሶስትዮሽ ውይይት መድረክን በማስተናገድ ላይ ስትሆን የሶስቱም ሀገራት መሪዎች በመድረኩ ላይ ተገኝተዋል።

የሶስቱ ሀገራት መሪዎች ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ላለችው ሶሪያ የተሻለ መፍትሄ መፈለግ በሚቻልበት ዙሪያ ይወያያሉ ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም የሶስቱ ሀገራት መሪዎች በተናጠል ዲፕሎማሲያዊ እና በአካባቢያዊ አጀንዳዎች ዙሪያ እንደሚወያዩ ተገልጿል።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ሩሲያ ጦሯን ወደ ዩክሬን የላከች ሲሆን ጦርነቱ ከተጀመረ አምስት ወራት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርቶታል።

በዚህ ጦርነት ምክንያትም ከአሜሪካ እና ምዕራባውያን ሀገራት ከስድስት ሺህ በላይ ማዕቀቦች የተጣሉባት ሩሲያ የእስያ እና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጋር አዳዲስ የንግድ ስምምነቶችን በማድረግ ላይ ትገኛለች።

ኢራን፣ ህንድ፣ ቻይና እና በተለያዩ አህጉራት የሚገኙ ሌሎች ሀገራት ደግሞ ከሩሲያ ጋር አዲስ የንግድ ስምምነቶችን በመፈጸም ላይ ናቸው።

News today, Politics

አምባሳደር ስለሺ በቀለ፤ ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ጋር በድርድርና በአጎአ ዙሪያ መወያየታቸው ተገለፀ

አምባሳደር ስለሺ በቀለ፤ ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ጋር በድርድርና በአጎአ ዙሪያ መወያየታቸው ተገለፀ
ልዩ መልዕክተኛ በዚህ ሳምንት ወደ አፍሪካ ቀንድ አካባቢ እንደሚመጡ ይጠበቃል

በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ በአፍሪካ ቀንድ ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሚካኤል ሃመር ጋር መነጋገራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

አምባሳደር ስለሺ እና በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በተጀመረው ጥረትና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ነው ውይይት ማድረጋቸው የተገለጸው።

አሜሪካ ማይክ ሀመርን በአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አድርጋ ሾመች
ሁለቱ ዲፕሎማቶች ስለመንግስትና ህወሃት ድርድር፤ ስለሰብዓዊ ድጋፍ፣ ብሔራዊ ምክክር፣ የሕዳሴ ድርድር፣ አጉዋ እንዲሁም ኤአር 6600 እና S3199 መወያየታቸው ተገልጿል፡፡

አምባሳደር ስለሺ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ያልተቆጠበ ስራ እየሰራ መሆኑን ለዲፕሎማቱ መናገራቸው ተገልጿል፡፡

አሁን ላይ መንግስት በሀገሪቱ ሰላም ይመጣ ዘንድ የሥራ ሂደቶችን የጀመረ መሆኑን የገለጹት ዲፕሎማቱ፤ ይህንን ዕውን ለማድረግ ግን ሌኛው ወገንም ሊሰራ እንደሚገባ ነው ያነሱት።

በሌላኛው ወገን ያለው አካል ሰላም እንዲመጣ ቢሰራ መንግስት የጀመረው የሰላም ጥረት ዕውን እንደሚሆንም ነው የኢትዮጵያ ዲፕሎማት የገለጹት።

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሚካኤል ሃመር በበኩላቸው የተጀመረው የሰላም ጥረት እንዲሳካ ሀገራቸው ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጸዋል።

የአሜሪካ ዲፕሎማት ኢትዮጵያውያን ሰላም እንዲያገኙ ሀገራቸው ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቷንም ለአምባሳደር ስለሺ ገልጸዋል ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

አምባሳደር ስለሺ መንግስት በግጭት እና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የሰብዓዊ ድጋፍ የማድረሱ ስራ ያለእንቅፋት መቀጠሉን ማንሳታቸው ተገልጿል።

አሜሪካ የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰዳቸው ላላቸው ጥረቶች አድናቆት እንዳለው መግለጹን የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

የሕዳሴ ግድብን በሚመለከት ኢትዮጵያ የምትከተለው አቋም ሚዛናዊ መሆኑን የገለጹ ሲሆን አምባሳደር ሚካኤል ሃመር ደግሞ ሶስቱ ሀገሮች ሁሉንም ጠቃሚ የሚያደርግ መንገድ ላይ ይደርሳሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

አምባሳደር ስለሺ ኢትዮጵያ ከአግዋ ተጠቃሚነቷ የወጣችበት መንገድና ማዕቀብ ለመጣል የተዘጋጁት ኤአር 6600 እና S3199 ረቂቆችም ረጅም ጊዜ ላስቆጠረው የአዲስ አበባንና የዋሸንግተንን ግንኙነት የሚመጥን እንዳልሆነና መስተካከል እንዳለበት መጠየቃቸው ተገልጿል፡፡

“የሱዳን ሽግግር መንግስትን በኃይል መቀየር የአሜሪካን ድጋፍ ያሳጣል”- የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ
የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ወደ አጉዋ ተጠቃሚነት እንዲትመለስ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸው ጠቃሚ መሆኑን መግለጻቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገለጸው።

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሚካኤል ሃመር በዚህ ሳምንት ወደ አፍሪካ ቀንድ አካባቢ እንደሚመጡ ይጠበቃል።

News today, Politics

አውሮፓ ህብረት ሩሲያ የምግብ አቅርቦትን እንደ ‘ድብቅ ሚሳኤል’ እየተጠቀመችበት ነው የሚል ክስ ያቀርባል

አውሮፓ ህብረት ሩሲያ የምግብ አቅርቦትን እንደ ‘ድብቅ ሚሳኤል’ እየተጠቀመችበት ነው የሚል ክስ ያቀርባል

የአውሮፓ ህብረት በዓለም አቀፍ የምግብ እና ማዳበሪያ ንግድ ላይ ያሉ ማነቆዎችን ለማቃለል በሞስኮ ባንኮች ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንደሚያሻሽል አስታወቀ፡፡

ህብረቱ ማሻሻያወን ለማድረግ በሚያስችለው ረቂቅ ሰነድ ላይ በመምከረም ተሰምቷል፡፡

ህብረቱ በሩሲያ ባንኮች ላይ የወሰደውን እርምጃ ተከትሎ የዓለም የምግብ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ችግር መፈጠሩ አይዘነጋም፡፡

በተለይም ሩሲያ በጥቁር ባህር የሚገኙ ወደቦች ዝግ ማድረጓ፤ የምግብ እጥረቱ በተለይም እንደ አፍሪካ ባሉ ክፍለ አህጉራት ከፍተኛ ጫና መፍጠሩ የአፍሪካ ህብረትም ጭምር ሲገልጽ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

እናም ችግሩን ከግምት ያስገባው የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ የገንዘብ ተቋማት ላይ በጣለው ማዕቀብ ላይ ማሻሻያ አደርጋለሁ ብሏል፡፡

አንድ የአወሮፓ ህብረት ለሮይተርስ እንደተናገሩት ከሆነ፤ ረቂቅ ሰነዱ ረቡዕ የሚጸድቅ ይሆናል፡፡

አውሮፓ ህብረት ሩሲያ የምግብ አቅርቦትን እንደ ‘ድብቅ ሚሳኤል’ እየተጠቀመችበት ነው የሚል ክስ ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሸል ከአንድ ወር በፊት በኒውዮርክ በነበረው የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እንደተናገሩት፤ ሩሲያ የምግብ አቅርቦትን እንድ ድብቅ ሚሳዔል በመጠቀም በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለከፋ ድህነት እየዳረገች ነው ሲሉ ከሰዋል፡፡

ሚሸል “የሚያሳዝነው ሩሲያ የጀመረችው ጦርነት በመላው ዓለም እየተዛመተ መሆኑ ነው፤ የምግብ ዋጋ እጅጉን እንዲንር በማድረግ የዓለም ህዝቦች ለድህነት እንዲዳረጉና የተለያዩ ቀጠናዎች እንዲታመሱ እያደረገ ነው ፤ለዚህ ሁሉ ቀውስ ተጠያቂ ሩሲያ መሆኗ ሊታወቅ ይገባል” ነበር ያሉት፡፡

ሩሲያ ግን በተወካይዋ አማካኝነት “መሰረተ ቢስ” ስትል በወቅቱ ክሱን ውድቅ ማድረጓ ይታወቃል፡፡

News today, Politics

እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል ” – አል ሃማሚ

እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል ” – አል ሃማሚ
ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ወንጀል እንዲሆን እና ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንዲጣል እየሰራች መሆኗን አሳውቃለች።
የኢራቅ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚከለክል ህግ ለማፅደቅ ማቀዱን አስታውቋል።

ኢራቅ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሶስት ብዙ አረቦች ከሚኖሩበት ሀገር መካከል አንዷና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን #በግልፅ ወንጀል እንደሆነ ካላወጁ ሀገራት የምትጠቀስ ናት ፤ ሌሎቹ ጆርዳን እና ባህሬን ናቸው። ምንም እንኳን በግልፅ ወንጀል ነው ተብሎ ባይገለፅም ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ በጣም የተወገዘ ነው።
አሁን ያለው ሁኔታ ያላማራት ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንደሆነ በህግ ለመደንገግ እየሰራች ሲሆን ህጉ ከወጣ ኢራቅ ሌሎች ድርጊቱን በህግ ወንጀል እንደሆነ ካፀደቁ ሀገራት ተርታ ትሆናለች።
አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በቀጥታ በግልፅ የሚከለክሉ ሲሆን ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስራት ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ #የሞት_ቅጣት ትቀጣለች።

በኢራቅ ፓርላማ የህግ ኮሚቴ ውስጥ ያሉት የፓርላማ አባል አሬፍ አል ሃማሚ ለDW በሰጡት ቃላቸው ፥ ” አዲሱ ህግ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል ፤ በእነሱ ላይም ከባድ ቅጣት ይጥላል ” ብለዋል።

ህጉ እስካሁን ድምጽ ያልተሰጠበት ሲሆን ድምፅ እንዲሰጥበት እየተሰራ ነው። አል ሃማሚ ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ #የሰብአዊ_መብት_ተሟጋች_ድርጅቶች ትችት ቢሰነዘርም ህጉ ይፀድቃል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

” እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል ” ሲሉም ገልፀዋል።

የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች እስከ ሞት ድረስ የምትቀጣድ ሳዑዲ አረቢያ ከወራት በፊት ድርጊቱን ያስተዋውቃል ያለችውን ምልክት ያለባቸውን ቁሳቁሶች ከየመደብሩ ስትሰበስብ እንደነበር ይታወሳል፤ በተጨማሪ ሁለት የምዕራባውያን የልጆች ፊልሞችን በሀገሯ እንዳይታዩ ማገዷም አይዘነጋም።

News today, Politics

አረብ ኤምሬትስና ፈረንሳይ በኢነርጂ ዘርፍ ሁሉን አቀፍ የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ

ስምምነቱ ነዳጅን ጨምሮ የኃይል አማራጮችን በዘላቂነትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የሚያስችል ነው

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስና ፈረንሳይ በኢነርጂ ዘርፍ ሁሉን አቀፍ የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት መፈራረማቸው ተገለፀ።

የፊርማ ስነ ስርዓቱ የአረብ ኤሚሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ ሞሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን እና የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በተገኙነት ነው የተካሄደው።

ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በመጀመሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸው ፈረንሳይን ለምን መረጡ?
በኃይል ዘርፍ የተደረሰው አጠቃላይ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ስምምነት በአረብ ኤምሬትስ እና በፈረንሳይ መካከል የመጀመሪያ ሲሆን፤ በአረብ ኢሚሬትሱ ኤዲኖክ እና በፈረንሳዩ ቶታል ኢነርጂ መካከል ሁለተኛው የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት ነው።

የመጀመሪያው ስትራቴጂካዊ አጋርነት በአረብ ኤምሬትስ በ2023 ለሚካሄደው 28ኛው የአየር ንብረት ጉባዔ (COP28) ስብሰባ ለመዘጋጀት ውጤታማ የአየር ንብረት ርምጃዎችን ለማስፋት ልምድ ለመለዋወጥ ሲሆን፤ በተጨማሪም የነዳጅን ጨምሮ ኃይል አቅርቦት ደህንነት ለማረጋገጥ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የሚያስችል ነው።

በአረብ ኢሚሬትስ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት ዶ/ር ሱልጣን አህመድ አል ጃበር ፤ “አረብ ኢምሬትስ እንደ አስተማማኝ የሃይል አቅራቢነቷ የኃይል አቅርቦት ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባትን እንደመትሰራ አስታውቀዋል

ስምምነቱ አረብ ኤሚሬትስ ለአጋሯ ፈረንሳይ በኃይል ዘርፍ ቀጣይነት ያለው እና ደህንነቱ የተጠበቀ ኃይል በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የሚያስችል እንዲሁም የሁለቱን ወዳጅ ሀገራት ኢኮኖሚ እድገት እና ብልጽግናን የሚያግዝ ነው ብለዋል።

ፈረንሳይ እና አረብ ኢሚሬትስ በኢነርጂ ልማት ዘርፍ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ትብብር የነበራቸው ሲሆን የፈረንሳዩ ቶታል ኢነርጂ በአውሮፓውያኑ ከ1939 ጀምሮ በአቡዳቢ በነዳጅ እና ጋዝ ልማት ዘርፍ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል።

አረብ ኢምሬትስ ካራካል የተሰኘ የኤርባስ ስሪት ሂልኮፕተሮችን ተረከበች
ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ ሀገራት የተለያዩ የንግድ ግንኙነቶችን ያላቸው ሲሆን፤ በፈረንጆቹ 2020 ብቻ የፈረንሳይ 3.1 ቢሊዮን ዩሮ ዋጋ ያለው ምርት ወደ አረብ ኤሚሬትስ ልካለች፤ በአንጻ ከአረብ ኢሚሬትስ 750 ሚሊዮን ዩሮ ግምት ያለው ምርት ወደ ሀገሯ አስገብታለች።

አረብ ኢሚሬትስ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሀገራት ውስጥ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፈረንሳይ ኩባንያዎችን ተቀብላ እያስተናገደች ሲሆን፤ በሀገሪቱ የሚገኝ 600 ኩባያዎች ከ30 ሺህ በላይ ሰራተኞችን መቅጠራቸው እና የሚቀጥሩት የሰው ሀይል መጠንም በየአመቱ በ10 በመቶ እድገት እንዳለው መረጃዎች ይጠቁማሉ

News today, Politics

ሩሲያ በጎግል ኩባንያ ላይ የ366 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት አስተላለፈች

ሩሲያ በጎግል ኩባንያ ላይ የ366 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት አስተላለፈች ሩሲያ ከዚህ በፊት 98 ቢሊዮን ዶላር እንዲከፍል መወሰኗ ይታወሳል

ሩሲያ ውሳኔውን በጎግል ላይ የወሰነችው ከዩክሬን ጋር በተያያዘ ከ 7 ሺህ በላይ ያልተገባ ምስል አሰራጭቷል በሚል ነው

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ነበር ከሩሲያ ጋር ወደ ይፋዊ ጦርነት ያመሩት።

ሩሲያ የአሜሪካዊያን ንብረት በሆነው ጎግል ኩባንያ ላይ 366 ሚሊዮን ዶላር እንዲከፍል ወስናለች።

በሞስኮ የሚገኘው ታጋንስኪ ግዛት ፍርድ ቤት ጎግል ኩባንያ ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ሀሰተኛ ምስሎችን አሰራጭቷል በሚል የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፉን አርቲ ዘግቧል።

ዘገባው አክሎም ጎግል ኩባንያ ስለ ዩክሬን ጦርነት ከሰባት ሺህ በላይ ሀሰተኛ ምስሎችን አስራጭቷል ብሏል።

ሩሲያ ሀሰተኛ ምስሎችን ማስተላለፍ በህግ የደነገገች ሲሆን ጎግል ኩባንያ ቅጣቱ የተላለፈበት ሀሰተኛ ምስል በማስተላለፍ እና ያስተላለፋቸውን ምስሎች ከድህረ ገጹ ላይ ለማጥፋት ፈቃደኛ ባለመሆኑ እንደሆነ ተጠቅሷል።

ሩሲያ ባሳለፍነው ታህሳስ ወር ላይ ይሄው ጎግል ኩባንያ ሆን ብሎ ሀሰተኛ ምስሎችን አሰራጭቷል በሚል 98 ቢሊዮን ዶላር እንዲከፍል ውሳኔ ማስተላለፏ ይታወሳል።

የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎም በሁለቱ ሀገራት እና በተቀረው ዓለም ላይ በርካታ ለውጦች የተመዘገቡ ሲሆን ከ15 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

ይህ በዚህ እንዳለም የዓለም ምግብ እና ነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል።

በጦርነቱ ምክንያት በተከሰተው የዋጋ ግሽበት ምክንያትም በበርካታ ሀገራት ኑሮ ተወደደብን በሚል መንግስታት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እንዲደርጉ በሰላማዊ ሰልፍ በመጠየቅ ላይ ናቸው።

አምስት ወራት የሆነው ይህ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት አሁንም የቀጠለ ሲሆን አሜሪካንን ጨምሮ ሌሎች የምዕራባዊያን ሀገራት ዩክሬንን በጦር መሳሪያ እና ሌሎች ወታደራዊ ድጋፎችን በመስጠት ላይ ናቸው።

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬን ጦርነት በኋላ ከቀድሞ ሶቬት ሀገራት ውጭ ባደረጉት የመጀመሪያ ጉዞ ኢራንን ጎበኙ

ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬን ጦርነት በኋላ ከቀድሞ ሶቬት ሀገራት ውጭ ባደረጉት የመጀመሪያ ጉዞ ኢራንን ጎበኙ

ፑቲን ከቱርኩ ፕሬዝደንት ኦርዶጋን ጋርም በኢራን ይመክሯሉ
ከኢራን ጋር “በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አቋማችን ተቀራራቢ ወይም ተመሳሳይ ነው” ብለዋል የፑቲን የውጭ ፖሊሲ አማካሪ

ፕሬዝዳንት ፑቲን ከዩክሬን ጦርነት በኋላ ከቀድሞ የሶቬት ሀገራት ውጭ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢራንን በመጎብኘት የኢራኑን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሚኒን አግኝተዋል፡፡

ፑቲን ፊታቸውን ወደ ህንድ፣ ኢራን እና ቻይና በማዞር የምእራባውያን ሀገራት ሩሲያን በኢኮኖሚ የማሽመድመድ እቅድ ላይ ጥላ ማጥላቱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ሩሲያ በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” መጀመሯን ተከትሎ ይህን የሚቃወሙት ምእራባውያን ሀገራት በታሪክ ከባድ ነው የተባለውን ማእቀብ በሩሲያ ላይ ጥለዋል፤ እየጣሉም ነው፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸው በሳኡዲ አረቢያ ካጠናቀቁ ሶስት ቀን በኋላ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን ከኢራኑ ጠቅላይ መሪ እና በፈረንጆቹ በ1989 ወደ ስልጣን ከመጡት አሊ ካሚኒ ጋር ለመወያየት ኢራን ደርሰዋል፡፡

“ከካሜኔ ጋር ያለው ግንኙነት በጣም አስፈላጊ ነው” ሲሉ የፑቲን የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ በሞስኮ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ “በሁለትዮሽ እና በአለምአቀፍ አጀንዳዎች ላይ በጣም አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ እምነት የሚጣልበት ውይይት በመካከላቸው ተፈጥሯል” ብለዋል አማካሪው፡፡

ከኢራን ጋር “በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አቋማችን ተቀራራቢ ወይም ተመሳሳይ ነው።” ብለዋል የፑቲን የውጭ ፖሊሲ አማካሪ

የፑቲን የኢራን ጉብኝት ከቱርክ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር የሚገጣጠም ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ቴህራን ላይ በመገናኘት የዩክሬን የጥቁር ባህር እህል ወደ ውጭ መላክን ለማስቀጠል ያለመ ስምምነት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ቱርክ በሰሜን ሶሪያ ወታደራዊ ዘመቻ የመክፈት እቅድ አላት፤ ነገርግን ሩሲያ ይህን ትቃወማለች፡፡ ሁለቱ መሪዎች በዚህ ጉዳይም ይመክራሉ ተብሏል፡፡

ሩሲያ እና ኢራን ምእራባውያን ሀገራት የሶሪያ የእርስበእርስ ጦርነት ከተጀመረ ከፈረንጆቹ 2011 ጀምሮ ከስልጣን እንዲወገድ የሚፈልጉት የሶሪያ መሪ በሽር አላሳድን ይደግፋሉ፡፡

News today, Politics

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የምዕራባውያንን ማዕቀብና የሀገራቸውን ዕድገት እንደሚያደናቅፍ ተናገሩ

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የምዕራባውያንን ማዕቀብና የሀገራቸውን ዕድገት እንደሚያደናቅፍ ተናገሩ

የሩሲያ የቴክኖሎጂ ልማት በምዕራባውያን ማዕቀብ እንደማይቆም የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አስታወቁ።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዛሬ ባደረጉት ንግግር የምዕራባውያንን ማዕቀብና የሀገራቸውን ዕድገት የተመለከቱ ጉዳዮችን አንስተዋል።

ፑቲን በንግግራቸውም የሞስኮ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዕድገት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

ፑቲን በሩሲያ ያለው የድህነት ሁኔታ እየቀነሰ እንደሆነም ነው በንግግራቸው ያነሱት። የሀገሪቱ የቴክኖሎጂ ዕድገት ምዕራባውያን ማዕቀብ ስለጣሉ እንደማጠይቆምም ነው የገለጹት።

ምንም እንኳን ምዕራባውያን ማዕቀብ ቢጥሉም የሞስኮ እድገት ግን ቀጣይነቱ አይቀሬ እንደሆነ ነው ያነሱት፡፡ የሩሲያ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አሁን ባለው መልኩ እንደሚቀጥልም ፑቲን ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ዛሬ በስትራቴጂክ ልማት ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ስለኮሮና ቫይረስ ማንሳታቸውም ተጠቅሷል፡፡ ምንም እንኳን ዓለም አቀፍ ጫና ቢኖርም ኮሮና ካስከተለው ችግር ለመውጣት ሀገራቸው ጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኗን ጠቅሰዋል፡፡

አሁን ላይ በሩሲያ ያለው የድህነት ደረጃ እንጅ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱንም ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም በሀገሪቱ የሞት ምጣኔ መቀነስ ማሳየቱን ጠቅሰዋል፡፡

የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን የሆነው ሩሲያ ቱዴይ እስካሁን ፕሬዝዳንቱ ተናገሯቸው ካላቸው ነጥቦች መካከል የዩክሬን ጉዳይ አልተገለጸም፡፡

ባለሙያዎች እንዳሉት በኢንዱስትሪዎች ላይ ያለው ማዕቀብ ከሶስት እስከ አምስት ዓመታት ባሉት ጊዜያት እንደሚቀለበስ ገልጸዋልም ተብሏል፡፡

News today, Politics

በሶማሊያ የመንገደኞች አውሮፕላን በማረፍ ላይ እያለ ባጋጠመው አደጋ ተገለበጠ፡፡

በሶማሊያ የመንገደኞች አውሮፕላን በማረፍ ላይ እያለ ባጋጠመው አደጋ ተገለበጠ፡፡

ሰበር አውሮፕላኑ በሞቃዲሾ አውሮፕላን ማረፊያ እያረፈ ባለበት ነው የመገልበጥ አደጋ ያጋጠመው

በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ አንድ የመንገደኞች አውሮፕላን የመገልበጥ አደጋ ማስተናገዱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

አደጋው ያጠመው የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በማጓጓዝ ላይ የነበረ አውሮፕላን ሲሆን 33 መንገደኞችን ከባይደዋ ወደ ሀገሪቱ መዲና ሞቃዲሾ በማጓጓዝ ላይ ነበር፡፡

ይህ የመንገደኞች አውሮፕላን በሞቃዲሾ አውሮፕላን ማረፊያ በማረፍ ላይ ሳለ ባጋጠመው ግጭት ምክንያት የተገለበጠ ሲሆን በሁሉም ተሳፋሪዎች ላይ ያጋጠመ የጎላ ጉዳት እንደሌለ የሶማሊያ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡

አውሮፕላኑ ጁባ አየር መንገድ እንደሚባል የተገለጸ ሲሆን ስለ አውሮፕላኑ አደጋ መንስኤ እስካሁን ምንም የወጣ መረጃ የለም፡፡

በሶማሊያ የአውሮፕላን አደጋ የተለመደ ሲሆን፤ ወደ ሞቃዲሾ የሚበሩ የተለያዩ ሀገራት አውሮፕላኖች ተደጋጋሚ የመከስከስ አደጋዎች ያጋጥማሉ፡፡

የአልሻባብ የሽብር ጥቃት ባዳከማት ሶማሊያ የአውሮፕላን በረራ ተመራጭ የትራንስፖርት መንገድ ቢሆንም ተደጋጋሚ የአውሮፕላን አደጋዎች መከሰት ሌላኛው የተጓዦች ስጋት ሆኗል።

ከዚህ በፊት የኬንያ የግል የመንገደኞች እና የጭነት አውሮፕላኖች በተደጋጋሚ አደጋዎችን በሶማሊያ ያስተናገዱ ሲሆን ከጥቂት አየር መንገዶች በስተቀር በርካታ አየር መንገዶች ወደ ሶማሊያ የሚያደርጉትን በረራዎች አቋርጠዋል።

News today, Politics

በሱዳን ብሉናይል ግዛት በተፈጠረ ግጭት ከ65 በላይ ሰዎች ተገደሉ፡፡

በሱዳን ብሉናይል ግዛት በተፈጠረ ግጭት ከ65 በላይ ሰዎች ተገደሉ፡፡

 በሱዳን ብሉናይል ተብሎ በሚጠራው ግዛት በበርቲ እና ሀውሳ ጎሳዎች መበካከል በተፈጠረ የጎሳ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ65 በላይ የደረሰ ሲሆን ከ200 በላይ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከሰዎች መጎዳት ባለፈም ከ16 በላይ የንግድ ሱቆች በዚሁ የጎሳ ግጭት ምክንያት ሲወድሙ ሌሎች መሰረተ ልማቶችም እንደወደሙ ተገልጿል፡፡

ብሉናይል ግዛት ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚዋሰኑ አካባቢዎች ያለ የሀገሪቱ ክፍል ሲሆን ከዚህ በፊት መሰል አደጋዎች ይከሰቱበታል፡፡

በደቡብ ሱዳንም ተመሳሳይ የጎሳ ግጭት ተከስቶ 65 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ከ150 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆስለው ነበር፡፡

የሱዳን ጤና ሚኒስትር ጀማል ናስር ኤል ሳያድ እንዳሉት ባሳለፍነው ቅዳሜ በተከሰተው በዚህ አደጋ የተጎዱ ሰዎች አብዛኞቹ ወጣቶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ግጭቱ አሁንም የቀጠለ ሲሆን ዛሬ ጠዋት ላይ በብሉ ናይል ግዛት መቀመጫ ዳማዚን ከተማ ላይ በተከሰተው እና በቀጠለው በዚሁ አደጋ ከ16 በላይ የንግድ መገበያያዎች መውደማቸው ተገልጿል፡፡

ግጭቱ አሁንም የቀጠለ ሲሆን የሟቾች እና ተጎጂዎች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የግዛቲቱ ባለስልጣናት የተናገሩ ሲሆን ተጨማሪ ወታደሮች እንዲገቡላቸው ጠይቀዋል፡፡

በአል ሩሳሪስ ሆስፒታል ያለው የህክምና ቁሳቁሶች እያለቁ መሆናቸውን የተናገሩት ባለስልጣናቱ በግጭቱ ቆስለው ወደ ህክምና ተቋማት የሚመጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ እየጨመረ መሆኑንም አክለዋል፡፡

የግዛቲት ባለስልጣናት በብሉ ናይል ዋና ዋና ከተሞች ለአንድ ወር የሚቆይ የሰዓት እላፊ ቢጥሉም በርካቶች አሁንም ግጭቱ ሊቀጥል እንደሚችል ስጋት እንዳላቸው ተገልጿል፡፡

News today, Politics

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን ጀመሩ
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አቀባበል ተደርጎላቸዋል
አረብ ኢሚሬትስና ፈረንሳይ በኢነርጂና በትራንስፖርት መስኮች እንደሚፈራራሙ ይጠበቃል

የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት መሀመድ ቢን ዛይድ የፈረንሳይ ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸውን በይፋ ጀምረዋል።

በትናንትናው ለት ምሽት ፈረንሳይ ፓሪስ የደረሱት
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ ዛሬ በፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑዔል ማክሮን በኤሊሴ ቤተ መንግስት ይፋዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።0
ፕሬዝዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በኤሊሴ ቤተመንግስት ከፈረንሳይ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተገናኝተው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የፈረንሳይ ባለስልጣናትን ያነጋግራ።

ሼህ መሀመድ ቢን ዛይድ አልነሃያን በፈረንሳይ ቆይታቸው በኢነርጅ እና በትራንስፖርት መስኮች እንደሚፈራራሙ ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

የፈረንሳዩ ጉብኝት ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ በኋላ ያደረጉት የመጀመሪያ አለምአቀፍ ጉብኝት ነው፡፡

News today, Politics

ባይደን በጉብኝታቸው ወቅት ኢራን ኒውከሌር እንዳይኖራት መስራት የሚለው ጉዳይ አንደኛው አጀንዳ ነበር

ባይደን በጉብኝታቸው ወቅት ኢራን ኒውከሌር እንዳይኖራት መስራት የሚለው ጉዳይ አንደኛው አጀንዳ ነበር

ኢራን አሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝት ወቅት ውጥረት ለመፍጠር የኢራን ፍራቻን ወይም ኢራኖፎቢያን ተጠቅማች ስትል ከሳለች፡፡

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እሁድ እለት ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸው ወቅት ያቀረቡትን ተከታታይ ውንጀላዎች ውድቅ ማድረጉን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡ ኢራን አሜሪካ “ኢራኖፎቢያ”ን ቀጣናዊ ውጥረት ለመፍጠር ተጠቅማለች የሚል ክስ አቅርባለች፡፡

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ናስር ካናኒ የባይደን ጉብኝት አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ “አሜሪካ በድጋሚ በቀጠናው ውጥረት እና ቀውስ ለመፍጠር ፈልጋለች”፡፡

 ባይደን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ባደረጉት ጉብኝት ኢራን በተግባሯ ቀጣናውን እንዳይረጋጋ እያደረገች ነው የሚል ክስ ሰንዝረዋል፤ አሜሪካ “ቴህራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳታገኝ” እንደሚያደርጉ፣ ተናግረዋል፡፡

በመግለጫው ላይ ካናኒ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መግለጫ መሠረተ ቢስ እና በቀጠናው ውስጥ ውጥረቶችን ከማስነሳት እና ከመፍጠር ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል ።

ቃል አቀባዩ አሜሪካ በክልሉ ሀገራት የውስጥ ጉዳይ ላይ በምታደርገው ተከታታይ ጣልቃ ገብነት፣ ተደጋጋሚ ወታደራዊ ወረራ እና ከፍተኛ የጦር መሳሪያ ሽያጭ በቀጣናው ውጥረት እና ቀውስ ለመፍጠር እየሞከረች ነው በማለት አውግዘዋል።

በመግለጫው ባለፉት አስርት አመታት የፍልስጤምን ህዝብ መብት ሲጣስ አሜሪካ ለእስራኤል የምታደርገውን “ጭፍን እና ያልተገደበ ድጋፍ” አውግዘዋል።

ካናኒ እንደተናገሩት ኢራን የኒውክሌር ቴክኖሎጅን አለምአቀፍ ህግን መሰረት ባደረገ መልኩ እንደምትጠቀም እና ማእቀቡ እንዲነሳ እንደምትጥር ገልጸዋል፡፡

ወደ ኒውክሌር መርሃ ግብሩ ስንመጣ ካናኒ የኢራንን የኒውክሌር ቴክኖሎጂን በሰላማዊ መንገድ የመጠቀም ስትራቴጂካዊ ፖሊሲ በአለምአቀፍ የህግ ማዕቀፍ ውስጥ ደግሟል እና ኢራን ማዕቀቡን ለማንሳት ድርድርዋን እንደምትቀጥል ተናግሯል።

ኢራን ለአካባቢው ፀጥታ፣ ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ገንቢ ጥረቶችን ለማቅረብ ከአካባቢው ጎረቤቶች ጋር የሚደረገውን ውይይት እና ትብብር እንደምትቀበል በመግለጫው ተጠቅሷል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከሰሞኑ እስራኤል እና ሳኡዲ አረቢያን ጨምሮ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ባይደን በጉብኝታቸው ወቅት ኢራን ኒውከሌር እንዳይኖራት መስራት የሚለው ጉዳይ አንደኛው አጀንዳ ነበር፡፡

News today, Politics

ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቷን በቀን ወደ 13 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ

ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቷን በቀን ወደ 13 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ መወሰኗን አስታወቀች

ትናንት በተካሄደው የገልፍ ሀገራት-አሜሪካ የልማትና ደህንነት ጉባዔ ላይ ትኩረት ከነበሩት ውስጥ አንዱ የነዳጅ ጉዳይ ነበር።

የሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን፤ “ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ያገናዘበ ሚዛናዊ አካሄድ መከተልን ይጠይቃል” ብለዋል።

ከነዳጅ ጋር ተያይዞ ሊያጋጥም የሚችል እጥረትን ለመቅረፍም ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቷን በቀን ወደ 13 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ መወሰኗንም አስታውቀዋል።

News today

ዓለማችን በቀጣይ በሁለት ወይም ሶስት ልዕለ ሀያላን ሀገራት የመመራት እድሏ ከፍተኛ ነው ተብሏል

ዓለማችን በቀጣይ በሁለት ወይም ሶስት ልዕለ ሀያላን ሀገራት የመመራት እድሏ ከፍተኛ ነው ተብሏል

የዩክሬን ጦርነት የምዕራባዊያን የበላይነት እያበቃ ለመሆኑ ማሳያ መሆኑን ቶኒ ብሌር ተናገሩ፡፡

የቀድሞው የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶኒ ብሌር እንዳሉት የዩክሬን ጦርነት የምዕራባዊያን የበላይነት እያበቃ መምጣቱን ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

ጦርነቱ የምዕራባዊያን የበላይነት እያበቃ መሆኑን እና የቻይና ተጽዕኖ እያደገ ለመምጣቱ ማሳያ መሆኑንም ብሌር በለንደን በተዘጋጀ ሴሚናር ላይ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ምዕራባዊያን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ከሶቪየት ህብረት ጋር ተጋርጦባቸው የነበረውን የበላይነት ማሸነፍ ቢችሉም አሁን ግን በታሪካዊ እጥፋት ላይ መሆናቸውን ብሌር አክለዋል፡፡

አሁን የምዕራባዊያን የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ የበላይነት መጨረሻ ላይ እንገኛለን ያሉት ብሌር ዓለም በቀጣይ ቢያንስ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ ባሉ ልዕለ ሀያላን ሀገራት እጅ ስር መውደቋ አይቀርም ብለዋል፡፡

ይህም ዓለማችን በሩሲያ ሳይሆን በቻይና የበላይነት ልትምራ እንደምትችልም ቶኒ ብሌር በሴሚናሩ ላይ ተናግረዋል ተብሏል፡፡

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦርን ወይም ኔቶን በአባልነት እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ወደ ጦርነት ካመሩ 145ኛ ቀናቸው ላይ ያሉ ሲሆን ከ15 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል፡፡

በአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት የሚመራው የምዕራባዊያን ቡድን ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ከመርዳት ጀምሮ ከ6 ሺህ በላይ ማዕቀቦችን በሩሲያ ላይ ጥለዋል፡፡

ሩሲያ በበኩሏ ሰፊ ሸማች ካላቸው ቻይና እና ህንድ ጋር ንግዷን በማሳደግ ላይ ስትሆን በተለይ የቻይና ድጋፍ ከፍተኛ እንደሆነ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

News today, Politics

የኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት ለ1443 የሂጅራ ስኬት ለሳውዲ ንጉስ የደስታ መልእት አስተላልፈዋል

የኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት ለ1443 የሂጅራ ስኬት ለሳውዲ ንጉስ የደስታ መልእት አስተላልፈዋል

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ ሀገራቸው በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና መረጋጋት ላይ ዋነኛ አጋር ሆና እንደምተጥል አረጋገጡ።

የገልፍ ሀገራት-አሜሪካ የልማትና ደህንነት ጉባዔ በዛሬው እለት በሳዑዲ አረቢያ ጄዳህ ተካሂዷል።

በጉባዔው ላይ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፣ የሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን እና የአረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት መሃመድ ቢን ዛይድን ጨምሮ ሌሎችም የገልፍ ሀገራት መሪዎች ተሳትፈዋል።

በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና ለሩሲያ፣ ለቻይናና ለኢራን ክፍተት አንሰጥም- ፕሬዝዳንት ባይደን
የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ መሃመድ ቢን በጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት፤ ሀገራቸው በቀጠናው ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ለማሳደግ እንዲሁም አለም አቀፋዊ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እና የጋራ ችግሮችን ለመጋፈጥ ፍላጎት እንዳላት አረጋግጠዋል።

አረብ ኢሚሬትስ በአለም አቀፍ ግንኙነት ላይ የምትከተለው ፖሊሲ በሚዛናዊነት ላይ የተመሰረተ እና ከአለም ሀገራት ጋር የጋራ የጥቅም መሰረትን በማስፋት ለሀገራዊ ልማትና ሰላምና መረጋጋት ግቦችን ማስፈን መሆኑን አስረድተዋል።

ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ እንዳሉት “በቀጠናችንም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ትልቅነት ለማንም የተሰወረ አይደለም” ያሉ ሲሆን፤ “እንዚህን ተግዳሮቶች ለመቋቋም እና የህዝቦቻችንን ምኞት ለማሳካት የጋራ ጥረቶችን ማጠናከር ይጠይቃል” ብለዋል።

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ፕሬዝዳንት አክለውም ለ1443 የሂጅራ ስኬት ለሳዑዲ አረቢያው ንጉስ ሳልማን ቢን አብዱላዚዝ አል ሳኡድ የደስታ መልእክት አስተላልፈዋል።

ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን፤ “ይህ የመሪዎች ጉባኤ ሀገሮቻችንን ከአሜሪካ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።

“ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ያገናዘበ ሚዛናዊ አካሄድ መከተልን ይጠይቃል” ያሉት መሃመድ ቢን ሰልማን፤ የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮቶች ለመቋቋም የካርበን ልቀተን መቀነስ ልቀትን መሰረት ያደረገ አሰራር መከተላቸውን አስታውቀዋል።

News today, Politics

ጆ ባይደን በሳኡዲ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የመካከለኛው ምስራቅ የባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤቷ አገር ሳኡዲ አረቢያ ገብተዋል። ጆ ምናልባት በዘመነ አሜሪካ የስልጣን ጊዜያቸው ነዳጅ ልመና የመጡ መሪ ያደርጋቸዋል። በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ሳኡዲ ከአፍሪካ አገሮች ጋር ተመሳሳይ ያለው አቋም የያዘች አገር ናት። የራሳችንን ጥቅም መሰረት አድርገን የምንራመድ እንጅ የማንንም ይሉይታ የምንቀበል አይደለንም ያለች አገር ናት ሳኡዲ። ሳኡዲ እንደበፈቱ አይነት
ለነ አሜሪካ የምትጨነቅ አገር አይደለችም።

News today, Politics

ኢትዮጵያዊነት የወለደው የታማኝነት እዳ

ኢትዮጵያዊነት የወለደው የታማኝነት እዳ
ለ40 አመት ትልቁን የመዲናን መስጊድ ሲጠብቁ የነበሩት ሸህ መሀመድ ሀቢብ አል አፋር መሞታቸውን የሳኡዲ መንግስት ዓሳውቋል።

በአረቡ አለም ውስጥ ኢትዮጵያዊነት
የታማኝነት እዳ ነው። በማንኛውም መንገድ ስማችን ሊጎድፍ ይችላል። በድህነታችን ላይ ሊሳለቁብን ይችላሉ። ሴት እህቶቻችን ለባርነት በመላካችን ሊንቁን ይችላሉ። በአንዳንድ አጥፊዎች ሊያሙን ይችላሉ። እነሱም የሚያምኑት አንድ የማይሸሸግ ነገር ግን አለን

ሙሉ ታሪካቸውን ሊንኩን ከፍታችሁ አንብቡ

ሱሌማን አብደላ

News today, Politics

ሰሜን ኮሪያ እውቅና ሰጠች

ሰሜን ኮሪያ በሩሲያ ለሚደገፉት ተገንጣይ ግዛቶች እውቅና ሰጠች

እርምጃው ለሁለቱ በሩሲያ ለሚደገፉ ተገንጣይ ግዛቶች ማለትም ለዶንቴስክን እና ለሉሃንስክ ግዛቶች የሀገርነት እውቅና በመስጠት ከሩሲያ እና ሶሪያ ቀጥሎ ሰሜን ኮሪያን 3ኛ ሀገር ያደርጋታል፡፡

News today, Politics

ጆ-ባይደን የእስራኤል እና የፍልስጤም ግጭትን የማርገብ ጉዳይ

ጆ-ባይደን የእስራኤል እና የፍልስጤም ግጭትን የማርገብ ጉዳይ ላይ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ-ባይደን የእስራኤል ጉብኝታቸውን ዛሬ ጀምረዋል።

ጆ ባይደን በአውሮፕላን ማረፊያ በተሰናዳው መድረክ ባደረጉት ንግግር “በእኔ እይታ አዲስ ባይሆንም የእስራኤላውያንም ሆነ የፍልጤማውያን የእኩልነት ነፃነት፣ ብልጽግና እና ዲሞክራሲ የወደፊት እጣ ፈንታ ለማረጋገጥ በሚጠቅመው ጉዳይ ላይ እንወያያለን” ብለዋል።

News today, Politics

ኢራን አዳዲስ ዴሮኖቿን ለሩሲያ የመስጠት ፍላጎት አላት ስትል አሜሪካ ከሰሰች

ምዕራባውያን ስጋት የሆኑት ሩሲያ እና ኢራን

ኢራን ለሩሲያ ድሮኖችን ለመስጠት እቅድ አላት ስትል አሜሪካ አስጠነቀቀች

ኢራን በጦርነት ላይ ላለችው ሩሲያ ሰው አልባ የጦር አውሮፕላኖችን (ድሮን) ልትሰጥ ነው ሲሉ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን አስጠነቀቁ።

ኢራን ሩሲያ በዩክሬን ምድር ለምታደርገው ወታደራዊ ዘመቻ ድጋፏን ለሩሲያ ስትሰጥ ቆይታለች ያሉት ባለስልጣኑ አሁን ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) ለሩሲያ ልትሰጥ መሆኗን ደርሰንበታልም ብለዋል።
የKe alemi zuriya-ቤተሰብ ይሁኑ

👉የke alemi zuriya ሌሎች አድራሻዎች
instag:https://instagram.com/kealemizuriya
twitter:https://twitter.com/KeAlemiZuriya
YouTube:https://bit.ly/kealemizuriya
Telegram:https://t.me/KeAlemiZuriya
website:https://kealemizuriya.data.blog/
ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን

News today, Politics

ፑቲን ኢራን ሊጎበኙ ነው

ፑቲን ኢራንን ሊጎበኙ ነው

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ኢራንን ሊጎበኙ ነው።
ፑቲን ቴህራንን የሚጎበኙት በቀጣይ ሳምንት እንደሆነ የኢራን ፓርላማ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ተናግረዋል።

የKe alemi zuriya-ቤተሰብ ይሁኑ
👉የke alemi zuriya ሌሎች አድራሻዎች
instag:https://instagram.com/kealemizuriya
twitter:https://twitter.com/KeAlemiZuriya
YouTube:https://bit.ly/kealemizuriya
Telegram:https://t.me/KeAlemiZuriya
website:https://kealemizuriya.data.blog/
  ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን

News today, Politics

የባይደን የሳኡዲ ጉበኝት

ፕሬዝዳንት ባይደን በሳኡዲ አረቢያ የጉብኝት እቅዳቸው ላይ የተነሳውን ትችት ተከላከሉ

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን በሳኡዲ አረቢያ የጉዞ እቅዳቸው ላይ የተነሳውን ትችት ተከላክለዋል፤ በሳኡዲ ቆይታቸው የመብት ጉዳይ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል።

ንጉስ ሳለማን በፈረንጆቹ 2018 ከተገደለው የዋሽንግቸን ፖስቱ ጋዜጠኛ ጀማል ካሾግጂ ግድያ አሉበት ተብሎ ይታመናል።

News today

“ሄሮን ቲፒ” አደገኛው የእስራኤል የውጊያ ድሮን

“ሄሮን ቲፒ” አደገኛው የእስራኤል የውጊያ ድሮን ምን የተለየ ያደርገዋል…ʔ
“ሄሮን ቲፒ (Heron TP)” ድሮን የእስራኤል አየር ኃይል ከታጠቃቸው አደገኛ የአውደ ውጊያ መሳሪያዎች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው።
ሄሮን ቲፒ ድሮን በየትኛውም አይነት የአየር ፀባይ ለ30 ሰዓታት ያክል መስራ ይችላ የተባለ ሲሆን፤ በሰዓት 370 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መጓዝ እንደሚችልም ተነግሯል።
ድሮኑ ለተልዕኮ በሚሰማራበት ወቅት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከባህር ጠለል በላይእስከ 45 ሺህ ጫማ ድረስ ከፍ ብሎ በመብረር ከራዳር እይታ ውጪ ጥቃት መሰንዘር ይችላል።

News today, Politics

የአለማችንን ልዕል ሀያል ወንዝ ይዞ በጓሮ አትክልት መብሸቅ እራስን ማሳነስ ነው።

የአለማችንን ልዕል ሀያል ወንዝ ይዞ በጓሮ አትክልት መብሸቅ እራስን ማሳነስ ነው።
.
ባለፈው ሳምንት በሳኡዲ የሪያድ አምባሳደር ሌንጮ ባቲና አብረዋቸው ያሉ ዲፕሎማቶች ከሳኡዲ የውጭ
ኢንቨስትመንት ክፍል አመራሮች ጋር ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን የኢንቨስትመንት አማራጮች በተመለከተ ምክክር አድርገው ነበር። ታዲያ እኒህ የሳኡዲ ባለስልጣናት እናተኮ አላወቃችሁበትም እንጅ አላህ
ሁሉንም ነገር አሟልቶ ሰቷችሁ ነበር፣ በቀላሉ የከብት መኖ ብቻ በመሸጥ ሀብታ ትሆናለችሁ ሌላውን ተውትና ግን አላወቃችሁበትም አሉ።
.
ኢትዮጵያ ስትባል መናጢ ደሀ ችጋራም ምንም የለሌላት ምድረ በዳ የምትመስለው ብዙ ኢትዮጵያዊ አለ። አገራቸውን በመሳደብ የተጠመዱም ፖለቲከኞች አሉ። ውጩ አለም ግን ምነው የኛ ሆና በሆን እያለ እንዲህ ይጎመጃል። ታዲያ ይህ ስሜት ያላደረበት የአገሬ ፖለቲከኛ አሁንም ድረስ የኢትዮጵያን ገናናነት ከማሰብ ይልቅ ሰፈሬ ትቅደም እያለ ይዘምራል። ባህር አቋርጦ፣ አህጉር የነቀነቀው ቼ ጉቬራ በተወለደባት አለም አፍሪካ ውስጥ ግን
እንዲህ አይነት ፖለቲከኛ ተወልዷል

News today

የኪምን ሙሉ መረጃ ይዞ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት

የኪምን ሙሉ መረጃ ይዞ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ለመጣ ሰው በዚህ ምድር ላይ የፈለገውን ሁሉ እንዲያገኝ አደርገዋለሁ

(አሜሪካ )

አሜሪካ እጅግ የምትፈልገው የምድራችን ሰው ኪም ጆንግ ኡን ነው። ClA የዚህን መሪ ሽንት ለማግኘት መሮጥ ከጀመረ ከአስር አመት በላይ ሆኖታል። በአስር አመት ስራው ምንም ያመጣው ውጤት የለም። ደቡብ ኮሪያ የሱን ሽንት በጨረር ውስጥ ለማስገባት ከአሜሪካ ጋር የሰራችው መሳሪያ እስካሁን ድረስ ውጤት አላመጣም። በኪም የመዝናኛ ገንዳ ውስጥ ለመሰለል የተላኩ ጭልፊቶችና ዶኒህ ተሳቢ ነባሪዎች እስካሁን አልተመለሱም።

News today

ፕረዚዳንት ፑቲን ለሁሉም ሀክሬናዊ የሩሲያ ፓስፖርት እንዲሰጣቸው አዘዙ

ፕሬዝዳንት ፑቲን ለሁሉም የዩክሬን ዜጎች የሩሲያ ፓስፖርት እንዲሰጣቸው አወጁ

ሩሲያ ከዚህ በፊት ለዶምብአስና ሉሃንስክ ግዛት ነዋሪዎች የሩሲያ ፓስፖርትን ስትሰጥ ነበር። የሩሲያ- ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ አምስተኛ ወሩን ሊይዝ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል።

News today

በሽንዞ አቤ ላይ ጥይት ተኩሶ የገደለው ግለሰብ በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተባለ

በሽንዞ አቤ ላይ ጥይት ተኩሶ የገደለው ግለሰብ በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተባለ

የቀድሞው የጃፓን ጠቅላይ ሚንስትር ሽንዞ አቤ በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ናራ ተብላ በምትጠራ ከተማ በተሰናዳ አንድ የፖለቲካ መድረክ ላይ ከሰዓታት በፊት ንግግር በማድረግ ላይ እያሉ ከኋላ በተተኮሰባቸው ጥይት ተመትተው ህክምና እያሉ ነበር ህይወታቸው ያለፈው።

በሽንዞ አቤ ላይ ጥይት የተኮሰው ግለሰብም በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት መሆኑም ተነግሯል።

News today

ሩሲያ በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለች

ሩሲያ በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አለች

ሩሲያ በስንዴ እና በሌሎችም የእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ገለጸች።
ሩሲያ ይህን የገለጸችው በኢንዶኔዥያ መካሄድ በጀመረው የቡድን 20 (G20) አባል ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ነው።
በስብሰባው የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሃገራቸው በእህል ምርቶች ጉዳይ ላይ ከዩክሬን እና ቱርክ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
ቱርክ ከሰሞኑ ከዩክሬን የተሰረቁ የእህል ምርቶችን የጫኑ ናቸው ያለቻቸውን የሩሲያ የጭነት መርከቦች መያዟ ይታወሳል።

News today

የነዳጅ ላኪ ሀገራት ዋና ፀሀፊ አረፋ

የነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) ዋና ጸሐፊ ህይወታቸው አለፈ
የነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) ዋና ጸሐፊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ናይጄሪያዊው ዋና ጸሐፊ ሞሐመድ ባርኪንዶ በ63 ዓመታቸው ነው ህይወታቸው ያለፈው። የናይጄሪያ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ሃላፊን ጨምሮ ሁለት የኦፔክ ምንጮች የዋና ጸሐፊውን ማረፍ አስታውቀዋል።

News today

የአውሮፓ ህብረት ለ ኢትዮጵያዊ 81m ዩሮ

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ81 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ሊያደርግ ነው

የህብረቱ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል ድጋፉን ለማድረግ የሚያስችሉ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል፡፡
ቻርለስ ሚሼል ይህን ይፋ ያደረጉት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ ነው፡፡

News today

Ethiopia | አርቲስት ሀናን ታሪክ በዛሬው ዕለት የ”ኢንጂ ፈርኒቸር” ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተፈራርማለች

ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተፈራርማለች

ቡሩል ትሬዲንግ ኃ / የተ / የግ / ኩባንያ ( Burul Trading PL.C. ) እ.ኤ.አ መስከረም 2016 የተመሰረተ አስመጪና ላኪ ኩባንያ ሲሆን ፤ ኩባንያው “ ኢንጂ ፈርኒቸር ”የሚል የብራንድ ስያሜ በመያዝ ! “ ይታሽ ሞቢሊያ ” የተባለው እድሜ ጠገብና ግዙፍ የቱርክ ፈርኒቸር ኩባንያ ወኪል በመሆን የሚሰራ ነው ፡፡

በተጨማሪም ኩባኒያው ባለፉት ስድስት ዓመታት ባደረገው ጥረት ፤ ኢንጂ ፈርኒቸር በአሁነ ጊዜ ለሦስት የተለያዩ ታዋቂ የቱርክ ፈርኒቸር ኩባንያዎች “ የምስራቅ አፍሪካ ገበያ ብቸኛ ወኪል ” በመሆን እየሰራ ይገኛል ።

የኢንጂ ፈርኒቸር ዋና መሥሪያ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፤ በሴንቸሪ ሞል አካባቢ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም አዲስ አበባ ውስጥ ሴንቸሪ ሞል ሦስተኛ ፎቅ እና ግራውንድ ፎቅ ላይ ሁለት ሾው ሩም በመክፈት ለደንበኞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው።

ኢንጂ ፈርኒቸር የሚለውን የብራንድ ስም የመረጠው ፤ በሾው ሩማቸው ውስጥ የሚገኙትንና ከተለመደው ወጣ ያሉ ቅንጡ ውብና ማራኪ ፈርኒቸሮች የሚወክል ስያሜ በመሆኑ ነው።

ኢንጂ ፈርኒቸር እስካሁንም በልዩ ትእዛዝና በከፍተኛ ጥራት የሚመረቱ ፤ እጅግ ቅንጡ ፤ ከተለመደው ወጣ ያሉ ቅንጡ ፤ ውብና ማራኪ ፈርኒቸሮች የሚወክል ስያሜ በመሆኑ ነው ፡፡

ዘመናዊ የነገውን ፋሽን መሰረት ያደረጉ ፤ አዳዲስና ብራንድ የቤትና የቢሮ ፈርኒቸሮችን በከፍተኛ ወጪ በማስመጣት ፤ የውስጥ ዲዛይን ማማከርን ጨምሮ የተገዙ ፈርኒቸሮችን ደንበኞች ባሉበት ቦታ የማድረስና የማስረከብ አገልግሎቶችን በመስጠት ረገድም ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ግንባር ቀደምና ታዋቂ ኩባንያ ነው ፡፡

ኩባንያው አዲስ አበባ ከከፈተው የምስራቅ አፍሪካ ወኪል ቢሮ በተጨማሪ ፤ በናይኖቢ ፤ ኬንያ ሌላ አስመጪና ላኪ ኩባንያ አቋቁሞ እየሰራ ሲሆን ፤ በናይሮቢ የመጀመሪያውን ሾው ሩም እ.ኤ.አ. መስከረም 2022 ለመክፈት የሚያስችለውን የዝግጅት ሂደት አጠናቅቋል ፡፡

እንዲሁም ፤ በደንበኞቹ ጥያቄ መሰረት ፤ የሆቴልና የአፓርትመንት ፕሮጄክት ቅንጡ ፈርኒቸሮችን በማስመጣት በኬንያ ፤ በደቡብ ሱዳን ፤ በናይጄሪያና በታንዛኒያ ለሚገኙ ደንበኞቹ በማቅረብ ! ለአስመጪነት ስራው የሚያውለው ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጭምር የውጭ ምንዛሪ ገቢ በማስገኘትና ለዜጎች የስራ እድል በመክፈት ረገድ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል ፡፡

ኢንጂ ፈርኒቸር በአሁነ ጊዜም ምርትና አገልግሎቱን በውጤታማ ስልትና በላቀ ደረጃ በማስተዋወቅ ቢዝሱን በከፍተኛ ጥራትና ቅልጥፍና ለማሳደግ ፤ “ ተወዳጇን አርቲስት ሃናን ታሪክን ታዋቂ ኢትዮጵያዊ የኩባንያው የብራንድ አምባሳደር አድርጎ በዛሬው ዕለት በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል አስፈርሟል።


ቴዲሾው መልቲ ሚዲያ
ህጋዊ ሰውነት አግኝቶ በማስታወቂያ የስራ ዘርፍ የተሰማራው ቴዲ ሾው መልቲ ሚዲያ፤ ባለፉት አምስት አመታት ባደረገው ጥረት፤ በርካታ የቪዲዮና የድምፅ ማስታወቂያ ክርኤቲቭ ፕሮዳክሽን ስራዎችን በጥራት በማከናወን ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ደንበኞች አስረክቧል፡፡

ከዚህ አንፃር ቴዲ ሾው የማስታወቂያ ኢንዱስትሪውን ከተቀላቀለ ወዲህ ማከናወን ከቻላቸው ስራዎች የሚከተሉት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፤

• ከ300 በላይ የቴሌቪዥን ማስታወቂያዎችን ለአገር ውስጥ ድርጅቶች ሰርቶ አስረክቧል

• ከ225 በላይ የሬዲዮ ማስታወቂያዎችን ለአገር ውስጥ ድርጅቶች ሰርቶ አስረክቧል

• 7-የቪዲዮና የኦዲዮ ፕሮዳክሽንኖችን በመስራት፤ በውጭ አገር ለሚገኙ ዓለም-አቀፍ ጅርጅቶች አስረክቧል

• እስካሁን 8-የብራንድ አምባሳደር ማስታወቂያ ስራዎችን የስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ያዘጋጀ ሲሆን፤ በዛሬው እለትም ባዘጋጀው ዘጠንኛው የብራንድ አምባሳደር ፊርማ ስነ-ስርአት፤ አናን ታሪክ የተባለቸውን ታዋቂ ኢትዮጵያዊ አርቲስት ከቡሩል ትሬዲንግ ጋር በከፍተኛ የኢትዮጵያ ብር በማፈራረም ስራ አስጀምሯል፡፡

News today

ሩሲያ

ሩሲያ በድል ላይ ድል እያደረገች ነው አሁን ደግሞ በአርክቲክ ባህር ላይ 82 ሚሊየን ቶን ጋዝ አግኝታለች

Ethiopia ሩሲያ መላውን ሉሀንስክ ተቆጣጠረች በዚህም የሞስኮ ኗሪዎች ሀገራቸው ደል በማድረጓ አዲስ ውሳኔ ወስነው አክብረዋል በዚህም መሰረት የአሜሪካ ኤምባሲ የሚገኝበትን አከባቢ የዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ሲሉ የኢንግሊዝ ኤምባሲ ደግሞ የሉሀንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ሲሉ ሰይመውታል።
News today, Politics

ቱርክዬ በሽብር የተከሰሱ ኩርዶች ተላልፈው እንዲሰጧት

ቱርክዬ በሽብር የተከሰሱ ኩርዶች ተላልፈው እንዲሰጧት ለስዊድን ያቀረበችው ጥያቄ ውድቅ ሆነ

አንካራ 70 የኩርድ ታጣቂዎችን እንድትሰጣት ስዊድንን ብትጠይቅም ተቀባይነት አለማግኘቷ ተገልጿል፡፡
ሆኖም ስዊድን እና ፊንላንድ የአንካራን ጥያቄዎች የማያሟሉ ከሆነ የኔቶ አባልነታቸው ጥያቄ ውስጥ እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን አስጠንቅቀዋል፡፡
ስዊድን እና ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን ተፈራርመዋል፡፡ አባልነታቸውን ተቃውማ የነበረችው ቱርክዬም የኋላ ኋላ ጥያቄያቸውን ተቀብላለች፡፡
አሁን ግን ጥያቄዎቿ ካልተሟሉ ወደ ድጋፏን ልታነሳ እንደምትችል ነው አንካራ የዛተችው፡፡

News today, social life

ስለቀጠለው የወለጋ ጥቃት

አቶ ደመቀ መኮንን ”በወለጋ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል ይደረጋል” አሉ

ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፤ በዜጎች ላይ ተጨማሪ ጥቃትና ጭፍጨፋ እንዳይከሰት በሁሉም አካባቢዎች ተጋላጭ ቀበሌዎችንና መንደሮችን በመለየት አስፈላጊው ጥበቃ እንደሚደረግ ገለጹ።

ከዚህ ባለፈም ነዋሪው ራሱን በተደራጀ መልኩ እንዲከላከል የሚሊሻ እና የኮሙኒቲ ፖሊሲንግ ስርዓት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚደረግም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት።